ልጥፎች

መሆኑን ሳይ አልደነቀኝም።

ምስል
መሆኑን ሳይ አልደነቀኝም። „የጣኔዎስ አለቆች ፍጹም ሰነፎች ናቸው፤ ፈርኦንን የሚመክሩ ጥበበኞች ምክራቸው  ድንቁርናን ሆነች።“ ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፲፱ ቁጥር ፲፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ 07.11.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ። ዛሬ ጎልጉል ድህረ ገጽ ገብቼ ነበር። አንድ ጹሑፍ አገኘሁ እና ቀልቤን ስለሳበው አነበብኩት። እኔ ጀርመን ላይ አቶ ሺመልስ አብዲሳ ሲገኙ በምን አግባብ ብዬ ሁሉ ጽፌ ነበር። ስለ አቶ ሺመልስ አብዲሳ የጠቅላይ ሚኒስተር ጽ/ቤት ሃላፊ ስለመሆናቸው በፎቶ የተደገፈ ዘገባ ነበር ጉግል ላይ ያገኘሁት። ካወጡት አስተያዬቴንም ከሥር ጽፌበታለሁኝ። http://www.goolgule.com/shimeles-abdissa/ ሽመልስ አብዲሳ አዲሱ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ / ቤት ኃላፊ ለእኔ እጅግ አዎንታዊ በሆነ ሁኔታ በዛ ወጀብ በበዛበት ጊዜ በጠ/ሚር አብይ እጩነት አቅም ጎን በመሆን ምስክርነት የሰጡ አንድ የኦህዴድ/ አዴፓ ሊሂቅ ቢኖሩ አቶ ካሳሁን ጎፌ ብቻ ነበሩ። ለቦታውም ምጥን ያለ፤ ክውን ያለ መረጃ በመስጠት እረገድ አቅማቸው አዬር ላይ አንቱ ነበር። አሁን የት እንደ ገቡ አላውቅም። የሆነ ሆኖ አቶ ሽመልስ አብዲሳ ውስጣቸው ከአቶ አዲሱ አረጋ የተለዬ አቋም እና ምልክታ ይኖራቸዋል ብዬ አላስብም። ነገር ግን አሁን ባለው ሁኔታ ስጋትም ተስፋም ሁለቱም በእኔ ቦታ የላቸውም ።  ጊዜ የሚሰጠውን መረጃ ከማድመጥ ውጪ ማድመቅም ማጉላትም ማንኳሰስም በበቃኝ ተከውኗል። ብቻ ያው ኦህዴድ/ ኦዴፓ አንዱን አምጥቶ ሌላውን ቢሸኝ፤ አንዱን ሸኝቶ ሌላውን ቢያመጣ ያው የኦነጋውያን መንፈስ ተጽዕኖ ይለቀዋል ለማለት አይደፈርም። ጊዜ እዬጠበቁ የወጡ ዕውነቶች አሁን ከሆነ ሰብሰብ እንድንል ድርብ እና ድርጁ መል

የዘመን ልቅ መንገድ።

ምስል
የጥገናዊ ለወጡ ውጥንቅጥ የዘመን ልቅ መንገድ ፈተና። „በሰው ተፈጥሮ ያለ ሞትን መጠራጠር ፅኑ ነው።  ከናታቸው ሆድ  ከተወለዱት ጀምሮ በሁሉ እናት  በመቃብር ሆድ እስኪቀበሩ ድረስ በአዳም ልጆች  ላይ የከበደ ሞት አለ።“ መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፵ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ  07.112018 ጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ይህን የጥገናዊ ለወጥ ዝንባሌ የዛሬ ዓመት ደግፌ መፃፍ ስጀምር ዛሬ በዚህ መልኩ ይገኛል ብሎ ብዙ ሰው አላሰበውም ነበር። መልካሙን ነገር ድጠን በትችት ላይ ስለምንባዝን ነው እንጂ ኢትዮጵያ በዘመኗ እኛ ላለንበት ትውልድ በአዎንታዊነት እንዲዚህ ዓመት የዓለም ሚዲያ አመደኛ ሆኗ አታውቅም ነበር። ሐሴታችንም በውነቱ ልክ አልነበረውም። እኔ በግሌ ብዙ ደስታዎችን አግኝቻለሁኝ።  ቅድስት ኦርተዶክስ ተዋህዱ አህታዊነት ራሱ ገድል ነው። ሁለገብ ውጤቶቹም ህልም የሚመስሉ ነበሩ። ጉልበታም እና ጥበባዊ አቅሙም የሚታመን አልነበረም። ከዬት ተሰጠን እንዲህ ዓይነት ምርቃት ያሰባለ ነበር። ያ ሰበለ ም ነበር።  በሌላ በኩል ያው አሉ ለመባል ብቻ ጥቂት ሰዎች ሥማቸውን ጎላ አድርገው ሲያስጠሩ የነበሩትም የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት አባልነትም አብዛኞቹ እጃችሁ ከምን ሲባል ባ ዶ እጃቸውን ብቻ አገር ቤት እንደ ገቡ ይታወቃል። ፉከራው ቀረርቶው ማሰናከሉ ግን ሞገድ ላይ የነበረው ጉጉስ የብራና ቋቶች ይመሰክራሉ። ዛሬም አገር ገብተው ቀን ለውጡን መደገፍ ማታ በመናድ ላይ ሲታትሩ የተገኘው ብልጭታ በመጉሸት እና ተስፋ በመቀልበስ ጣረሞት ላይ ይገኛል። ብሄራዊ ሃላፊነቱን የተረከበው ኦህዴድ /አዴፓ በያዘው ጥንካሬ በእርጋታ መጓዝ ሲገባው በአማካሪ ስስነት፤ በራሱ ውስጥ የተፈጠረው የጦፈ ቅናት አድማ የተፈጠረው ስንጥቅ እ

