ልጥፎች
ለመሆኑ የአማራ ህዝብ እንደ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ይታያልን? ትክክለኛ የፖለቲካ ዕውቅና እና ውክልናስ አለውን? ወላጅ አልባ ህፃናትንስ ሞግዚት ቀጥራችሁ ይሆን ወደ ወላጋዊ ሞት የምትሸኟቸውን??? ፍፁም ጨካኞች! ፍፁምም አረመኔወች ናችሁ።
- አገናኝ አግኝ
- ፌስቡክ
- ቲዊተር
- ኢሜይል
- ሌሎች መተግበሪያዎች
ለመሆኑ የአማራ ህዝብ እንደ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ይታያልን? ትክክለኛ የፖለቲካ ዕውቅና እና ውክልናስ አለውን? ወላጅ አልባ ህፃናትንስ ሞግዚት ቀጥራችሁ ይሆን ወደ ወላጋዊ ሞት የምትሸኟቸውን??? ፍፁም ጨካኞች! ፍፁምም አረመኔወች ናችሁ። "ከንቱ የከንቱ ከንቱ፤ ሁሉም ነገር ከንቱ።" ትናንት ከEMS ጋር አቶ አረጋ ከበደ ያደረጉትን ቃለ ምልልስ አዳመጥኩት። ለቃለ ምልልሱ ፈቅደው መቅረባቸው መልካም ነው። ነገር ግን ለቀረበላቸው ለስለስ ያለ ጥያቄ የሰጡት ምላሽ በሲዊዝ ወይ በሲዊድን እንደሚኖር የአንድ አካል ተጠሪ ሆነው ነው የቀረቡት። ቤታቸው በበላያቸው እዬፈረሰ ለሳቸው ያሉበት ዶፍ አልታያቸው። የጦር ኃይሎች በሚመራው ክልል ሆነው፤ ከከተማ ከተማ በኢሊፍተር እና በብዙ አጃቢ በነፍስ ውጪ እና ግቢ ላይ እያሉ እሳቸው ልማት ጉብኝት ላይ ስለመሆናቸው ተርከዋል። የአማራ ህዝብ የማንነት እና የህልውና ተጋድሎ ፖለቲካዊ ዕድምታም አልገባቸውም። ስለሆነም በጭፍጫፊ ሳቢያወች ላይ ብቻ አተኩረው መልስ ለመስጠት ሞክረዋል። ጥያቄው እራሱ ሞጋች አልነበረም። ለዛም የበቃ ምላሽ ለመስጠት አልቻሉም። ለምሳሌ ወደ አዲስ አበባ አትገቡም የሚለው መከራ ዛሬ የለም፤ ስለቀደመው ተጠያቂ አይደለሁም ባይ ናቸው። የኦነግ ፖለቲካ ስትራቴጅ እና ታክቲክ ፈጽሞ አልገባቸውም ወይንም ለፖለቲካ ሴራው ሊጋባው ናቸው ማለት ነው። በአማራ ክልል ላይ ስለሚዘንበው የድሮን ጭፍጨፋም እኔ ማርስ ላይ ስለነበርኩ ልጠዬቅ አይገባም የሚል ዕድምታ ያለው ፍፁም የሆነ የጭካኔ ምላሽ ሰጥተዋል። ዬሚመሩትን ህዝብ መከራ እንዳላዩ፤ እንዳልሰሙ አልፈውታል። የጊዜ ጉዳይ እንጂ እሳቸውም ነገ ተረኛ መሆናቸውን ልብ አላሉትም። ደራጎንም ደራጎን፤ መቃብርም መቃብር፤ ሲኦልም ሲኦል ነውና በተራቸው የድርሻቸው
EMS "...በቤታችሁ ይድረስ!" አሰቃቂው የኢሰመጉ ሪፖርት Wed 27 Dec 2023
- አገናኝ አግኝ
- ፌስቡክ
- ቲዊተር
- ኢሜይል
- ሌሎች መተግበሪያዎች
ይድረስ ለኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን። ኢትዮጵያ - አዲስ አበባ።
- አገናኝ አግኝ
- ፌስቡክ
- ቲዊተር
- ኢሜይል
- ሌሎች መተግበሪያዎች
