ልጥፎች

እልል በል አማራ!

ምስል
  እልል በል አማራ!                                            ከሥርጉተ ሥላሴ 10.06.2010 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።)                               „እሱም ጥበብንና ምክርን ይገልጥለታል፣ የተሠወረውን ይገልጥ ዘንድ ያሳስበዋል።“                                                        („መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፴፱ ቁጥር ፯“) አንተ እናት ሆዱ እግዜሩን አማኙ፣ አንተ አንጀት አራሹ ትህትናን ተናኙ፣ አንተ ቅን ወተቱ ፍቅርነን ተመኙ፣ ስትሞላ የሰው ጓዳ ስትድር ጠጋኙ፣ አንተኑን እራስተህ ለሌሎች ሥንኙ ። እልል በል አማራ አንተ መከረኛ፣ እልል በል አማራ አንተ አሳረኛ፣ እልል በል አማራ እዬሞትክ ተረኛ፣ አንተ አናጋች በመሆን ለጋስ ተረብኝ፣ አልቀህ ባታልቅለት ለዘመን ወረተኛ፣ ቀንህ ጆሮ ገዛ የአብን ሁነኛ! እኔስ እልሃለሁ ከልቤ ታድሜ፣ እኔስ እልህለሁ ከውስጤ አስቀምጬ፣ እኔስ እልሃለሁ ድምጼነን ሰጥቼ፣ ከእንግዲህ ጅልነት አውልቀህ ጣል ብዬ። አንተ ገራገሩ የዘመናት ትንግርት፣ አንተ ብሩኽ ማዕልት የመቻል ትዕይንት፣ አንተ ግማደኛ የእንትዬ ትፍስህት፣ ስትጋፋ የኖርክ የደሙ ግብረኛ፣ ለባድማ ትውስት፣ ምን አትርፈህ ከቶ ከማገዶ ትርሲት? መሸከም ብቻ እንጂ የዕንባን መፈለጥ። አልል በል አማራ ደስ ይበልህ ከቶ፣ አቅምህን ብልሃትህ ሁሉነን አካቶ፣ የህልውና አብራክ መኖርህ ታክቶ፣ በብርሃና አገር ጨለማህ በርክቶ፣ የለህምም ተብለህ በእሬትም ተቦክቶ፣ ሃምሌ 5 መጣልህ የድል ብሥራት ተግቶ። እልል በል አማራ አንተ የማዳን ቀኑ፣ እልል በል አማራ አንተ የቀደምት - ፊ

የአብን መሥራች ጉባኤ ልዩ የምሥራች ነው - ለእኔ።

ምስል
            የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ                   መሥራች ጉባኤ                   ታላቅ           የምሥራች ነው።                                           ከሥርጉተ ሥላሴ ሲዊዘርላንድ 09.06.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።)                                    „ሁሉ በሥላሴ ፈቃድ ተፈጥሯልና፣ ይህ ለምንድን ነው ያ ለምንድን ነው የሚል የለም።“                                                              (መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፴፬ ቁጥር ፳፩) ብሥራት አባተ። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ መሥራች ጉባኤ በባህርዳር እዬተካሄደ ስለመሆኑ ዛሬ ግንቦት 09.06.2018 ከሚሊዮኖች ድምጽ ከጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሽፈራው እና ከዘሃበሻ ደስ የሚል ዜና አሁን ተደምጧል። ይህ ትውልድ ከቶውንም ሊረሳቸው የማይችለውን የሰብዕዊ እና የሰላማዊ ትግል መብት ተሟጋቹን የፕ/ አስራት ወልደዬስን ቅዱስ መንፈስ በባዕቱ ዳግም ትንሳኤውን ያወጀ እጅግ ታሪካዊ የምሥራች ነው። አማራ ለ43 ዓመት በሥውር ህሊናው ሲመዘበርበት የነበረውን ዘመን ማክተሚያሚ ላይ ይህ መረጃ ሲመጣ ታላቅ የሰናይ ቀን ነው። አማራ አቅሙን፤ ብልህነቱን፤ ችሎታውን፤ ተመክሮውን፤ ክህሎቱን፤ ሰብዕናውን፤ በራሱ አቅም ልክ ፖለቲካውን ዕውቅና እና ተቀባይነትን አስጥቶ ትውልዱ የሚሻውን ማናቸውንም የዜግነት ሙሉ መብት በእኩልነት ለማስከበር የሚያስችል ቁመና ላይ ለመገኘት ብዙ መጣር አለበት። ሥሙን ወድጀዋለሁኝ። አማራ አገሩ ኢትዮጵያ ናት እና። ገና ውጥን ስለሆነ ተጠልፎ እንዳይወድቅ ከኦህዴድ ብልህ መሪዎች ሰፊ የሆነ ተመክሮ መውሰድ አለበት። ኦህዴድ በራሱ ላይ በ

የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን)

ምስል
በአማራ ምሁራን የተቋቋመው የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ( አብን ) በባህርዳር የፓርቲውን መመስረቻ ጉባኤ ማድረግ ጀመረ June 9, 2018 |  Filed under:  News Feature , የዕለቱ ዜናዎች  |  Posted by:  Zehabesha ( ዘ - ሐበሻ ) በአማራ ምሁራን የተመሰረተውና    የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ( አብን ) በሚል የሚጠራው አዲሱ ፓርቲ በባህርዳር ከተማ የመመስረቻ ጉባኤውን እያደረገ መሆኑን ለዘ - ሐበሻ የተላከው መረጃ ጠቁሟል :: የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ; የአማራን ሕዝብ በሁሉም መልኩ ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥና በተለያዩ አካባቢዎች ክልሉ ህዝብ ላይ እየደረሱ ያሉ ጥቃቶችን የመከላከል ዓላማ በመያዝ መቋቋሙን በባህርዳሩ መመስረቻ ጉባኤ ላይ ተነግሯል :: በባህርዳር ሙሉዓለም አዳራሽ ዛሬ የተጀመረው ጉባኤ በነገው ዕለት እሁድ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል :: በጉባኤም ድርጅቱን የሚመሩ የአመራርና የብሄራዊ ምክር ቤት አባላት ምርጫ እንደሚደረግ ይጠበቃል :: በነገው ዕለትም ለህዝብ ክፍት እንደሚሆን ተገልጿል :: የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄን የመሰረቱት    19 ሰዎች በህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲ ምስረታ ሂደ ድጋፍ በሚያሰባስቡበት ወቅት በኮማንድ ፖስቱ መታሰራቸውና መለቀቃቸው አይዘነጋም :: ምንጭ ዘሃበሻ ዘገባ። https://www.zehabesha.com/amharic/archives/91865#respond

አዲሱን የአማራ ፓርቲ ማን ወለደው?

ምስል
አዲሱን የአማራ ፓርቲ ማን ወለደው ?     ከጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው June 9, 2018 | Filed under: የዕለቱ ዜናዎች | Posted by: ዘ - ሐበሻ ዛሬ ሰኔ 2/2010 ዓም በባህርዳር አዲስ የአማራ ፓርቲ ምስረታ ጉባኤ ተጀምሯል። በምስረታው ላይ ሁለት አይነት “ የሕዝብ ” ስሜት ይብፀባረቃል። አንደኛው ደስታ ነው። ሁለተኛው በጥቅሉ ትችት ይመስላል። በዘር ተደራጁ የሚል። ደስታው ሕዝብ ወኪል ከማጣቱ የመጣ ነው። የሕዝብን ብሶት የሚያሰማ አካል በመጥፋቱ አማራጭ ተገኘ ከሚል ነው። የትችቱ ስሜት የሚመጣው አማራ እነ መለስ በተለሙት የዘር ቀመር መደራጀት የለበትም ከሚል የቅንነት የሚመስል ሙግት፣ የአማራው ሕዝብ በማንነቱ ከተደራጀ ቦታ አናገኝም ከሚሉ ቡድኖች ስጋት ይመስለኛል። በዚህ ወቅት የአማራ ሕዝብ አይደራጅ ለማለት ይህን ህዝብ የሚታደግ ሌላ አማራጭ ያስፈልጋል። ሁለት አማራጮች አሉ ሊባል ይችል ይሆናል። ·          አንደኛው የትህነግ / ህወሓት ተላላኪ ሆኖ የአማራን ሕዝብ ሲያስገዛ፣ ሲያስገድል፣ ሲያስዘርፍ የኖረው ብአዴን የሚሉት ቡድን ነው። ይህ ቡድን የትህነግ / ህወሓት ወኪል ሆኖ የአማራን ሕዝብ ላይ በደል ሲፈፅም የኖረ እንጅ ለህዝብ የሚሰራ አይደለም። ·          ሁለተኛው አማራጭ አንድነት ሀይሉ ነው። ብአዴን የአማራውን ስም እየጠራ አማራን ሲበደል ኖሯል። የአንድነት ሀይሉ በበኩሉ አማራ አይደራጅ ከማለት አልፎ ስለ አማራ መናገርን ነውር አድርጎታል። ገዥዎቹ ከመነሻ