ልጥፎች

ሰማዕት የእኔ ሰው ገብሬ።

ምስል
የመሆን የእኛ ሰው በመሆን! ከሥርጉተ -  ሥላሴ 12.04.2018 (ከጭምቷ - ሲዊዘርላንድ - ዙሪክ።)                                    „ነፍሴ በኋዋላህ ተከታተለች፤ እኔንም  ቀኝህ  ተቀበለችኝ።"                                        (መዝሙር ፷፪ ቁጥር ፰) እንደ መቅድም። ይሄ ጹሑፍ እንደምታዩት በ12.04.2108 የተፃፈ ነው። ይህ ሰማዕት በውስጤ ያለ ነው። ስለ ጀግናው ረ/ አውሮፕላን አብራሪ በጻፍኩበት ወቅት አብሬ የኔ ሰው ግብሬ እና የሰማዕት የሽብሬን ደስአለኝን ሠራሁት። በዛን ሳምንት ደግሞ ቅኑ ሳተናው ድህረ ገጽ አብዝቼበት ነበር። ከ እኔ ጋር መሥራት ከባዱ ነገር እኔም አይደክመኝ ሰውንም ይደክመዋል ብዬ አላስብም። ስለሆነም በተከታታይ ቀናት ላይ የእኔ ከ4 በላይ ጹሑፍ ብራናው ላይ ሲለጠፍ ለህሊና ዳኝነትም ከባድ ነው። ይገባልም። ተግ በይ በማለት ልጓም ማበጀት። ለእኔም ለጤናዬ የተገባ ነው። ተቆጣጣሪ ከሌለኝ በጣም ነው ሥራ እማበዛው።    በዛ ላይ የእኔን ጹሑፍ ማተምም በፈተና ውስጥ ያለ ቀራኖዮ ነው። ጽናቱ እራሱ ይገርመኛል የሳተናው። የሆነ ሆኖ ጹሁፍ አብዝቼ በላኩበት ወቅት ተልኮ ዕጣ ያልወጣለት ስለነበር ዛሬ በእኔው ብሎግ ላይ መለጠፍ አሰብኩኝ። የሰማዕቷ ሺ ብሬም ይቀጥላል። ቢያንስ ለዛሬ ቀን ያደረሱ የትናንት ጀግኖችን፤ ሰማዕታት፤ ቅዱሳንን ማሰብ የተገባ ስለሆነ።  መንፈሳቸው ይወቅሰናል። ውስጣችነንም በእሳት ነበልባልም ይገርፈዋል። ይቀጣዋል። ቀን እዬወጣ ስለሆነ በዚህ ቀን መውጫ ላይ ሰማዕታቱን ማሰብ የህሊና ጉዳይ ነው። ያን ጊዜ እንደ ዛሬው ሃላፊነት የሚሰማው መንግሥት ስላልነበረን ደመ ከልብ ሆኖ የቀረ ሰማዕት ነው

አለማፈር እስቲ ይጠራ ...

ምስል
   ወይ አለማፈር …                              ከሥርጉተ  ©  ሥላሴ 25.08.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።)                            „መንገዳችን እንመርምርና እንፈትን፣ ወደ እግዚአብሄርም እንመለስ።“                                            (ሰቆቃው ኤርምያስ ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፵) ·          ኢትዮጵያ ወግ ደረሳት። ኢትዮጵያ ወጉ ደርሷት የሰማዕታት ቤተሰቦችን ደውሎ የሚያጽናና መሪ ፈጠራለት። ተመስገን! የተጎዱትን ደግሞ በአካል ሄዶ የሚያይ በማጽናኛ መንፈሱ ድብስብስ የሚያደርግ ብሩክ ቅዱስ የሆነ የአሮን በትር ተሰጣት። ተመስገን! ተጎጂዎችን ለመርዳትም በመንግሥት ደረጃ እርዳታ የሚያሰባሰብ በብሄራዊ ድርጅት እስከ መፍጠር ደረሰች አላዛሯ ኢትዮጵያ። ይገርማል። በተጨማሪም አንድ ጠ/ ሚር ደም ለወገኖቹ የሚለግሥ ኢትዮጵያ ፈጠረላት። አሁንም ተመስገን። የሊቢያ ሰማዕታት ብትን የአፈር እና ዕንባ አልተፈቀደላቸውም ነበር።  ለዚህ ሰውኛ ቀን ነበር ሌት ተቀን ተግተን እኔ በብዕሬ ሳተናውም ደከመኝ ሳይል በብራናው የተጋነው። ተመስገን ቃሉ አነሰብኝ። ምን ልበለው? እንደ ገና ተፈጠርኩኝ ልበል ይሆን። ዕድሜዬም ከመጋቢት 24 ቀን ጀምሮ ይሁንልኝ ብያለሁኝ። አዎና! በእኔ ዕድሜ እንዲህ ዓይነት ህልም የሚመስል በትረ ፍቅር … መሪ ማዬት ስለታዕምር ነው። ፍቅር እንዲህ አገር ምድሩ የእኔ ሲለው … ገድል። የጸሐይ ዘመን። ·          የሙርቅርቁ ብዛት የውልቅልቅ ጥገት። አሁን ወደ በኽረ ጉዳዬ ኮተት ልበል፤ እንደ እነ እንቶኔ … በስንት ግራሞት ስንት ድብልቅልቅ መሬት ትሸከም ይሆን? በስንት ዝብርቅርቅ ምድር እሾኾችን ተሸከሚ ተብሎ ይፈረድባት ይሆን?

"አሜን!"