አቶ ፍጹም አረጋ ከሃላፊነታቸው ተነሱ።

ምስል
አዲስ የፕሬስ ሴክረታሪ ለውጥ በጠ/ሚር ጽ/ቤት። „አቤቱ በልቤ ሁሉ አመሰግንህ አለሁ።   ተአምራትህንም ሁሉ እናገራለሁ።“ መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፱ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ© ሥላሴ  05.11.2018 ከገዳማዊቷ አገር ከሲዊዝ። በአዲሳዊነት ቀመር ፋታ ሳይሰጥ እዬገሰገሰ ያለው የጥጋናዊ ለውጥ ማዕበል ዛሬ ደግሞ አዲስ ነገር እያሰደመጠን ነው። አንዱንም በቅጡ አጣጥመን ሆድ ዕቀውን ዛረጋግፈን ፈትሸን ሳንቃኘው በዬዕለቱ በአዲሳዊነት መርህ ግብር ወደ ፊት የሚገሰግሰው የለማ አብይ ካቢኔ አሁን አዳምጡኝ እያለን ነው። በፎቶ በተደገፈ አጫጭር መረጃዎችን በማዕከልነት ሲያሰተናግዱ የቆዩት አቶ ፍጹም አረጋ በሌላ መተካታቸውን አዲስ ዜና እያደመጥን ነው። "ከአረጋ" ሥያሜ አንድ ቀነሰ እንደ ማለት፤ አቶ ፍጹም "አረጋ" አቶ አዲሱ አረጋ አቶ ዳዊት "አረጋ።" የሆነ ሆኖ እርእሱ እንዲህ ይላል። „Ethiopia:ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ስር የተቋቋመው የፕሬስ ሴክሬታሪ በይፋ ስራ መጀመሩን አስታወቀ“ ማድመጡን ትንታኔውን ለእናንተው የቤት ሥራ ሰጥቼ ሥርጉትሻ ሹልክ … https://www.youtube.com/watch?v=rBfiQz1fH0Q ሰላም ሲሆኑበት ችግርን የመፍተት አቅሙ አንቱ ነው። መሸቢያ ጊዜ። ትሁት አካባሪያችሁ።

ከወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም የአማራ ተጋድሎ ግብ አይጠብቅም!

