ልጥፎች

ከታሪክ ማህደር፤ ኮርያ /ከጸሐፊ መስፍን ማሞ።/

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ከታሪክ ማህደር፤ ኮርያ “እግዚአብሄር አለኝ፣ --- አንተ ልጄ ነህ። እኔ ዛሬ ወለድሁህ። መዝመረ ዳዊት ፪ ምዕራፍ ፯ ጸሐፊ መስፍን ማሞ ተሰማ ሠላም ለናንተ ይሁን! መቼም የኢትዮጵያ ታሪክ እንደ ሳይንስ የሚያመራምር እንደ ድንቅና ውስብስብ ልቦለድ ታሪክ ውሉን ለማግኘት ታሪኩ የሚመስጥ በዚህች ምድር ላይ ሌላ መሰል ታሪክ ያለው ሀገር ይኖር ይሆን? በ1950ዎቹ (እአአ) ኢትዮጵያ የምትደዳደረው በዘውዳዊው (ሞናርኪ) ሥርዐት ኢኮኖሚያዊ መሰረቷም ፊውዳላዊ። ያም ሆኖ ከራሷ ጂኦግራፊያዊ ክልል አልፋ አህጉራዊና ዓለም ዓቀፋዊ ተቀባይነትና ግዝፈት ያላት ሀገር - ገራሚ ነው!!  ለማንኛውም ኮርያ እንዝመት፤  ዘመኑ ከ1950 እስከ 1953 (እአአ) ነው። የኮርያ ጦርነት። በኪም ኢል ሱንግ የምትመራዋ ሰሜን ኮርያ በሲንግማን ሪህ የምትመራዋን ደቡብ ኮርያ ወረረች። ሰሜኖች ኮሙኒስት ደቡቦች ካፒታሊስት ሥርዐት ተከታዮች። ከሰሜን ኮርያ ጎን ቻይና እና ሶቪየት ህብረት በግንባር ቀደምትነት ሲሰለፉ ከደቡብ ኮርያ ጎን ደግሞ አሜሪካና የምዕራብ ዲሞክራሲ ሀገራት ተሰለፉ። በዘውዳዊው የግርማዊነታቸው መንግሥት በፊውዳላዊ ኢኮኖሚ የምትደዳደረው ኢትዮጵያችን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ነበረች። እነሆ ከተመድ መሥራች ሀገሮች አንዷ ኢትዮጵያ ኮሙኒዝምን ልትዋጋ ከዲሞክራሲያዊ ሀገራት ጎን ተሰለፈች። በ1951 (እአአ) ቃኘው ሻለቃ ጦር ወደ ኮርያ ዘመተ። እነሆም በሩቅ ምሥራቁ ጉደኛ ጦርነት ተዓምረኛ ተዋጊዎች የተባሉት የቃኘው ሻለቃ ጦር የኢትዮጵያን የጀግኖች ማማነት በደማቅ የደም ቀለም በዓለም ዐውደ ውጊያ አስፃፈ። ቃኘው ሻለቃ ጦር በዚያ የጦር ዐውድ በተለያዩ የጦር ግንባሮች

