የህሊና ሪህ
የህሊና ሪህ። „እኔ ግን ንጉሤን ሾምሁ በተቀደሰው ተራራዬ በጽዮን ላይ።“ መዝሙር ፪ ቁጥር ፮ ከሥርጉተ©ሥላሴ 12.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። መነሻ። https://www.zehabesha.com/amharic/archives/91906 « እኔን እጎዳለሁ ብለህ መሃል ሰፋሪውን አድማ አስተማርክ » | አቻምየለህ ታምሩ ነገረን ነገር ሲያመጣው .. . እኔ አማራ የሆንኩት አቶ አቻምየለህ ታምሩ በቪዥን ኢትዮጵያ ጉባኤ ላይ ተጋብዞ ጊዜ ፈጀህ ተብሎ ሁለት ደቂቃ ሲለምን እና ሌሎች ደግሞ የተሰጣቸውን ዕውቅና አክብሮት ሳይ ነበር በዛች ቅጽበት አማራነቴ ውስጤን ያሟሸው። ጥቃት አልወድም! እና ሁልጊዜ ሥሙን ሳይ የአቻምን የእኔ አማራነት የመሆን ፈቀድ ከሱ ነፍስ ጋር የተያዘዘ ስለመሆኑ አዘክረዋለሁኝ። የአማራነቴ ሥጦታ የመጣው ከአቻም መገለል ጋር በፅኑ የተያየዘ ነው። ከእንግዲህ ወደኋላ እንደ አልመለስ አድርጎ ደግሞ ቅኑ የጎጃም ህዝብ በደሙ አትሞበታል። የጎጃምን የመሆን ልቅና ያዬሁበት ዘመን በዚህ የአማራ የህልውና የማንነት ተጋድሎ አብዮት ዘመን ነው። የጎጃም ህዝብ የቅኔ ጉባኤ አቅም እና ቃልኪዳን አማራነቴን የበለጠ አድምቆልኛል። እሰቃለሁኝ እኔ እዚህ በአማራ ጉዳይ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት በአማራ ክልል ብቻ አማራነትህን ጣል ቲያትር ሲተውን። እሚሆን አይደለም። በልዩ ሁኔታ አማራኔቴ ልክ እንደ ፆታዬ ክብሬ ሆኗል። የአብይ ሌጋሲ ይልቅ ባይደክም ደስ ይለኛል። ሥርጉተ ሥላሴ እኮ ሞገደኛ ናት። የእሷን ልብ፤ የሷን ፍቅር፤ የእሷን ታማኝነት ለማግኘት ብዙ መድከም ያስፈልጋል። እኔ ስላልኩት ሳይሆን ከልጅነት እስከ እውቀት የሚያውቁኝ ሰዎች ያውቁኛል። አብሬያቸው የሠራሁት እንደ ዕድል