ልጥፎች

ሆዴን ባር ባር ቢለውም። ይህን ፍፅምና ትህትና ነው እያሰደደው ያለው የቤተ - መንግሥቱ ደራጎን።

ምስል
ሆዴን ባር ባር ቢለውም። ይህን ፍፅምና ትህትና ነው እያሰደደው ያለው የቤተ - መንግሥቱ ደራጎን። "የቤትህ ቅናት በላኝ።" #ለምን ስለምን ሆዴን ባር ባር አለው? ብፁዓንን ሳይ፣ ይህን አውሬ ሥርዓት ሳስብ፣ ቅንጣት ስለማላምነው እንደ ሌላው ሁለመናችን እንዳያራግፈን እሰጋለሁኝ። እንዳያሳጣን እሰጋለሁ። እንደዚህ ዘመን ብፁዓን አቨው በሥጋ በብዛት የተለዩበት ጊዜ የለም። በአራት ዓመት ውስጥ ብዙ ነገር አጥተናል። አውሬ ዘመን ነውና። ስልቱን አናውቀውም። ይፈፀማል ዕንባችን አፍሰን ዝም እንላለን። ለማስተዋል፣ ለጥሞና ጊዜ ወስደን አናውቅም። እንጂ ለተዋህዶ ምፃዕት ዘመን ላይ ነን። አጥንተውናል። በአጠኑን ልክ በስውር እያጠቁን ነው። ዛሬ እምናዬው መልካም ነገር የነገ #ሃዘን እንዳይሆን እሰጋለሁኝ። ምነው በቀረብን እንዳንል። ብፁዑ አባታችን አቡነ አብርኃም አጽናኛችን፣ ጥጋችን፣ በከፋን ሰዓት ከጎናችን የማይለዩትን ሳይ ሆድ ይብሰኛል። ለሳቸውም ለእኛም የመኖር ዋስትና ባህርዳር ምርጫዬ ነበር። ይህን ሥርዓት አናውቀውም። ከአጠቃን በኋላ ነው የሚገባን። ስንቀደም እንጂ #ቀድመነው አናውቅም። እና መጪው ጊዜን ፈራሁት። ብፁዑ አባታችን አቡነ ጴጥሮስ (ዶር) እሳቸውም ቢሆኑ በፈተና የፀደዩ፣ ርትፁ ናቸው። ልስሉስ። የእኛ፣ የውስጥ ናቸው። ቅርባችን ናቸው። የእሳቸውም ህይወት ያሳስበኛል። ይህን ሥርዓት አምኖ #ልብ #መጣል አይገባም ባይ ነኝ። ከፈጣሪ በታች። ይህ ድንቅ ሥራ የፈጣሪ ቢሆንም ዲያቢሎስ የሰፈነበት የቤተ - መንግሥቱ ዓውድን ግን አላምነውም። እርቅ እና ውጤቱ እኛ በቅንነት ብናዬውም የሆነው ነገር ዘለግ ብሎ ታስቦበት፣ ለአንድ ትርፍ ወዘተረፈ ኪሳራ ተደራጅቶ አይቻለሁኝ። እናም እንደ ተዋህዶ ልጅነቴ ውስጤ በስክነት፣ በአትኩሮት ከመከታተል ው