ምስል
የሴቶች የፖለቲካ ዕውቅና ማግኘትን አንገት ማስደፋት ትልቅ የታሪክ ፍቀት ነው። „አቤቱ ምህረትህን ለዘላለም እዘምራለሁ እውነትህንም በአፌ ለልጅ ልጅ እናገራለሁ።“ መዝሙር ፹፭ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ  05.11.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። የሴቶች የፖለቲካ ዕውቅና ማግኘትን አንገት ማስደፋት ትልቅ የታሪክ ፍቀት ነው። የኢትዮጵያ ሴቶች በማንኛውም መስከ ለዘመናት የአገር አንድነት እና ሉዑላዊነትን ለማስከበር ጉልህ ተጋድሎ ያደረጉ ናቸው። የኢትዮጵያ ሴቶች ያልተሳተፉበት፤ ያልተሰዉበት አንድም የትግል መስክ አልነበረም። በሌላ በኩል በኢትዮጵያ የአገር ግንባታም የኢትዮጵያ ሴቶች ሁለገብ ተሳትፏቸው ቢልቅ እንጂ የሚያንስ አይደለም። የኢትዮጵያ ሴቶች ብልህነታቸውን፤ መክሊታቸውን፤ ጸጋቸውን፤ ስጦታቸውን፤ ጥበባቸውን፤ ብልህነታቸውን፤ ሁለመናቸው ሳይቆጠቡ ሳይሳሱ የሰጡ ድንቅ ፍጥረቶች ናቸው። የኢትዮጵያ ሴቶች በማናቸውም መሰክ የግንባር ቀደሙን ድርሻ በመውሰድ እኩልነታቸውን በዬዘመኑ በዬምዕራፉ አስመስከረዋል። ቀደም ባለው ጊዜም ቢሆን ለሴቶች የፖለቲካ ዕውቅና በመስጠት አጤዎች የአንስት እቴጌዎችን ምክራቸውን በማድመጥ፤ ብልህነታቸውን በመቀበል የብዙ ዕድል ባለቤት መሆን መቻላቸውን ታሪክ ያስረዳል። በ60ዎቹ የማርክስስት ሌኒኒስት ፍልስፍና ተጋድሎ ሂደቶች ውስጥም ሴቶች እኩል ተሳትፎ ቢያደርጉም ከፖለቲካ የተገለሉበት፤ እንዳሉም ያማይቆጠሩበት ለመስዋዕትነት ብቻ የሚፈለጉ የበይ ተመልካቾች ነበሩ። ከዚህም ሌላ የሰው ልጅ አቅርቦት ላይ ብቻ አትኩሮት ከማድረግ ውጪ ሴቶች ዜግነታቸውን በስልት የተነፈጉበት ወቅት ነበር። „እንዳያማ ጥራው እንዳይበላም ግፋው“ ዓይነት ነበር። አሁን ባለው የአማራ እና የኦሮሞ ተጋድሎ በተገኘው የለወ

ከብርት ፕሬዚዳንት ሳሀለ ወርቅ ዘወዴ ትውፊት ናቸው!

ምስል
መልካምነት ይበጃል። „ወደ ደጋግ ሰዎች የሚላኩ ሪቂቃን የሆኑ መላዕከት ብርሃን ናቸው።“ መጽሐፈ መቃብያ ከልዕ ምዕራፍ ፳ ቁጥር ፲ ከሥርጉተ©ሥላሴ 04.11.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።                       ዋው! የኮ/ ጎሹ ወልዴ ክብር አከበርኩት። ምኞቴም ተሳካ ተመስገን! የጭብጤ መነሻ አሉታዊ ነገሮች አቅም ማግኘት አይገባቸውም ነው። ክፉ ነገር ይወረናል። ክፉ ነገር ይገዛናል። ክፉ ነገር ያሰተዳድረናል - ፈቅደንለት። ቀና በሆኑ ጉዳዮች ላይ እንኳን ስምምነቱ ያን ያህል ነው። ታዲያ በዬት ታልፎ መልካም ነገሮች ሥር ይኑራቸው። ፍሬስ እንዴት ያፈሩ? መልካሞችን መልካም ለማለት ካልተደፈረ፤ መልካም ያልሆኑት መልካም አይደለም ማለት ካልቻልን ታዲያ እኛ ሰው መሆናችን ከምኑ ላይ ነው? እውነት ለመናገር አሉታዊ ነገር ወረራው መልካሞችን እንዳናይ ሸብቦናል። መለዬት አልቻልንም። በጣም ጥሩ የሆኑ መልካም ነገሮች ይታያል ኢትዮጵያ ውስጥ። እጅግ የሚመስጡ ጥሩ ነገሮች አሉ ኢትዮጵያ ውስጥ አሉ፤ አሁን ሴቶችን የፖለቲካ ዕውቅና በመስጠት እረግድ ሉላዊ አብዮት በአብነት እዬተካሄደ ነው ልብ ላለው ልበ ህሊና ብርሃን ላለው፤ እነዚህ አቅም እንዲያገኙ፤ እንዲራቡ፤ እንዲበራከቱ መትጋት ቀርቶ ደግመን ደጋግመን ከክፉ ነገሮች ጋር ልውስውስ አድርገን ግርዶሽ ሰርተን፤ ዝንቅንቅ አድርገን መልካምነትን የተፈጠረበትን ቀን እንዲረግም እናደርገዋለን። ግን ስለምን? የሰው መለያው እኮ ክፉ እና ደጉን የሚለይበት ህሊና ስላለው ነው። ያ ህሊናው እንኳንስ መልካም ነገሮች እያሉ ወደ መልካም ነገር የሚወስዱ ጥሩ ዜናዎች፤ ውጥኖች፤ ጅምሮች፤ ፈሎች፤ ቀንበጥ ሃሳቦች እንኳን ሲኖሩ እነዛ ሃይል ብርታት አግኝተው የመልካም ነገሮች ቤተኛ