ልጥፎች

እናት የክት እና የዘወትር ልጅ የላትም ...

ምስል
ሾጣጣ። „ልጄ ሆይ ቃሌን ጠብቅ፤ ትእዛዜንም በአንተ ዘንድ ሸሽግ።“ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፯ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ 02.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ሾጤ - ሞጤ - ሽም ጤ  - ሾጣጤ - ሞጣጤ  - ሞጥሟጤ። ሁሎችም ቃሎች ናቸው። ሁሎችም እኩል መብት እና ግዴታ አለባቸው። ሁሎችም የአማርኛ ቋንቋ አባልተኞች ሽሙንሙኖች፤ ሸባላዎች፤ ሸንቃጣዎች ናቸው። ሁሎችም የስዋሰው ቤተኞች ናቸው። ሁሎችም መነሻቸው ከአማርኛ ፊደላት ነው። ሁሎችም ባለድምጽ፤ ባለ ቃና፤ ባለ ደንብ፤ ባለ ጌጥ፤ ባለ ዘለበታዊ ምት፤ ባላ ዜማ ናቸው። እኩል ናቸው ማለት ነው። እኩልነት እንዲህ ሲገልጥ የልብ ያደርሳል።  ኢትዮጵያዊነት እንዲህ ቢሆን ምኞቴ ነው። በመኖር እና በመኗኗር መሃከል ግን መኖር ለሁሉ ተፈጠረ፤ ግን ለሁሉ ለመሆን አቅመ ቢስ ነው። ስለሆነም መኖር ወይ እረኛ ነው ወይ ደግሞ የታገተ ነው። ወይ ደግሞ ዲዳ ነው ወይ ደግሞ ሰውር ብቻ።  „አይዋ መኖር“ ተብሎ ሲጠራ „አለሁ ለሁሉም“ ሲል ይደመጣል፤ አንዱን ሲያንጠለጥል አንዱን ሲያፈርጥ አንዱን ሲካለ ሌለውን ሲከውን፤ አንዱን ሲያቆምስ ሌላውን ሲያሰምጥ ብቻ አለሁኝ፤ አኗኗርኩኝ፤ ተኖርኛ ጋር ሆንኩኝ ይለናል ወገኛ በሉት ///  አሁም ማን ይሙት አይዋ መኖር አለሁኝ ለሁሉ፤ ሁለማንም ሆንኩኝ ሊል ነውን? አብሶ ለእጣ የለሾች ባለሾጣጣ ዕጣ ፈንታዎች አዳብለኳቸው ቢል ይመረጣል። አይዋ መኖር ግድዬለሽ ነው። አንዱን ሲያገዝፍ ወይንም ሲያስገዝፍ ሌላውን ደግሞ አጫጭቶ ሲያከስም ወይንም ሲያስተንን፤ አንዱን ባለዝናር ሲያደርግ እና አኮፍሶ ሲያስጀግን ሌላውን ትጥቅ አልቦሽ አድርጎ በዳዴ አንበርክኮ ሲያስኬደው አኗናርኩት፤ ከእኔ ወዲያ እኩልነት እና ነፃነት አዳይ ላስር ብሎ

እናላችሁ ... ስለ አቶ መላኩ ፈንታ/ ቴ

ምስል
ሚዛናዊ ሆነ የማዬት ተደሞ። „የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል፤ እግዛበሄር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።“ ምሳሌ ምዕራፍ ፲፮ ቁጥር ፱ ከሥርጉተ©ሥላሴ 02.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·        መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=SDNaiNMzENY „አቶ መላኩ ፈንታ የአቶ በረከት ስምኦንን ሚስጢ ዘረገፉት“ ·         መ ቅድመ ተደሞ። ዛሬ ፏ ብሏል። ፏ ብሏል ስላችሁ ግን ልዕልተይ ተገኝታለች ማለቴ አይደለም። እሷ የለችም። ፊታውራሪ የሰማይ መስኮትም በበቀኝ ዛሬ ቀና ሆኗል። ካፌያ ነገረሩንስ ሳይቀር ተቆጠብ ብሎ ደንግጓል እንደማለት። ኮነሬል ዳመናም እስቲ ይሁናችሁ ብሏል። ስለሆነም አዬሩ የሚመች ብርሃን ያለበት ብራ ሆኗል እላችሁአለሁኝ። ግን እንዴት ናችሁ የኔዎቹ ውዶቹ ነፍሶቹ? ደህና አላችሁልኝ ወይ? ኢትዮጵያዊነት እኔን መጨመረ አለበት - እናንተንም። እኔን መጨመር ያልቻለ ኢትዮጵያዊነት፤ እናንተንም መጨመር ያልቻለ እትዮጵያዊነት በአፍንጫዬ ይውጣ ትላላች ሥርጉትሻ። ስንቱን ነገር እምቅ አድርጋ ተሸክማ መኖሯን እሷና እና ጥቂት ቅን ወገኖቿ ያውቁታል እና። እራሱ አካሉን፤ ስደተኛ ወገኑን፤ ጤና ያጠውን ወገኑን ሰርዞ፤ ሲያስድድ የነበረው ሁሉ ተቆጥሮ ነው ኢትዮጵያዊነት የሚበለው። በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ የወገንን ሰብዕና ምሶ ሲቀብር የኖረው፤ አጋጣሚውን ሲያገኝ ከራሱ ክብር እና ዝና በስተቀር፤ የሌላውን ውስጣዊ፤ ማህበራዊ ሰላም ሲጨምቅ የኖረው ሁሉ ልሙጡን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ዓላማ ስለለበስ ለሥርጉተ የታይታ እንቆቅልሽ ነው - ነገረ ተረብ።  ኢትዮጵያዊነት አስተዋይነት ነው። ኢትዮጵያዊነትም ሚዛናዊነትም ነው። መጀመሪያ ስደተኛ ወ

ናፍቆትን መገደብ ለነፍስ ራህብተኞች ሃጢያት ነው ...

