ልጥፎች

ብፁዑ አባ ልቅና ማዕዶተ - ዕውነትን ተመገቡት። ጠጡት።

ምስል
  ብፁዑ አባ ልቅና ማዕዶተ - ዕውነትን ተመገቡት። ጠጡት።   "ዬቤትህ ቅናት በላኝ።"   "ዬኦሮምያ ህብረት ባንክ የቤተክርስትያኗን ቅምጥ ሃብት በካዝናው አስቀምጧል። እንሸነፍ ብለን። አዋሽ ባንክ፤ ዬኢትዮጵያ ንግድ ባንክም ድርሻ አላቸው። ብዙም የረባ በንጠቀምም። አባይ ባንክ ግን ተወዳድሮ በገብያ ህግ አሸንፎ ነው። ከአማራ ባንክ ጋር ምንም ዓይነት ውል ዬለንም። ከእሱ ይልቅ ከሌሎች ተጨማሪ ባንኮች ጋር ዬጠበል ያህል አብረን እንሰራለን። የተሻለ ዬሚጠቅም ተወዳዳሪ ከመጣ ደግሞ ውላችን ይቀጥላል። " ……… ከጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ጋር ስለነበረው ውይይት ተጠይቀው ሲመልሱ ከመሄዳቸው በፊት እንደምን እንደ ተሰናዱ፤ ከዛም ከሞት ጋር ፊት ለፊት ቆመው እንደምን እንዳስረዱ ገልፀው የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድን ትዕግሥት አድንቀው ጠቅላይ ሚሩ ሊያወያዮዋቸው እንደጠዬቁ እና ጠቅላዩ ማዕከላዊ ይሆኑ ዘንድ፤ መንግሥታቸው ያለበትን ኃላፊነት እንዲወጣ በትህትና ገልፀው የቤተክርስትያኗ ጉዳይ አወያዮዋም፤ አነጋጋሪዋም ውል አስፈፃሚውም ዶግማና ቅኖናዋ ስለመሆኑ እንዳስረዱ፤ በዚህም እንደተስማሙ ከገለፃው ዕድምታ ተረድቻለሁኝ። የእግር እና የጭንቅላት አስተዳደርን ፍልስፍናም ባርከውልናል። ሰላማዊ ሰልፍ የገኃዱ ዓለም እና የሰማያዊውንም ፍንትው አድርገው ገልፀውታል። በዚህ እንደ ተረዳሁት ሰማያዊው ሰልፍ በሚያስደምም አኳኋን መከወኑን አብሥረዋል። የአንድም ሦስትም ሆኖ የመምራት ዬማስተዳደር ክህሎትን፤ ዊዝደምን ሲገልፁም የእጬጌው የብፁወቅዱስ አባታችን አቡነ ማትያስ ልዩ ስክነት እና ዬረጋ ብስለት እንዲሁም የበታቾች አባ ትምህርት ብፁዑ ዶር አቡነ ጴጥሮስ እና የአባ ልቅና ዬብፁዑ አቡነ አብርኃም አህቲ መስመር ዕውነት ስለመሆኑ በአጽህኖት ገልፀዋል።
ከፀሐፊ አቶ አሳዬ ደርቤ ያገኜሁት ነው። #እባካችሁ_Share_አድርጉት "ለኦርቶዶክስ ልጆች የተዘጋጀውና አዋሽ አርባ አካባቢ የሚገኘው ምድራዊ ሲዖል!.. ▬▬▬▬▬ እነ ስንታየሁ ቸኮልን ጨምሮ ከአዲስ አበባና ከኦሮሚያ ክልል የታፈሱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የታሠሩት አዋሽ አርባ የማጎሪያ ጣቢያ መሆኑን ስሰማ የሚከተለውን ታሪክ ላጋራችሁ ወደድኩ። አባ ሳሙዔል እስር ቤት ሳለሁ በአዋሽ አርባ የማጎሪያ ጣቢያ ታስረው የከረሙ ከአምስት መቶ በላይ ዜጎችን አግኝቼ ነበር። እኒህንም ዜጎች "ስለ አዋሽ አርባ አውሩኝ እስኪ" ስላቸው ቶርች የተደረገ ሰውነታቸውን እያሻሹ እንዲህ የሚል ተመሳሳይ ማብራሪያ ነበር የሚነግሩኝ። " አዋሽ አርባ የማጎሪያ ጣቢያ ማለት ➔የማታውቀውንና ያልሰራኸውን ወንጀል አጋልጥ" የሚሉ መለዮ ለባሾች ማዕከላዊን የሚያስንቅ አረመኔያዊ ድርጊት የሚፈጽሙበት፤ ➔እንደ ኢሰመኮ እና ኢሰመጎ ያሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ከእነ መኖሩም የማያውቁት፤ ➔ቤተሰብ ቀርቶ ሲቪል የለበሰ ሰው የማይታይበት፤ ➔ፍርድ ቤት ሳትቀርብ ከሶስት ወር በላይ ታስረህ የምትቆይበት፤ ➔በ24 ሰዓት ውስጥ አንድ ዳቦና አንድ ኩባያ ውሃ ብቻ በሬሽን መልክ የምታገኝበት፤ ➔የመጸዳጃ ቤት ጥያቄ ስታቀርብ "ፌስታል ላይ ተጠቀም" የሚል መልስ የምታገኝበት፤ ➔ከጸሎት ውጭ ምንም አይነት የሕክምና አገልግሎት የሌለበት፤ እናም እልኻለሁ.... ስንታየሁ ቸኮልን ጨምሮ ከአዲስ አበባና ከኦሮሚያ አካባቢ የታፈሱ አብዛኞቹ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የሚጓጓዙት ወደዚያ ምድራዊ ሲዖል ነውና ይሄንን መረጃ ሼር በማድረግ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች እንዲደርሱላቸው እናድርግ።"

