ልጥፎች

ሥርዓት አልበኝነት ክብር ሳይሆን ውርዴትም ውርዴም ነው።

ምስል
ጨካኝነት ወደ እንሰሳነት የመቀዬር ዋዜማ ነው። „ከቀና ህግ ወጥተን ሳትነ የክርስቶስ ብርሃን ረድኤቱ አልተገለጠልንም፤ ክርስቶስም ለኛ አልተወለደልንም።“ መጽሐፈ ጥበብ ምዕራፍ ፭ ቁጥር ፮ ከሥርጉተ©ሥላሴ 29.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።   መቅድም።  በምንም ሁኔታ ጭካኔ ዓይን ሊሰጠው አይገባም። በምንም መስፈረት አረመኔነትን ዝም ልንለው አይገባም። ወንጀልን ወንጀል ስለመሆኑ ልናወግዘው እንጂ ልንከባከበው ወይንም ግርዶሽ ልንሰራበት አይገባም።  ሰባዊነት ነው ሰውን 'ሰው' የሚአሰኘው። የሚያደርገውም። ርህርህና ነው ሰው የሚያሰኘው። አዘኔታ ነው ሰው የሚያሰኛው። የሰው ልጅ ከርህርህና፤  ከአዘኔታ ወጥቶ ጭካኔ መሪው ካደረገ ያ ሰው ወደ እንሰሳነት ተለወጧል ማለት ነው።  ከአዕምሮውም የጎደለ ነገር አለ ማለት ነው። እንደ ሰው ማሰብ ከልተቻለ ወደ እንሰሳነት የመለወጥ መለያነት ነው።  ሰው መሆን ማለት እኮ ከእንሰሳ ዓለም መለዬት ማለት ነው። በሌላ በኩል እናት የምትባል ልዩ ፍጥረት አለች። ሁልጊዜ እናት ልጇ ጎልማሳ ሆነ አዛውንት ልጇ ለእሷ ሁልጊዜ እምታዬው ልክ እንደ ህጻን ነው። እናት አብሶ የአላዛሯ ኢትዮጵያ እናት ባላባራ የዘመናት ጦርነት የልጅ ብርንዶ አቅራቢ ናት። መፍትሄ ለሌለው ማናቸውም በትረ ስልጣን ልጇኝ ስትገብር ኖራለች የኢትዮጵያ እናት። እናት የኢትዮጵያ እናት እንጨት ለቅማ ሽጣ፤ ኩበት ለቅማ ሽጣ፤ እንጀራ ጋግራ ሽጣ፤ በቀን ሰራተኝነት ተቅጣራ ላቧን አንጠፍጥፋ፤ የሰው ፊት ገርፏት ወጥታ ወርዳ፤ የረባ ልብስ ሳይኖራት፤ የረባ የለማ የጣመ ሳትመገብ፤ አንጀቷን አስራ፤ ሙሉ ቀን ስትባትል ውላ ስትባትል አድራ፤ ዓመት ይዞ እስከ አመት በታከተ እድል ፍዳዋን

ትእግስት ሲያልቅ እንዲህ ፍቅር ይሰደዳል። አማራ አምሯል!