ምስል
ሳቅን፤ ናፍቆትን ለመገደብ የታደመው ዕሳቤ ወቅታዊነት ይጎድለዋል። „ማንም ራሱን አያታልል፤ ከእናንተ ማንም በዚች ዓለም ጥበበኛ የሆነ ቢመስለው ጥበበኛ ይሆን ዘንድ ሞኝ ይሁን።“ ወደ ቆረንቶስ ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፲፰ ከሥርጉተ©ሥላሴ 01.09.2018 ከጭምቷ ሰዊዘርላንድ። ·         የጭብጥ መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=en5MiO0Tq1w #EBC   አድማ የመቱ የሲቪል አቪየሽን ሰራተኞችን በመተካት ለሰሩ ሰራተኞች እውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው፤   ·        መቅድመ ነገር። የኔዎቹ እንዴት ናችሁ? ትናንትም ዛሬም ደምኗል። ትናንትም ዛሬም ልዕልተይ የለችም። ትናንትም ዛሬም ብትጠራ ዓይኔን ግንባር ያድርገው ብላ፤ ጠላታችሁ እልም ይበል እልም ብላለች። ትውር አላችም። እናም እኛ ምናችን ሞኝ ነው ደረትረት ብለን ጉብ ብለናል። ግን ያው እንደ ዳሽን ተራራ ከንፈራችን በልዕልተይ ላይ ነፋ አድርገናል።  ያካፋል፤ ያበራል፤ እንገናም ያካፋል እንደ ገናም ይባራል በቃ እንደ ወርህ ሚያዚያ ቅጥ አንባሩ ጥፍት ያለበት ቀን ነው ዛሬ። ብቻ በዚህ ዓመት የተሻለ የበጋ ጊዜ ስለነበር እንዳሻት ሙቀቷን አክስክሳናለችና አሁን ብትመጣም ብትቀርም እንደ ፍጥርጠሯ ብለናል ስለ አውሮፓዊቷ እሜቴዋ ጠሐይ። ·        የወ ግ ገበታዬን እስቲ ዘለግ አድርጌ ላስኪደው… እንዲህ … የአብዬሽን ሰራተኞች ካለፈው ሰኞ ጀምሮ የሥራ ማቀም አድማ ለመምታት አቅደው ነበር። መቼም ዜናው ሲሰማ ጎሽ፤ ደግ አደረጉ ልላቻው እልቻልኩም። ምክንያቱም ወቅታዊነቱ የሴራ ይመስል ስለነበር። ስለምን ዓውዳመትን ታክኮ አድማን ለመከወን ታሰበ? እኔ የሠራተኛ ማህበር አደራጅ ነበርኩኝ።

ነፃነት ከኖረ ድል ከሃሳብ አቅም ይመነጫል።

ምስል
ሃሳብ የማያቋርጥ ጅረት ወይንም ፏፏቴ እንጂ የታቆረ የኩሬ ውሃ አይደለም! „እሱን እግዚአብሄር ስለመረጠው ጌትነቱ እንደ እጁ ሥራ ነውና ባለመድኃኒትን አክብረው።“ መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፴፰ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ 31.08.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ                                   ትውልድ በፍቅር ማዋህድ የአብይ ሌጋሲ ነው!  ስለዚህም ሊከበርም- ለወደድም ደሊደነቅም ይገባል።  ነገን በፍቅር ማሰብ፤  በእዮባዊነት መቀመር መክሊቱ የእዮር ነው። ተመስገን!  43 ዓመት የተባከነበትም የተተረፈበትም፤ የተጎዳንበትም የተጠቀመንበትም ዘመን ታይቷል - ተፈትሿል። እግዚአብሄር በቃችሁ ሲለን ይህን ዘመን አመጣልን። በዚህ ዘመን ያኮረፉ እንዳሉ ይታወቃል። በዚህ ዘመን ምንም ለውጥ አልመጠም የሚሉ ወገኖችም እንዳሉ ይታወቃል። በዚህ ዘመን የተሻለ ዘመን መጥቷል የሚሉም አሉ።  በርከት ያለነው ደግሞ የተሻለ ሳይሆን የ43 ዓመቱን ዘመን የሚያስንቅ ብሩህ ተስፋን የሰነቀ ነው የምንል ደግሞ አለን። ሰዎች እንደመሆናችን ስለምን ሬድ ሜድ ሃሳብ አልኖረንም ሊባል ግን አይገባም። በሌላ በኩል መልካም ነው በርቱ የምንል አለን፤ መልካም አይደለም የነበረው ይሻል ነበር የሚሉም አሉም። ከነበረውም ከአሁንም ያልሆኑ ወገኖችም አሉ። ወለሌ ገበታ ላይ ያሉም አሉ። ይህም ቢሆን የእናት ሆድ ዥንጉርጉር ስለመሆኑ ስለሚያጠይቅ ተስፋ አስቆራጭ አይደለም።  በሌላ በኩል ደግሞ ፍጽና የሚጠይቁ ሰዎች አሉ፤ ሌሎች ደግሞ ፍጹም የሆነ የተባረከ መንገድ ነው የሚሉም አሉ፤ ጥቂት የማይባሉም ፍጹም ነውም አይደለም የማይሉ አባ እና እማ ዝማታዎችም አሉ። ማዕዶታችን ሰፊ ስለሆነች ሁሉንም የማስተናገድ አቅም አላትና እንደ እ