ከጋዜጠኛ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ።

ምስል
  "አድርገህልኛል እና አመሰግንኃለሁኝ።"     መምህር፤ መርጌታ፤ ጋዜጠኛ፤ ርቱዑ፤ ሩህሩህ፤ ጽኑ ወጣት። እሱን የሰጠን አምላክ ይክበር ይመስገን አሜን። ለእናቴ፤ ለክብርቴ፤ ለቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጠቅላይ ቤተክህነት እንደ ልጅነቴ ይህን ባለ ቅብዓ ሽልማት ብትጠቀምበት። ዬተከበረ፤ ዬተደላደለ ቦታ በአማካሪነት ሰጥታ ትውልድ ፋናውን ይከተል ዘንድ ዕድል በሩን ብትከፍት እመኛለሁኝ። ተስፋ ዬእግዚአብሄር ነውና። ተስፋ አደርጋለሁ። እናት ቤተክርስትያኔ የእኔን የትቢያዋን ልጇን መሻት ብታደምጥ። ዛሬ ለደወለችው የደወል ንቅናቄ የዛሬ አራት ዓመት ጽፋዋለች፤ አስተምራዋለች። እናቴ የህልውና አደጋ ላይ ናት ንቁ፤ ትጉ የሚል ሳምንታዊ መርኃ ግብር በድወሏ ድምጽ ብቻ ታቀርብ ዘንድ አስቀድም፤ እጅግም ቀድማ ተናግራለች። ፖለቲከኞች ጥሞና አያውቁም። ላም እረኛ ምን አለ ጉዳያቸው አይደለም። ግን አልበረከቱም። አብሶ አቅምን ማኔጅ በማድረግ አልቦሽ ናቸው። "ኹሉም ነገር የቀናት ጉዳይ ነው። የትኛውም የሴራ ፈትል የትኛውም የተንኮል ጉንጉን መበጣጠሱ አይቀርም!!!ምክንያቱም ሰልፉ የእግዚአብሔር ነው።" ተዋሕዶ #ኢንፈርህ_ሞተ #ሞትን_አንፈራውም ዬሆነ ሆኖ "ዬሚጠላ ሰው ሲያልፍ ብትጠላው ጥቁር አትለብስም ግን ነጭ ለብሰህ አትታይም። " ይገርማል። ዘመን የማይተካው ጋዜጠኛ ጋሼ ሙሉጌታ ሉሌ በድንገት በ2015 እኤአ ስናጣው ስለ እሱ በተሰራ ልዩ ዝግጅት በነጭ ሸሚዝ ያዬሁት አውራ ጋዜጠኛ ነበር። የአውራ ፓርቲ ልሳን። ብፁዑ ወቅዱስ ፓትርያርከ ዘኢትዮጵያ አባታችን ፃድቁ አቡነ መርቀርዮስ በሥጋ ሲለዩን እፎይ ያሉ የሚዲያ ሰወች ሙሽራ ይመስሉ ነበር። ነጭ ለብሰው ነበር ተግባራቸውን የከወኑት፤ ሌላም ሚዲያ ቆራጣ የዕንባ ጠብታ አልነበረም።