#በራስ መተማመን ሚዛኑን ሲስት እና ጠኔው።

#በራስ መተማመን ሚዛኑን ሲስት እና ጠኔው። ዕለተ ሃሙስ ሰጋሪው በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ። "ዝም ብዬ የመከራን ቀን እጠብቃለሁ።" (ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፲፯) #ጠብታ ። በራስ መተማመን የሰብ ተክለ ሰውነት የግንባታ ሂደት ቀዳማይ ጉዳይ ነው። በራስ መተማመን ምንጩ ነፃነት ነው ብዬ አምናለሁ። ነፃነት የአገር፣ የሙያ፣ የቤተሰብ ወዘተ ሊሆን ይችላል። ግን አያያዝም፣ አፈፃፀምም፣ አስተዳደርም ይጠይቃል። #ዕፍታ ። አንድ ልጅ ከእናቱ ማህፀን ሲወጣ ራቁቱን ነው። እርግጥ ነው ለዬት ብለው የሚወለዱ ልጆች አሉ። ተክሊል ለብሰው ተወለዱ የሚባሉ። ተክሊሉ እንደ ሞራ ነገር ነው ይህ በጎንደር ይትበኃል የተለዬ አክብሮት አለው። ያ ሲቀደድ ያው ባዶ ገላ ነው። ልጆች ሲወለዱ አካላቸውን ብቻ ይዘው ነው የሚወለዱት። የሰብዕና ግንባታው መነሻ ሆነ መድረሻው ከተዉለዱ በኋላ ነው የሚታነፀው፣ ውኃ ልኩም የሚጀመረው እንደ ማለት። እያንዳንዱ ወላጅ ባሊህ ሊለው የሚገባ ቁምነገር ቢኖር እያንዳንዱ ልጅ ሲወለድ #መክሊትም #መልዕክትም ይዞ መወለዱን ነው። #አሳዳጊነት ። ……… ይህን በቅጡ ዕውቅና ሰጥተው ገርተው ያሳደጉ ወላጆች ወላጅ ሊባሉ ይገባቸዋል ብዬ አስባለሁ። ወላጅ ስል የወለደ ብቻ ሳይሆን ያሳደግም። በኢትዮጵያ ይትበኃል ጎረቤትም የወላጅ ያህል ነው፣ የማር ልጅነት፣ የክርስትና ልጅነት አብሮ የሚሄድ ሲሆን የትዳር አጋር ልጅም እንዲሁ። "እንጀራ እናት እንጀራ አባት" የሚለውን አልወደውም። ደወሉ አሉታዊ ነውና። #ተመክሮዬ ። ተፈቅዶም የሚሰጥ ልጅ አለ። እኔ እጅግ የምወዳቸው፣ የምሳሳላቸው ሁለት ጓደኞች ነበሩኝ ኦሮሞወች ናቸው። ሁለቱም የአንድ እናት አባት ልጆች

የአማራ ፖለቲካ ቅንነት ማንፌስቶው ሊሆን ይገባል። ቅንነት አሻራው ነውና።

የአማራ ፖለቲካ ቅንነት ማንፌስቶው ሊሆን ይገባል። ቅንነት አሻራው ነውና። አንድ ተመስገን የምለው ጉዳይ አለኝ። በዘመነ 60ዎቹ የአማራ ፖለቲካ እንኳንም አልተጀመረ። መርዝ ይሆን ነበር። እናት አገሩን ኢትዮጵያን ከውስጡ የሚያወጣ ሳጥናኤላዊ መንፈስ ይውጠው ነበር። ተፈጥሯዊ እና ሰዋዊ መሆን ይሳነው ነበር። የሸር ባንድ ይኖረው ነበር። የሴራ ኦርኬስተር ይኖረው ነበር። የኢጎ ቁልል ይንጠው ነበር። መገዳደል መርኹ ይሆን ነበር። ስለዚህም እግዚአብሄር አምላክ ተማልዶት በ21 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነጥሮ ወጣ። ይህ ማለት ሰዋዊ እና ተፈጥሯዊ መንፈሱን ያጎላለታል። እኔ እንደ ሥርጉተ በህወሃት ተፈጥሮ እና ሰው ገዳይ ማንፌስቶ የተቀረፀው የተጋሩ ትውልድ ያሳዝነኛል። በኦነጉ የጭካኔ አውራ በማህበረ ሌንጮ የተፈጠረው የቁቤ ትውልድም ያሳዝነኛል። የሚገርመው፣ ግዙ፣ ንዱ ተብለው አሁንም ሰው አጥፊ ትል አስተሳሰብ ሲያመርቱ ውለው ያድራሉ። የለማወአብይወአባዱላ ዴሞግራፊን እሰቡት። የአቶ በቀለ ገርባን ጭራቃዊ ጨለማ የዘፍጥረትን ገዳይ ማንፌስቶ አስተውሉት። እንኳን የቁቤ ትውልድ ወጣቶችን ማንዴላ የተባሉት ፕሮፌሰር መራራ ጉዲና ጭካኔ ማርኳቸው ቀኝ ጌታ ሆነው ፀረ ሰው ራዕይን ወደውት፣ አቅፈውት በአውራነት እዬተመሩበት ነው። ሜዳው አልበቃቸውም ብሏል። ይህ አስቀንቶ ወደዚህ ሲኦላዊ መርዛማ መንፈስ የአማራ ፖለቲካ ዘንበል ማለት ለሰከንድ አያስፈልገው። ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር እንጂ በሽተኛ ትውልድ ለመፍጠር አቅም፣ ጊዜ፣ መንፈስ ሊዋጣም፣ ሊባክንም አይገባውም። ሰው ሆኖ ለሰው ልጆች የተረጋጋ የመኖር ዋስትና መትጋት ያስፈልጋል። ሰውነት ደንበር፣ ወሰን የለውም። ኢትዮጵያ የራባት ሰዋዊ፣ ተፈጥሯዊ ሥርዓት ነው። ለዚህ መትጋት የአማራ ፖለቲካ ሁነኛ መሥመሩ ሊሆን ይገባል። ይህን ለማድረ