ዘመን ያላዳነው ቅምባ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  „በክፉዎች ምክር ያልሄደ በዋዘኞች ወንበር ያልተቀመጠ፤ እሱ የተመሰገነ ነው።“ መዝሙር ፩ ቁጥር ፩ ዘመን ያላዳነው ቅምባ። ከሥርጉተ © ሥላሴ Sergute © Selassie 16.02.2019 ውዶቼ እንዴት አላችሁልኝ። ደህና ባጃችሁ? እንዴት ናችሁልኝ አዱኛዎቼ። እኔ ልዑሌ ፈጣሪዬ ክብሩ ይስፋ በሙሉ ጤንነት ላይ እገኛለሁኝ። ደህንነተኔ የጠያቃችሁ ክብሮቼ ደህና ነኝ። ግን ድንብልብሏ ከቶ እንዴት ሰነበተች? አላዛሯ ኢትዮጵያስ? መቼም ብዙ ነገር በዚህ 15 ቀን እንደ ተከወነ እና አንደገጠመ አስባለሁኝ። መንፈሴ ከአገሬም ሆነ ከግራጫዋ ፕላኔታችን ጋር ቢሆንም ጥሞና ጊዜ ላይ ስለነበርኩኝ በተዘጋ ገሃዳዊ ዓለም ግን ቧ እና ፏ ባለ መንፈሳዊ የፀጋ ትፍስህት አብሮነት አድርጌ ቆዬሁኝ። ተመሰገን። ዛሬ እጅግ ማልጄ ነበር የተነሳሁት። እትዬ ንግሥትም ፍንትው ብላለች። ብቻ እህታችሁ ትንሽ ዞር ዞር እንያልኩኝ ትንሽ ነገር ለማዬት ለማድመጥም ሞከርኩኝ። ያው የሳተናው ነገር ነፍሴ ነው።  ከቶ እናት እንዴት ሰንብቶ ይሆን ብዬ መጀመሪያ በፍጥነት ከፍቼ ያዬሁት የጥንት የጥዋቱን ቤቴን የሳተናውን ነበር። ደህና ነው። ያለፈኝ እንዳለፈኝ ሆኖ አዳዲስ ጹሑፎችን አነበብኩኝ። እሱን ሳተናውን ደህና በማግኘቴ በውነቱ ደስ ብሎኛል። አማካይ ስለሆነ። ትንፋሽም። ይኑርልን። ልፋቱን የሚመዝን አምላክም ልጆች ካሉት ይበርክለት ይቀደስለት፤ ትዳርም ከኖረው በረከቱን ሁሉ በስፋት ይለግስለት። እማከብረው ድህረ ገጽ ነው። እውነት ምን ብትምር ይሆን ዘመን ከዘመን እንዲህ ሊያልፍላት ያልቻለ የሚል ፈታኝ ነገር ግን በውነቱ ገጥሞኛል። እናላችሁ ዕውነት ምን አለ ተምር ብትሆን አልኩኝ። ተምር በልጅነቴ

ቢራቢሮ

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ቢ ራ ቢ ሮ ... *** „የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል እግዚአብሔር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።“ ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 03.02.2019 ከእመ ዝምታ ከሲዊዘርላንድ። ነይ እሰኪ ዘንድሮ አለፈልግም ከርሞ የለኝም አርምሞ               ሁለመናዬ አሮ               በበቀል ተነክሮ              ቀለም የለሽ ኑሮ፣               ቋሳ ተዘርሮ               መብቴ ተዘሮ                   ሁኛለሁ ደንቆሮ። አንቺ ቢራቢሮ ሕይወት ቢራቢሮ ኑሮ ቢራቢሮ ነፍሴ ቢራቢሮ     ተስፋ ቢራቢሮ አትሁኝ በረሮ አታፍቅሪ ጦሮ።                 ነጠብጣቤ አሮ               ዓይኔም ተማርሮ ቢራቢሮ ...    በበላህሰቦች እንዲህ ም ተወሮ               ከምሾ ተድሮ               ከዋይታ ተዳብሎ። አንቺ ቢራቢሮ ሕይወት ቢራቢሮ ኑሮ ቢራቢሮ ነፍሴ ቢራቢሮ          ተስፋ ቢራቢሮ አትሁኝ በረሮ አታፍቅሪ ጦሮ።               ገሳ ተንተርሶ               ሞረሽን ተንፍሶ                    በቀልን ተቋድሶ፣               ዛሬ ተቀልብሶ               እህህን ተለብሶ። አንቺ ቢራቢሮ ሕይወት ቢራቢሮ ኑሮ ቢራቢሮ ነፍሴ ቢራቢሮ ተስፋ ቢራቢሮ     አትሁኝ በረሮ አታፍቅሪ ጦሮ               ፍሬ ዘሬ ሁሉ ...               .... በምጣድ ታምሶ               አመድ ተነስንሶ             