ምስል
       አሜኑ!                „ፍቅርህ ከወይን ጠጅ ይልቅ መልካም ነውና። ዘይትህ መልካም ማዕዛ አለው፤                          ሥምህ እንደሚፈስ ዘይት ነው፤ ስለዚህ ደናግል ወደዱህ።“                        (መኃልዬ መኃልዬ ዘሰሎመን ምዕራፍ ፩ ቁጥር ከ፩ እስከ ፫) ሕይወት ነፍሷን ጠርታ፤ ተጣርታ መንፈሷን ንብ በዓውራው ሆኖ አስከፈተ በሩን። ውለላ ከማሩ ጥንግ ድርብ ለግሶ ተስፋ እዬዘመረ በጃኖ ቆምሶ እርገቱ ወረደ ማዕረጉን ተላብሶ። ማግሥት ተስልፎ አቋቋሙ አምሮ ነፍስ አባት ሆነለት ሥርዬትን አዳምሮ። ዝ ግ ባለው መንበር የውቅያኖስ እርገት ዝ ቅ ብለው ሲበሩ በዝማሬ እዕዋፋት ትውፊት ትሩፋቱ ዳርእስከዳር ስምረት። ጥጆች ሲቧርቁ በግርግሙ ብሥራት ሽምጥ ሲጋልቡ ታማኞች በአኃቲት በድብባ ስትመርቅ ወላድ የወግ ደርሷት ዛሬን ተነ ገ ላይ የሉላዊ ቅምረት። ዝልቅቱ በፍጥነት ርምጃን ጨምሮ ምጥቀት በብልሃት በጥበብ ተቃኝቶ „ መደመር “ አበራ ራዕይን አጉልቶ! „ ቃል “ ቀን ለገሰው በቅኔ ዘቃና ጉባኤ ውልደቱ ተሟልቶ ሁለንትና - ዛጉኤ፤ እቅፍቅፍ በሐመር፤ ጥላቻ በሰኔል ፍቅርም በሞገሱ፤ ክስመት  ➳ ለሳጥናኤል። ርትህ ባባንዱ ሚዛን በህሊና በህብርነት ፈክቶ የሰንደቅ ደመራ ቀደምቱ በዕድምታ የአብይ ጎመራ! አይዞህ! የእናቴ ልጅ ደም መላሽ ታናሼ፤ አይዞህ! የእምዬ ልጅ የቁርጥ ቀን ዋሴ፤ የድንቅነሽ ጠሐይ የእውነት እጬጌ። ቀን ከሌት ስትባትል ከነባቢትህ ጋር ቀን ከሌትም ስትሮጥ ከውስጥህ ዘብአደር እማማን አፍሪካን በሰላም ልትቀምር። ከቶ ማን

የደም ስንቁ።

ምስል
የደም ስንቁ። ከሥርጉተ© ሥላሴ 24.06.2018 ( ተማንጠግቦሽ ሲዊዝ) "የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ።"           (መክብብብ ምዕራፍ ፲፪ ቁጥር ፩) የሰው ስጋ ስንቁ፤ የሰው ደም አጥንቱ የሰው ደም ንጋቱ፤ የሰው ደም ርስቱ የሰው ደም ጥሪቱ፤ የሰው ደም ሐሤቱ። የሰው ደም ኩራቱ፤ የሰው ደም ልክፍቱ የሰው ደም አለቅቱ፤ የሰው ደም ጥረቱ የሰው ደም ጉሮሮው፤ የገዳይ ክርፋቱ። ዋ! አዲስ አባባ የአንቺ ቀን ውለቱ ጸሐይሽ ደመና በሲዖል ሽንፈቱ ሲኦሎች፤ በጋራ በስፋት በፍቅር ሸፈቱ። ሰው ለማለት ሆኖ እንዲህ፤ በአውሬነት ተስልቶ መኖር ባባዶኖት ዳምኖ ታጣፈቶ ለደም ጠማኝ ጥሪት ፍቅር ተሰውቶ። ተጣፈ በአሁኒት ደቂቃ 17.35 ሥጦታ ለደም ጥማት ርስተኞች ለእነ ማህበረ ደራጎን። የኔዎቹ ግጥም ካሰኛችሁ … እነሆ https://www.youtube.com/watch?v=3XasnG3Ena8&t=3397s ናፍቀሽኝ አገሬ። https://www.youtube.com/watch?v=76IFoT-5yrg&t=1583s አፈሬ ነው መስመሬ (23 06 2018) ኑሩልኝ እነ እማ // አባ ቅንዬ። መሸቢያ ጊዜ።  

ዳገቶ!

ምስል
ዳገቶ ከሥርጉተ© ሥላሴ 24.06.2018 ( ተአትጠገብ ሲዊዝ) ወዴት ታሰማራለህ? በቀትርስ ጊዜ ወዴት ትመስጋለህ። (መሃልዬ ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፯) በስርንቅ ታክሎ በስርንቅ ተባዝቶ በስርንቅ ተካፍሎ እሱ በእሱ ሆኖ ሾተል አግርሽቶ በጥርኝ ቀላልዶ ጉራማይሎ ዘፍኖ ዥንጉርጉር ተጎምዶ በቁርሾ ጎርንቶ አንክርዳድ ተድሮ ወስከንቢያን ሰንጎ በዛር ኩፍኝ አውሬ ተማት ተደብቶ የደም ጥርኛ ናፍቆት ሲነስት ጎልብቶ ዘመን በቃህ በለው ጉልቱን ዳገቶ! ተጣፊ በዚችው ደቂቃ 17.15 የኔዎቹ ግጥም ካሰኛችሁ … እነሆ https://www.youtube.com/watch?v=3XasnG3Ena8&t=3397s ናፍቀሽኝ አገሬ። https://www.youtube.com/watch?v=76IFoT-5yrg&t=1583s አፈሬ ነው መስመሬ (23 06 2018) ኑሩልኝ እነ እማ // አባ ቅንዬ። መሸቢያ ጊዜ።