ፈጣሪ አምላክን ስለ ፍጥረቱ ሚስጢራት አትዳፈሩት።

ምስል

Unity Einheit አንድነት።

ምስል

No War

ምስል

ዬሞት ተማህጽኖ፣ የስቃይባለተስፋ።

ምስል
ዬሞት ተማህጽኖ፣ የስቃይባለተስፋ።     ምን እና ለምን ስለምንስ። ምን አድርገን ተገኜን??? ጭንቀት ያነሰን መሰለወትን? መሬት ደብድበው ማት አውርድ ብለው መና ለቤተ እግዚአብሄር ዬሚልኩ መሪ ነበሯት። ኢትዮጵያ። ጠቅላይ ሚኒስተር አብይም በድምጽ ያገኙትን በትረ ሥልጣን በደም ጎርፍ አጥለቀለቁት። እኛ ቋያ ላይ ያሉ ቅኔወቻችን ነገን እንዲዩ እንዴት ዞር ሊሉ ይችላሉ እያልን እንጨነቃለን ህግ በሌለበት አናርኪዝም በሰፈነበት ባዕት፣ ባረገረገ ዙፋን ልቀቀል ብሎ መፍቀድ ሥምዬለሽ ማት ነው።።።።።።። ውጭ አገር እንደሚሰለቻቸው አውቃለሁ። ግን ይህም መከራ መቀበል ነው። እናቴ አዘውትራ ፃድቅ ትለኝ ነበር። የቀረብኝን ነገር ሁሉ ኡስባ። ፆምም ሲመጣ የሁልግጤ ፆሚነሽ እኮ ትለኝ ነበር። ከሚወዱት ባተሌነት መለዬት መከራን ፈቅዶ መቀበልም ነበር። "ዬቤትህ ቅናት በላኝ።" ዛሬ ምዕራፍ ዘጠኝን ልጀምር ሃሳብ አልነበረኝ። ሦስት ሃሳቦች ሲሞግቱኝ አድረዋል። አንዱ በቤተሰብ ጉዳይ ነው። ሁለተኛው ውሳኔ ነው። ባርች ሆይ ይቅርታ አድርጊልኝ። ሰላም ስጧቸው ቢያንስ አንቺ በመልካምም ቢሆን ሥማቸውን እንዳታነሺ ብለሽ የህማማት ዋዜማ ቃል አስገብተሽኝ ነበር። ይህም በመሆኑ ያዘጋጁት ዬሽግግር ሰነድ በማን እና በምን አመክንዮ እንደ ተጨናገፈ ስገልጽ ኢዴፓ እያልኩ ነበር። የሆነ ሆኖ አሁን ሞት ውሰደኝ፣ ጭንቀት እና ስቃይ ራዕዬ ይሁን ብለው ሲወስኑ ዝም ልል ህሊናዬ አልፈቀደልኝም። ፈጽሞ። ላም እረኛ ምን አለ ዬእኛ ፖለቲከኞች ድርቅ ዬመታው አመክንዮ ነው። የብዙ ነገር ውድቀት፣ የብዙ ነገር ኪሳራ ዬሚነገረው ስለማይደመጥ ነው። ላደለው ንግግር ብቻ አይደለም ዬሚደመጠው። ፀሃይ አድማጭ ትሻለች። ንፋስ አድማጭ ይሻል። ተፈጥሯዊ ወጀብ አድማጭ ይሻል። የወፎች ዜማ አድማጭ ይሻል መ