"ዬንጋት ጨለማ ድቅድቅ ነው። ግን አጭር ነው።"

ምስል
"ዬንጋት ጨለማ ድቅድቅ ነው። ግን አጭር ነው።" ትምህርተ አባ ብፁዑ አቡነ ጴጥሮስ። "ወደ እግዚአብሄር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስአለኝ።" አጽናኝ ነው። በከፋኝሰዓት አግኝቼው ያጽናናኝ ነው። በጉነት ቅጣት ዬሚሆንበትን ዘመን ያመሳጥራል። • https://www.youtube.com/watch?v=mc4zFX7mxH0&t=4s «የንጋት ጨለማ መደመጥ ያለበት አጽናኝ ትምህርት || የአባታችን በረከታቸው ይደርብን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ» ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 13/02/2023 ወስብኃት ለእግዚአብሄር። አሜን።  

Es ist eine traurige Geschichte.

Es ist eine traurige Geschichte. • https://www.aljazeera.com/.../whats-behind-the-crisis-in... “What's behind the crisis in the Ethiopian Orthodox Church?” ቅድስቷ እና ዓለም አቀፍ ሚዲያ። "አድርገህልኛል እና አመሰግንኃለሁኝ።" ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 13/02/2023  

ትምህርተ ማተብ።

ትምህርተ ማተብ። "1. ሰባቱ አባቶች ሀ. ሰማያዊ አባት እግዚአብሔር ለ. የነብስ አባት ሐ. ወላጅ አባት መ. የክርስትና አባት ሠ. የጡት አባት ረ. የቆብ አባት ሰ. የቀለም አባት 2. ሰባቱ ዲያቆናት ሀ. ቅዱስ እስጢፋኖስ ለ. ቅዱስ ፊልጶስ ሐ. ቅዱስ ጵሮክሮስ መ. ቅዱስ ጢምና ሠ. ቅዱስ ኒቃሮና ረ. ቅዱስ ጳርሜና ሰ. ቅዱስ ኒቆላዎስ 3. ሰባቱ የጌታ ቃላት(እኔ ነኝ) ሀ. የህይወት እንጀራ እኔ ነኝ ለ. የአለም ብርሃን እኔ ነኝ ሐ. እኔ የበጎች በር ነኝ መ. መልካም እረኛ እኔ ነኝ ሠ. ትንሳኤና ህይወት እኔ ነኝ ረ. እኔ መንገድ እና ህይወት ነኝ ሰ. እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ 4. ሰባቱ ሰማያት ሀ. ጽርሐ አርያም ለ. መንበረ መንግስት ሐ. ሰማይ ውዱድ መ. እየሩሳሌም ሰማያዊት ሠ. ኢዮር ረ. ራማ ሰ. ኤረር 5.ሰባቱ ሊቃነ መላዕክት ሀ. ቅዱስ ሚካኤል ለ. ቅዱስ ገብርኤል ሐ. ቅዱስ ሩፋኤል መ. ቅዱስ ራጉኤል ሠ. ቅዱስ ዑራኤል ረ. ቅዱስ ፋኑኤል ሰ. ቅዱስ ሰቂኤል 6. ሰባቱ አቢያተ ክርስቲያናት ሀ. የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን ለ. የሰርምኔስ ቤተ ክርስቲያን ሐ. የጴርጋሞን ቤተ ክርስቲያን መ. የትያጥሮስ ቤተ ክርስቲያን ሠ. የሴርዴስ ቤተ ክርስቲያን ረ. የፊልድ ልፍልያ ቤተ ክርስቲያን ሰ. የሎዶቅያ ቤተ ክርስቲያን 7. ሰባቱ ተዓምራት ጌታ እየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈፀሙ ተዓምራት ሀ. ፀሐይ ጨልሟል ለ. ጨረቃ ደም ሆነ ሐ. ከዋክብት ረገፉ መ. አለቶች ተሰነጣጠቁ ሠ. መቃብራት ተከፈቱ ረ. ሙታን ተነሱ ሰ. የቤተ መቅደስ መጋረጃ

