ቢሆን። ምኞት ነው ተስፋን ያጨ። #የአይዟችሁ ሠራዊት ያስፈልጋል።
ቢሆን። ምኞት ነው ተስፋን ያጨ። #የአይዟችሁ ሠራዊት ያስፈልጋል። በቀጣይ ሊሆን የሚገባው ዬእርዳታ ሥርጭት ተጓዳኝ አመክንዮ ነው። ላም እረኛ ምን አለን ማድመጥ ላልተሳናችሁ ነው ይህን ዕይታዬን እማጋራው። ማህበረሰቡም ይህን የአቨው አስተውሎ ሊያደምጠው ይገባል። ሁሉ ነገር በመንግሥት ብቻ አይሆንም። ሲቢል ድርጅቶች ይህን ክፍተት ሊሞሉት ይገባል። "ዬቤትህ ቅናት በላኝ።" ህወሃት በለቀቀው ቦታ ሽሬ ይመስለኛል የተከዘነ የእርዳታ እህል ለነዋሪው ሲከፋፈል አዬሁኝ። መልካም ነገር ነው። ህይወት ማትረፍ ለሥጋ ሳይሆን የነፍስ ነውና። ለምን ዬተደራጀ ተግባር አልተከወነም ልል አልችልም። አንድ ኩታራ ልጅ ነበር ሥም ጠሪው። በጦርነት ቀጠና ውስጥ ላለ አስተዳደር፣ ሠራዊት በልጅነት ስላዬሁት የሚክዶናል ቨርገር እንዳልሆነ እረዳለሁኝ። ይህ ባይሆን ምርጫዬ ነበር። እርስ በርስ ውጊያ ስልጣኔ አይደለም። በእኛ ቢበቃ። ዬሆነ ሆኖ እህሉ ከታደላቸው ነዋሪወች ውስጥ አንዲት እናት አዬሁኝ። ነጠላቸውን ውልቅ አድርገው እንደ ገመድ እንዲያገለግል፣ ፍግም ብለው ተጎንብሰው 25 ኪሎ ይሆናል በዓይን ስገምተው ያን ተሸከሙ። እና ወደ ቤት ተጓዙ። በዚህ ውስጥ ብዙ ርብሽብሽ፣ ብጥብጥ ዬሚያደርግ ሃሳብ ነሰተኝ። እስከመቼ? ስለምንስ? ለእነኝህ ደካ እናቶች ያልሆነ ዬ50 ተጋድሎ አልቦሽ ሂደቱን በምልሰት ቃኜሁት? እናቴን ያሰቃዬኋት፣ ያስጨነቅኳት፣ ያከላተምኳት ታወሰኝ። እናም አንጀቴ ተላወሰ። ስፈጠር እንዲህ ሆኜ ስለሆነ መዳን አልችልም። የበዛ ችግር አለብኝ። በጣም ዬበዛ። እኔን ደፍሮ መርዶ ዬሚነግር አልነበረም። ዛሬ ደግሞ ሰርክ መርዶ ሆነ ያው ማህበራዊ ሚዲያ እንጂ በቤተሰብ ቅንጣት አይነገረኝም። አግደውኝ ነው ዬኖሩት ፌስቡክ እንዳልሳተፍ