#የኢትዮጵያ_86ቱ ብሄር ብሄረሰቦች መጠሪያ ስም:-

ምስል
አቶ መላኩ ደጀኔ ዬተገኜ ነው። ይህቺ ኢትዮጵያ ትናፍቃኛለች።      ለጠቅላላ እውቀት #የኢትዮጵያ_86ቱ ብሄር ብሄረሰቦች መጠሪያ ስም:- 1. አማራ 2. ኦሮሞ 3. ትግራዋይ 4. ሶማሌ 5. አፋር 6. ሲዳማ 7. አገው 8. ዎላይታ 9. ከምባታ 10. ሀዲያ 11. ጋሞ 12. ጉራጌ 13. ኢሮብ 14. አርጎባ 15. ቱለማ 16. ስልጤ 17. ሺናሻ 18. አኝዋክ 19. ኑዌር 20. ሀመር 21. ኩናማ 22. ጉምዝ 23. በርታ 24. በና 25. አሪ 26. ሙርሲ 27. ቡሜ 28. ካሮ 29. ፀማይ 30. ኮንሶ 31. ዳሰነች 32. ቦረና 33. ጋብራ 34. አላባ 35. አርቦሬ 36. ባጫ 37. ቤንች 38. ባስኬቶ 39. ቡርጂ 40. ጫራ 41. ጋዋዳ 42. ጌዲኦ 43. ጊዶሌ 44. ጎፋ 45. አደሬ 46. ከፊቾ 47. ኮንታ 48. ኒያንጋቶም 49. ናኦ 50. ቀቤና 51. ሱርማ 52. ጠንባሮ 53. የም 54. ወርጂ 55. ዲዚ 56. ዶንጋ 57. ዳውሮ 58. ዲሜ 59. ምዓን 60. ኮሞ 61. ማረቆ 62. ሞስዬ 63. ኦይዳ 64. ቦዲ 65. ፈዳሼ 66. ኮሬ 67. ማሌ 68. ማኦ 69. መሰንጎ 70. መዠንገር 71. ቀዋማ 72. ቀጨም 73. ሸኮ 75. ዘየሴ 76. ዘልማም 77. ሽታ 78. ቤተ እስራኤል 79. ማሾላ 80. ኮጉ 81. ድራሼ 82. ገባቶ 83. ጌዲቾ 84. ብራይሌ 85. ሙርሌ 86. ኮንቶማ .... ናቸው። ************************ ምንጭ - የኢትዮጵያ ታሪክ፣ Amsalu Getu ኢትዮጵያ በትገነጠል 86አገር ይወጣታል  

ኢትዮጵያ ምን ትፈልጋለች? አቅጣጫችን አዬሩ ምን ይሽታል? ምዕራፍ ዘጠኝ።

ምስል
  ኢትዮጵያ ምን ትፈልጋለች? አቅጣጫችን አዬሩ ምን ይሽታል? ምዕራፍ ዘጠኝ።     "መለዬትን የሚወድድ፦ ምኞቱን ይከተላል፥ መልካሙንም ጥበብ ሁሉ ይቃወማል።" (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፱፰ ቁጥር ፩) አመክንዮ ምን ይናፍቃል? እኛስ? እኔስ? ከአኔ ይጀመር። እሺ። ድካም እና ዬአቅም ፍሰት ለስኬት ሊሆን ይገባል። ትናንት ባልተደራጀ የትግል ፍሰት ሲኦል ውስጥ ተቀርቅረናል። አውራ ነን ያሉትም አውራ መሆን ተስኗቸው የኦነግ አንጋች ሁነዋል። አሁንም ያ እንዳይደገም በጠራ መስመር መጓዝ ግድ ይላል። እና። እኔ እምታገልለት ወሳኝ አመክንዮ። 1) ዬጎሳ ፖለቲካ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲታገድ። 2) ፀረ ሰው፤ ፀረ ተፈጥሮ፤ ፀረ ታሪክ፤ ፀረ ዜግነት የሆነው የአልባንያ ሶሻሊስት ዬዞግ ግዑዝ መንፈስ ጋር የተቃቀፈው ህገ መንግሥት እንዲታገድ። 3) ኢትዮጵያን ሊመራ የሚችል ሰዋዊ፤ ተፈጥሯዊ ግብረ ኃይል ዕውቅና አግኝቶ አመራሩን እንዲረከብ። 3.1 አሁን ያለውን ሥርዓት በኃይል መደምሰስ የሚለውን አልስማማበትም። 3.2 በምርጫ መቀዬር ይቻላል የሚለውን አልስማማበትም። 3.1 በኃይል ማስወገድ ስልጡን መንገድ አይደለም። በተጨማሪ ነገን አጎሳቋይም ነው። ዛሬንም ዬሚገድል። መስዋዕትነቱን ዬሚያከብድ። አቅም ዬሌላቸውን ዜጎችም ለፈተና ዬሚዳርግ።ለቀጣይ ሰዓታት ዬነፍስ ማሳደሪያ ዬሚሆን ዬሌላቸው፤ ሊለምኑ ያፈሩ ሚሊዮኖች፤ አልጋ ላይ ያሉ ወገኖች፤ ህፃናት ብዙ ችግርን ዬምታስተናግድ አገር ይህ ተመራጭ አይደለም። 3.1.1 በምርጫ። ይህን በጀርመንኛ ምርጫ በሰላም ተጠናቀቀ ሲባል ጽፌዋለሁ። አጣዬ ስድስት ጊዜ ተቃጥላ፤ ሽዋ ሮቢት፤ ሻሸመኔ፤ ዝዋይ፤ ሃረር፤ ጅማ፤ ነደው፤ ሚሊዮኖች በገፍ ተፈናቅለው ከደቡብ እስከ ማዕከላዊ ጎንደር፤ በጦርነት፤ በስጋት በጭንቅ ህዝብ ሌላ አማራጭ ዬ