እንደ ጠርሙስ ጭንቅላታቸውን ከሰከሱት፤

ለመናገር ሳይሆን ለማድመጥ ጊዜ ይኑረን። ልመና ነው። • https://www.youtube.com/watch?v=c6CMNXJ3BP8 EOTC TV | ወቅታዊ ጉዳይ | ደም ረግጠው ገብተው ፎቶ ይነሳሉ እንዴት ነን? አቅም አገኛችሁ ይሆን? አይዟችሁ። "ከመከራ በስተጀርባ ታላቅ ክብር አለ" "እንደ ጠርሙስ ጭንቅላታቸውን ከሰከሱት፤ ሌሊቱን ሙሉ ከተማይቱን በማዘጋጃ ቤት ፅዳተኞች አፀዱት፤ ሽታው አያስቀርብም፤ ዬተገኙት፤ ያሉትን ለመለዬት ሄደን ለማፅናናት ይፈቀድልን፤ ጥቃቱ ሦስት ነው ታግቶ ስንቅም መፀዳዳትም ዬማይፈቀድለት፤ ከዬቤቱ እዬታፈሰ ዬት እንደተወሰደ ዬማይታወቅ፤ በጅምላ ዬሚገደል፤ ዬሚቆስል፤ ዬሚደበደብ …… ከሌላ ቦታ አምጥተውደፋበት ……" ዕድምታውን አዳምጡት። አቅም ዬለኝም ለመሥራት። "የመከራን ቀን እጠብቃለሁ።" ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 09/02/2023 ቸርነትህን አበራክትልን፤ ምህረትህንም ላክልን። አሜን።  

ዬማተቤ ድምፅ ብቻ መሪዬ ነው።

ዬማተቤ ድምፅ ብቻ መሪዬ ነው። "ኢትዮጵያ ነነዌ ናት። ዕውነት ማብራሪያ አይሻም። ዕውነት እራሱ በቂ ነው። ያለ ደም መስዋዕትነት አለ። ሥራ አታብዙብን። ያለብን መከራ ይበቃናል። "በኢትዮጵያ ውስጥ ዬጥቁር ቀን ታሪክ ተጽፏል።" (ብፁዑ አባታችን አቡነ ጴጥሮስ።) • https://www.youtube.com/watch?v=tuwl_GsfHv0 EOTC TV | "ወቅታዊ ጉዳይ | የሴራ ፖለቲካ አያዋጣም" ከጽናት ጉልላት ዬኢትዮጵያ ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ድምጽ በስተቀረ ሌላ ለማድመጥ አንፍቀድ። መሪ አለን። ሙሴ አለን። እረኛ አለን። መሪ፤ ሙሴ፤ እረኛ ያለው የሃይማኖት ሰው ድምፁን የሚያገኜው ከማተቡ ብቻ ነው። አዳምጡት። በዛ መስመር እንጓዝ። መረጃውን ማሰባሰብ ጥሩ ነው። ጉዟችን ቀያሽ ግን ዬኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ብቻ ልትሆን ይገባል። ጋዜጠኛ፤ ፀሐፍት፤ ዬፖለቲካ ተንታኝ ለገኃዱ አለምነው። ለመንፈሳዊ ሕይወት ሚስጢረ ጥምቀት ነው ብርኃናችን። ቅድስታችን ፕሮፖጋንዲስት፤ ማኒፌስቶ፤ ካቢኔ አይደለችም። የሐዋርያት መሠረት እንጂ። ድምፀ ተዋህዶ ከኢትዮጵያዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ብቻ። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 09/02/2023 የብፁዓን ቅዱሳን አቨው ፀሎት እና በረከት ይደርብን። አሜን።  