ህግ በራስ ላይ እንዲህ ተፈጻሚ ሲሆን ተስፋ ማደሪያ ይኖረዋል።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ህግ በራስ ላይ እንዲህ  ተፈጻሚ ሲሆን ተስፋ ማደሪያ ይኖራዋል። „ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ ታማኝነትህ ብዙ ነው።“ ሰቆቃው ኤርምያስ ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፳፫ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 02.02.2019 ከእመ ዝምታ ከሲዊዝሻ።                                             „ለተባረከች አገር የተባረከ ትውልድ“    ·        መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=yIzEROYdwoE #EBC   ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ ዝናሽ ታያቸው እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የጉዲፈቻ ልጃቸውን ህጋዊ አደረጉ፡፡ „ለተባረከች አገር የተባረከ ትውልድ“ ዓላማው አድርጎ የተነሳው እሸቱ መንፈስ እንሆ እንደ ማንኛውም ዜጋ በፍርድ ቤት ተገኝተው ቀዳማዊት እመቤት ወ/ሮ ዝናሽ ታያቸው እና ጠ/ሚር አብይ አህመድ ከ5 ወራት በፊት በጉድፊቻ የተረከቡትን ልጃቸውን በህጋዊ ውሳኔ መቀበላቸው ኢቢሲ ዘግቧል።  ህግን እንዲህ በሁሉ ዘንድ እኩል ተፈጻሚ ሲሆኑበት ተስፋ ማደሪያ ይኖረዋል። ተስፋም መብቀያ ይኖረዋል። ተስፋም ጥግ ይኖረዋል። ተስፋም ትውልድ ይሆናል። የትውልድ የመንፈስ ብክነትም በዚህ መልክ መልክ ቅጥ ለማስያዝ ተግባሩ ትራስ ይሆነዋል። ትውልድም ከሚሰማው ይልቅ የሚያየውን ስለሚያምነው በሚያምነው ልክ ትውልዳዊ ድርሻውን ለማሳከት ወይንም ለመወጣት ቁርጠኛ ይሆናል። ይህ ከህግ አንጻር ብቻ ሳይሆን ከሰባዕዊነት አንጻርም በመንፈስ አትራፊ መንገድ ነው። ከሰባዕዊነት አንጻር ብቻ ሳይሆን ከእኛዊነት አንጻርም ተቋማዊነቱ ዝልቅ ነው። ችግርን የእኔ ማለት። አይዟችሁ የማለት። አለንላችሁ የማለ

ሁሉም ነገር ያስፈልጋል ሁሉም ነገር ጠቃሚ ነው ከሁሉ ግን የሉዑላዊነት ከብርን ማስጠበቅ የበለጠ ነው።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ጠ ጣ ር ። „ ኖን። መንገዳችን እንመርምር እና እንፈትን። ወደ እግዚአብሔርም እንመለስ።“ ሰቆቃው ኤርምያስ ፫ ቁጥር ፵ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie  01.02.2019 ከእመ ዝምታ ኪሲዊዝሻ። ·        ጠብታ። ውዶቼ እንዴት ናችሁ። ዛሬ ቪንቲ ከፋፍቷታል። እንዲህ ከፍቷት እኔ ደግሞ ጫና ብጨምርባት ሆድ ይብሳታል ብዬላችሁ መውጣቱንም ተውኩት እንጂ ዛሬ የዓመቱ ቅዳሜ ብዙ ነገር ታልሞለት ነበር። የውርጩ ገጹ ጭጎጎት አስመስሎ ይታመሳል።  ጠብታውም መጣሁ ሄድኩ እያለ እሱን እራሱን በተፈጥሮው ውስጥ ሆኖ ይነሳስተዋል። ፊታውራሪ ጉምም አይቅርብኝ ብሎ አብሬ ልታደም ብሎ ዕለቱን የሙጥኝ ብሏል። ሻሾ ግን ብቅ አላለም ትናንት መክሰስ ዛሬ ቁርስ አልሰጡትም መሰል። እና ሥርጉቱሻ በሶስት በአራት ለመሰለቅ ስለምን ትታደም እትዬ ዛሬን? ካሊሟን ደራርባ ጉብ ብላ እስቲ ብራና ሆይ! ይትናንቱን ልቀጥልህ ብላ ኮቢ ፍለጋ ስትማስን ሳይጠሩሽ አቤት በራሷ ጊዜ ከች። ·         መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=miHgNJKM4mY Ethiopia : [ አዋረዳት ] ጠ / ሚ አብይ ይህቺን ሃገር እንደ አዜብ መስፍን የበዘበዘ እና የሰረቀ ሰው የለም የቀለጠች ሌባ ናት ·        የፍሬ ነገር የሆድ ዕቃ። „በመጀመሪያ የተከበረው ምክር ቤት እንዲገነዘበው የምፈልገው ኢትዮጵየ ውስጥ ወንጀል ሰርቶ ወንጀል በመሠራቱ በመንግሥት ዲክለር ተደርጎ ያልታሰረ ሰው የለም። ልዩነቱ መንግሥት ባዘጋጀው እስር ቤት ውስጥ መንግሥት እዬጠበቀው፤ መንግስት እዬቀለበው መታሰር እና እራሱን ማሰር ካልሆነ በስተቀር አልታሰ