ምስል
„በሰዎችና፡ በመላእክት፡ ልሳን፡ ብናገር፡ ፍቅር፡ ግን፡ ከሌለኝ፡ እንደሚጮኽ፡ ናስ፡ ወይንም፡ እንደሚንሽዋሽ ው ፡ ጽናጽል፡ ሆኜአለሁ። ትንቢትም፡ ቢኖረኝ ፥ ምሥጢርን፡ ሁሉና፡ እውቀትን፡ ሁሉ፡ ባውቅ፡ ተራሮችንም፡ እስካፈልስ፡ ድረስ፡ እምነት፡ ሁሉ፡ ቢኖረኝ፡ ፍቅር፡ ግን፡ ከሌለኝ፡ ከንቱ፡ ነኝ። ድሆችንም፡ ልመግብ፡ ያለኝን፡ ሁሉ፡ ባካፍል፥ ሥጋዬንም፡ ለእሳት፡ መቃጠል፡ አሳልፌ፡ ብሰጥ፡ ፍቅር፡ ግን፡ ከሌለኝ፡ ምንም፡ አይጠቅመኝም።“ ( ዬሐዋርያው ዬቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት ወደ ቆረንቶስ ሰዎች ምዕራፍ ፫ ቁጥር ከ፩ እስከ ፫ )   ሥርጉተ©   ሥላሴ   23.12.2016  ( ዙሪክ  –  ሲዊዘርላንድ )                                                ማን ሲተኛ!                                    መነሻ ጎንደር የአማራ ተጋድሎ ህሊና!                                 የአማራ ተጋድሎ ብሌን ጎጃም!                                          የአማራ ማንነት ተጋድሎ ሰብል!                                       ገድለ የአማራ ተጋድ ሎ!               የሐምሌ አቦዬ ገደል ዛሬን እንዲህ አሳመረው!                                     28.10.2018                                   የአማራ ተጋድሎ ነባቢት ባህርዳር!                                                   ዛሬ እንዲህ ...        

የፊደላት ለዛ /ሥነ ግጥም/

ምስል
„የባሪያቱን ነፍስ ደስ አሰኛት፤ አቤቱ ነፍሴን ወደ አንተ አነሳለሁና።“ መዝሙር ምዕራፍ ፹፭ ቁጥር ፬ ሥርጉተ©ሥላሴ 28.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ                       ምላስ - በሩህ        ይ .... ደላላል። አፍ - በህይወት        ይ .... ንጋግዳል። ዘመን - በዕብለት        ያ .... ተራርፋል። እፍኝ - በህዝብ        ይ ..... ቀላልዳል። ጭብጥ - ነሺ        ጥጋብ ይላል። እርስ - በእርሱ        ይ .... ማማል። እርስ - በእርሱ        ይ .... ቃረናል። መላው ሁሉ        ይ .... ወላልቃል። ትርምስምሱ        ያኔ ያልቃል። ዕውነት በጊዜው        ይ .... ደምቃል። ·          ሥጦታ ... ዕውነት ህይወታቸው ለሆነ ወገኖቼ በሙሉ። ·          ተስፋ መጽሐፍ ለህትምት የበቃ። 1985 ዓ.ም ድል ገብያ ገብርኤል - ·          አዲስ አበባእርእስ ጭብጥ ነሺ። ·            የኔዎቹ ኑሩልኝ። ማለፊያ ሰንበት ቸር ወሬ ያሰማን ፈጣሪያችን።

ሥነ ግጥም።

ምስል
„አቤቱ ጆሮህን ወደ እኔ አዘንብል አምጠኝም።           ችግረኛ እና ምስኪን ነኝና።“ መዝሙር ምዕራፍ ፹፭ ቁጥር ፩ ሥርጉተ©ሥላሴ 28.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ                                                             መኖር ስንክሳሩ                                     ሲንር እና ሲከር                             ሲለዝብ ሲወይብ                      ጥንዝል አቅፎ ሲዞር                ሲያዝል ሲያደናብር               አሉት አሉ መኖር ?                    መኖር ስንክሳሩ                 መራራ ስንቅ ሲድር                  ሳቅንን ሲ ያ በርር                         ተስፋነን ሲቀብር                                እንዲህ ሲያደናግር ///   ሲያጨማትር                                       ጥርቅም - ጥንቅር፤ ሲድር                                        „ እኔን “ ሲያጣጥር፤   ሲያሳጥር                                         ቋሳነን ሲሸርብ                                         ተሰፋን ሲሰነ ጥ ር                                          ጨለማ ሲያስጨፍር                                           እኔን ሲያኮማትር                                            እኔን ሲጠዘጥዝ