#ለዘዋራ ሰብዕና ዬድፍረት ሐጢያት ያሰምጣል። #ለአሳቸው እና ለዘዋራው ለጠቅላይ ሚር ነው መልዕክቴ።

  #ለዘዋራ ሰብዕና ዬድፍረት ሐጢያት ያሰምጣል። #ለአሳቸው እና ለዘዋራው ለጠቅላይ ሚር ነው መልዕክቴ። #ሳናይ አምነን #ስናይ ተቀጣን። "ከንቱ ዬከንቱ ከንቱ ሁሉ ነገር ከንቱ።"   ሄሮድስ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ንቅንቅ ሳይል በትረ ሥልጣኔ ይቀጥላል ብለው በጨቀጨቅ መጪ እያሉ ነው። አሳቻነታቸው መስታውት ሆኗል። የሰው ልጅ ደም ለዛውም ሙሉ አምስት አመት ወደ እዮር ይላካል። ፈለጉትም አልፈለጉትም። አሁን ባለው ሁኔታ እሳቸው ፈብርከው ከሚፈጥሩት ቀውስ ውጪ አንድም ነፍስ ያለው ተቋም ቀርቶ አሰባሳቢ አጀንዳ ያለው የፖለቲካ ድርጅት ዬለም። ሁሉንም ፈጥፍጠው አፍዘውታል።   የተዋህደው ተዋህዷል፤ ዬተንከረፈፈው ጠርዝ ላይ ተንጠልጥሎ ኮሽ ባለ ቁጥር እዬተጣመረም እዬተሰባሰበም የመግለጫ ሲሳይ ሆኗል። በሳቸው ዘመን እንኳንስ የዓለምኔ ፖለቲካ ዬሚመጥን አቅም ያለው ተፎካካሪ የፖለቲካ ድርጅት ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለለብ ማውጣት አይታሰብም። ምክንያት አንደኛው ሰላይ ናቸው። ሁለተኛው በተፈጥሯቸው ዬተዥጎረጎሩ ሁነው ዬተፈጠሩ ናቸው።    ዬዓለሙን ሎሬት ሽልማት ከመውሰድ በላይ ድል ዬለም። በጨካኝ ሥርዓት ተወልገው አድገው ወስደዋል። እራሳቸው አስመራጭ ኮሜቴ ሆነው ፕሬዚዳንት ዬሚል ሥያሜ ቀርቶ ነበር ጠቅልለዋል። እሳቸው አይታመሙም፤ አካላቸው አይጎድልም፤ ድምፃቸው አይዘጋም፤ ዬምንም ዓይነት አደጋ አይደርስባቸውም። ዘሊለማዊ ናቸው። ዕሳቤያቸው ይህ ነው።    ዬሚያስታግሱን ሰጥ ለጥ ካደረጉ በኋላ በዬቤቱ እዬዞሩ በዶላር የሚያማልሉትን በዶላር፤ በስልክ ዬሚያማልሉትን በስልክ፤ በሽምግልና ዬሚያማልሉትን በሽምግልና፤ በብክል ዬሚሸኙትን በብክል፤ ለካቴና ዬሚሰጡትንም እንዲሁ። ኢትዮጵያ መዳፋቸው ውስጥ ናት። አባ ቶርቤ መሃንዲስ፤ አስተናጋጅ፤ ሃኪም፤ ነጋዴ፤ ተ