ዓላማ እንኳን ተፈጠርክልኝ ብሎ ዬሚመርቀው አቶ ኤርምያስ ለገሰ። • ለዓላማው ፍፁም ታማኝ።

ምስል
  ዓላማ እንኳን ተፈጠርክልኝ ብሎ ዬሚመርቀው አቶ ኤርምያስ ለገሰ። • ለዓላማው ፍፁም ታማኝ።   ለእኔ አቶ ኤርምያስ ለገሰ ግድፈታቸው ሳይዝረከረክ ጠቅላይ ሚር አብይ እንዲመሩ የተጋበት ዓላማው ነው ብዬ አምናለሁኝ። መብቱም ነው። አያደናግር ነበር በቀደመው ጊዜ ስሞግተው የነበረው። ኦህዴድ መራሿ ኢትዮጵያም ናፍቆቱ ናት ብዬ አምናለሁ። ይህም ሙሉ መብቱ ነው። አማራ ለሞቱ ግን ተኝተህ በለኝን ከዝኖ የያዘበት ስልቱ ያመኝ ነበር። ሰሚም ዬለም። ስንት ሰው ፈዞ፦ ደንዝዞ፣ ስንት አቅም ብን ብሎ ተፍረክርኮ ቀረ? "ዬቤትህ ቅናት በላኝ።" #ጠብታ ። አሁን ወጀቡ ረብ ብሏል። የጎሸውም ጠርቷል። ስለዚህ ሃሳቤን በሰከነ ሁኔታ ማቅረብ ፈለግሁኝ። አቶ ኤርምያስ ለገሰን ኢሳት መስራት ከጀመረበት ወቅት ጀምሮ አዬር ላይ አውቀዋለሁ። በደጉ ሳተናውም በሁለት ፁሁፎቼ ሞግቸዋለሁኝ። በተጨማሪም በባልደራስ እስር እና ያራምደው በነበረቀቀው ዬንደት ስልቱም በተከታታይ ፌስቡኬ ላይ ሞግቸዋለሁኝ። ሂደቱ በጥዋቱ ነበር የገባኝ እና። ከዛ በተረፈ ከህወሃት ሥልጣን ስለምን ዓላማ እንደለቀቀ፤ ሰብዕናውን ለአምስት ተከታታይ ዓመት ልክ እንደ አቶ ጃዋር መሐመድ አጥንቸዋለሁኝ። ምክንያቴ ሁሉም በዬቀለሙ ምን አስተዋፆ ሊኖረው ይችላል በሚል አርቄ ሳይሆን አቅርቤ የእኔ ብዬ አጥንቸዋለሁኝ። የፖለቲካ ድርጅት ተከፋይ ቋሚ ሠራተኛ መሆን እና ተምሮም ፖለቲካ ሳይንስን ዕድሉ ከሌለ የሰፋ ልዩነት አለው። በዚህም የዳበረ የፋንክሸነሪ ተመክሮ አለው። ከህወሃት ጋር መሥራቱ ከልጅነት እስከ ዕውቀት ከጫካ እስከ እስር ቤት ከእስር ቤት እስከ ስደት በነበረኝ ፀረ ህወሃት እና ባልተለወጠው አቋሜ ላይ ሆኜ አቶ ኤርምያስን ከህወሃት ጋር ሰራ የሚለው ወቀሳ ያመኛል፤ ለዚህ ተልዕኮም እስከ መጨረሻው ተባባ