ይድረስ ለኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን። ኢትዮጵያ - አዲስ አበባ። "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል ሰው ግን አያስተውለውም" የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ለማን እና ስለማን ይሆን የተቋቋመው??? #ስለአለቅትነት ይሆን??? አነሳችሁብኝ። እንደምን ሙሁራን ለሚያቀርቡትገንቢዕይታ ዕውቅና መስጠት ተሳናችሁ???? #ቁስለት ! የተከበሩ ፕሮፌሰር ሚንጋ ነጋሽ ከአደባባይ ሚዲያ ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልልስ በጥሞና ለአራት ጊዜ ያህል አዳመጥኩት። አምስተኛውም ለአዲሱ ዓመት ተቀጥሯል። አይጠገብም። ተቋም ነው። የአወያዩ የአቶ አቤል ጋሹ የአጠያዬቅ ዘዬም ለፕሮፌሰር ሚንጋ ሜጋ አቅም ደረጃውን የጠበቀ ሆኖ አግኝቼዋለሁኝ። በዚህ ዓመት በመቆጠብካዳመጥኳቸው ቃለ ምልልሶች ቀንዲሉ ሆኖልኛል ለእኔ። የኢትዮጵያን ክብረት እና አዱኛም ፏ ብሎ ያዬሁበት አጋጣሚ ነበር ማለት እችላለሁኝ። መስጦኛል። ተደምሜበታለሁኝ። ውስጤንም አግኝቸበታለሁኝ። ፕሮፖጋንዲስት ለማያስፈልገን ኢትዮጵያዊ ዜጎች ልካችን አግኝተናል ብዬ አስባለሁኝ። ለዚህም ነው እኔ ኢትዮጵያን በተፈጥሯዋ ልክ ያነበቡ፤ የተረጎሙ እና ያመሳጠሩ ከሳይለንት ማጆሪቲ ውስጥ ያሉ በቲም ፈላስፊቷን አገሬን ይመሩ ዘንድ ዕድሉን እንዲያገኙ እምመኜውም። ፌስ ቡኬ ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ነው ሼር የማደርገው። ባሉኝ ሁሉ ሚዲያወቼም ብሎጌን ጨምሮ ሼር አድርጌዋለሁኝ። ከማህበራዊ ሚዲያ ርቀው ለሚኖሩ ወገኖቼም ሼር አድርጌዋለሁኝ። የጠራ አቅጣጫ ያለው ብቻ ሳይሆን አብዝቶ ቅንነትን ማዕረጉ ያደረገ መሰጠትን ስለአገኜሁበት። የጨመተ እና የሰከነ፤ እላፊ ያልሄደ ጠፈፍ ያለ የእኛነት የኔታነትን አይቸበታለሁኝ። መስታውትም ራዲዮሎጂም ማለት እችላለሁኝ። በፍፁም ሁኔታ የገረመኝ ደግሞ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ህይወቴ ከልጅነት እስ
ለምን ሥማችሁን #አብይ አትሉትም? ጓዘ ቀላል ጥያቄ ለፋና፤ ለዋልታ፤ ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እና ራዲዮ፤ #ለኦሚኮ።
- አገናኝ አግኝ
- ፌስቡክ
- ቲዊተር
- ኢሜይል
- ሌሎች መተግበሪያዎች
ለምን ሥማችሁን #አብይ አትሉትም? ጓዘ ቀላል ጥያቄ ለፋና፤ ለዋልታ፤ ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እና ራዲዮ፤ #ለኦሚኮ ። ኢትዮጵያ አዲስ አበባ። "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል ሰው ግን አያስተውለውም።" እንዴት ናችሁ ማህበረሚዲያወች። የማንእንበላችሁ? የማንስ ትሰኛላችሁ? መቼ ይሆን ለገባችሁት ሙያዊ ቃል ሟች ሆናችሁ የምትገኙት? ዘወትር አንጋችነት አይሰለቻችሁም? ግን ስለምንሥማችሁን አብይ አትሉትም።