አባ ገብረ ሚካኤል ፈንቴ

ምስል
  ለበረከት ክብሮቼ ተሽቀዳደሙ። "ሰለማይነገር ሰጦታው እግዚአብሄር ይመሰገን አባታችን ተገኝተዋል እኔም ከእንግሊዝ በርኒግሀም እኛው ለእኛው መደራጇ መሀበር ካገኝሁት ብር ላይ 10 ሺ ብር ሰጥቻቸዋለው አባታችንን ለመርዳት ለማገዝ ከፈለጋቹ ይሄ ትክክለኛ ሰልካቸው እና የባንክ አካውንታቸው ነው አባታችን ህክምና ያሰፋልጋቸዋል 0912137799 ሰልካቸው ነው አባ ገብረ ሚካኤል ፈንቴ 1000200837936 ንግድ ባንክ ዳይ ወደ መርዳትና ሼር ወደ ማድረግ ሱራ የኪዲዬ ልጅ " "ዬቤትህ ቅናት በላኝ።" "አባታችን አባ ገብረ ሚካኤል ፈንቴ ህክምና ጀምረዋል። ቅዱስ ኡራኤል ኪሊኒክም ሙሉ ወጭውን ችሎላቸው ህክምና ማድረግ ችለዋል። አባታችንን ለመርዳት ለማገዝ ከፈለጋቹ ይሄ ትክክለኛ አካውንታቸው እና ስልካቸው ነው ደዉሉላቸው፤ 1000200837936 ንግድ ባንክ አባ ገብረ ሚካኤል ፈንቴ 0912137799 ሰልካቸው ነው።"……… ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 09/02/2023 አቤቱ ሃጢያታችን በርክቷል እና ምህረቱን ላክልን።     " ዝም ብዬ ዬመከራን ቀን እጠብቃለሁ" በመከራ ቀን ደግነት ይንገሥ። ዬተከበሩ ዶር ዳንኤል በቀለ እባከወት መታመናችን አይካዱት። እባክወትን። ይህን ቃለ ወንጌል ለረጅም ጊዜ ተጠቅሜበታለሁኝ። አንዲት ብሩክ እህቴ ለመነችኝ። ለእሷ ስል አስታገስኩት። እሷ መቼ ትግል እንደ ጀመረች አላውቅም። ዬእኔው በጥዋቱ ሆነ እና ዘመኔን በዕንባ ሸኜሁት። ውስጤ ዬሚለኝን ነገር ሳልቆጥብ፤ ዬዘመኑን የፖለቲካም ባህሬ፤ ዬሄሮድስ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ያልተገለጠ ተቆጥቦ እዬተመነዘረ ጥቅም ላይ የሚውለው ተለዋዋጭ ሰብዕና፤ ኢትዮጵያ ከተፈጠረችበት ዘመን ያለውን ክፋ ነገር ሁሉ ሪባይዝ በማ

መንፈሳዊ የሐዘን ቀን በብሄራዊ ደረጃ አዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፋ ይቻላንል? ኦሮምያ ክልል ከፈቀደ ብቻ። ይህ ለብዙወቻችሁ መርዶ ሊሆን ይችላል።