መሃያ ቆርጠው የሚያስተዳድሧችሁ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ ናቸውን? በቃ የሳቸው ውሎ አዳር ዘጋቢ ብቻ ሁናችሁ ቀራችሁ እኮ? ግን የቀራችሁንስ መቼ ታስደምጡን ይሆን? የሌሊቱን አዳርንም፤ የጠሎት ሥርዓቱን ሁለመናውን ልጠቅሰው የማልሻውን ሁሉ? እሳቸውም እኮ እንደ እናንተ ኢትዮጵያ ቀጥራ የምታስተዳድራቸው አገልጋይ እንጂ አሰሪያችሁ አይደሉም። ይህንያክልግልምት ብሎን እስኪያቅለሸልሸንድረስ ዝክረ እሳቸው ብቻ? ሥራጠፋን? የሚገርመኝስለ ራሺያ እና ዩክሬን፤ ስለ ፍልስጤም እና እስራኤልሐተታ አላችሁ። አንዳንድጊዜ ፋና፤ ዋልታ፤ ኢቲቢ፤ ጁቢተር ላይ ያላችሁ ይመስለኛል። በቃ የመጠቃችሁ። የደም አላባ፤ የዕንባ ጎርፍ፤ የድሮንሥልጣኔ በህዝብ፤ በቅርስ፤ በውርስ፤ በሃይማኖት፤ በትውልድ ላይቀንከሌት በጭካኔ እዬዘነበእናንተ የጠቅላይ ሚር አብይአህመድን ፋንታዚስታቆላምጡ፤ ስታሽሞነሙ ግንመሬት ላይ ስለመኖራችሁ ይረዳኛል። ለእኔ በኢትዮጵያ መከራ ላይ እያላገጠ፤ እዬተጫወተ ያለው እናአረመኔነት እንዲንሰራፋ፤ ትውልድ በባዕቱ፤ ትውልድ በሁለመናው ይነቀል ዘንድ እዬሠራችሁ ያላችሁ ሚሳኤሎች እናንተው ናችሁ። የጥፋት መልዕክተኝነትን ስለምን እንደምንትከባከቡ ይጨንቃል። ይጠባል። የኢትዮጵያ አምላክም ሩቅ ይመስላችኋል። የኢትዮጵያአምላክም የማይፈርድይመስላችቿል።
ፅናት ማሸነፍ ነው።
- አገናኝ አግኝ
- ፌስቡክ
- ቲዊተር
- ኢሜይል
- ሌሎች መተግበሪያዎች
ያጣኽውን በማጣትህ ከፀፀተህ በገደልከው በደል ውስ ለመኖር አትፍቀድለት። አገርን ፈጣሪ ከመረቃት አይዞሽ ባይ እረኛ ይሰጣታል። ይህ ካልሆነ አገር የህዳር ዝናብ እርግማን እንደታዘዘባት ትረዳለህ። ሰብል አልባ ትውልድም አደራም እራፊ መጠጊያ ዬልብ ዓይን የላቸውም እና። የክፋት ሽርሽር በደግነት ላይ ማፈናቀልን ለመተግበር ነው። ገዳዮች እርቃናቸውን ተወልደው፣ እርቃናቸውን ኖረው፣ እርቃናቸውን ከመሬት ጋር እርክክብ ይፈፅማሉ። ክትመት። ትዝታ ሲሄዱ ማደር ነው። ፅናት ማሸነፍ ነው። የህሊና ድንግልና የትውፊት ማህደር ነው። ማድመጥ ሥጦታ ነው። እራሱን የማድመጥ አቅም ያለው ሌላውን ለማድመጥ ዳጥ አይሆንበትም። አቅል ያለው ትውልድ የሚገነባውም ይህ መሰል ሰብዕና ያላቸው መሪዎች ሲኖሩት ብቻ ነው። መታደል ከበለፀገ፣ ምርቃትም ከተበራከተ የተስፋ አዝመራ ይኖራል። ትውልዱን የምናባክነው እኛ ነን። ከትናንት የተሻለ ሥርዓት መፍጠር ስላልተቻለን። ለምን? በውዳሴ ሥካር አቅም ስለሚባክን። ትውልዱ ይረገማል። ረጋሚዎቹ ዘመኑን አባካኞች ናቸው። የእነሱን ዘመን አክስለው፣ የዛሬውን ቀምተው፣ የነገን ማሳረር የተፈጠሩበት ነው። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 17.12.2019
ክፋዎች ሳይኖሩ የኖሩ ይመስላቸዋል። መኖራቸውን ቀምተው የሚኖሩት ኑሮ ሙጃ መሆኑን አያስተውሉትም እና።
- አገናኝ አግኝ
- ፌስቡክ
- ቲዊተር
- ኢሜይል
- ሌሎች መተግበሪያዎች