  መንፈሳዊ የሐዘን ቀን በብሄራዊ ደረጃ አዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፋ ይቻላንል? ኦሮምያ ክልል ከፈቀደ ብቻ። ይህ ለብዙወቻችሁ መርዶ ሊሆን ይችላል። "ዬቤትህቅናት በላኝ።" በጣም ለረጅም ጊዜ ጽፌበታለሁኝ። አዲስ አበባ ላይ ምንም ዓይነት ህዝባዊ ንቅናቄ በአደባባይ አይፈቀድም። ምክንያቱ ከፔጄ ላልቆያችሁ ለአዲሶቹ መርዶ ሊሆን ይችላል። እንደ ሥርጉተ ዕይታ ከመስከረም 05/2011 ጀምሮ አዲስ አበባ ዬኦሮምያ ክልል ሆናለች። ኦህዴድም፤ ኦፌኮም መግለጫ ሰጥተውበታል። ዬፌድራሉ መንግሥት ማስተባበያ አልሰጠም። አልገሰፁም። ለምንኢትዮጵያ ስለተጠለፈች። አዲስ አበባ ውስጥ ያሉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ፤ ፌድራላዊ ተቋማትም ተጠሪነቱ ለኦሮምያክልል ነው። መርዶ ነው ይሄ ዬማይታዬው እኮ ጠቅላይ ሚሩ ከኦሮምያ ዬመጡ ስለሆነ አይታያችሁም ዕውነቱ። አባይ በጣና ላይ፤ ጣና በአባይ ላይ ተዋህደው ሲኖሩ አይታይም። ልክ እንደዛ ነው። ማንኛውም ብሄራዊ ክንውን በዋዜማው የኦሮምያ ፕሬዚዳንት ወጥተው ይናገራሉ። ለምን? ጠቅላይ ሚሩ አንድ ነገር ቢሆኑ ዬሚተኩ እሳቸው ስለሆኑ ነው። ደቡብ ሲሄዱም ይዘዋቸው ነው ዬሚሄዱት። በ2011 ዬፃፍኩት ነበር አዲስ አበባ ከውጪ ሲገባ በቢዛ ይሆናል ብዬ። ለምን የያዙት አቅጣጫ ያ ስለሆነ። ለአፍሪካም አስጊ ነው። አንድ ሆቴል የምስራቅ አፍሪካ ባህል ማዕከል በኦሮምያ ዬሚል አዳምጫለሁኝ። ለነገሩ በ2019 ታህሳስ ላይ ለአፍሪካም አስጊ መሆኑን በድፍረት ጽፌበታለሁኝ። ከሁሉ በላይሄ ሮድስ ጠሚአብይ አህመድ ዘዋራም፤ አሳቻም ናቸው። ብዙ ግሎባል ፍላጎቶችን አከማችተው ለመፈፀም ሁሉ ዲታ ሆነዋል። ይህን ያልተረዱ ሰብዕናወች ምርኩዛቸው ናቸው። አሁንም አቅጣጫእዬሰጡበብፁዓን ቅዱሳን አባቶቻችን ላይ እስር እንዲኖር ዬአቅጣጫ በር ሲከፍቱ ተመልክቻለሁኝ።

የዬካቲት 5/2015 ህዝባዊ መንፈሳዊ ሰልፍ ቅድመ ሁኔታው ካልተሟላ ይካሄዳል ዬሚል መንፈሳዊ መግለጫ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ተሰጥቷል።

የዬካቲት 5/2015 ህዝባዊ መንፈሳዊ ሰልፍ ቅድመ ሁኔታው ካልተሟላ ይካሄዳል ዬሚል መንፈሳዊ መግለጫ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ተሰጥቷል። ትናንት ማምሻ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት ዬሰጠው መግለጫ ዬኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ምላሽ ሰጥታለች። በፆመ ነነነዌን ምህላ ዬንስኃ ፀሎት መጠናቀቁን ተገልጧል። ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍንም በሚመለከት ቅድመ ሁኔታወች ካልተሟሉ ዬቀጣይ ዬህልውና ተጋድሎም እንደሚቀጥል አቅጣጫ ተስጥቷል። እናዳምጥ። ከልባችን ሁነን። ፀሎቱ፤ ምህላው፤ ሱባኤው በፈቃድ መቀጠል ይገባል። ከ30 በላይ የሆኑ ሰማዕታትን አስባለች። ፍትኃቱ እንደሚቀጥልም አስገንዝባለች። ዬተጎዱትንም ለመጠገን፤ ለማፅናናትም ፈቃድ መታጣቱን ቅድስቷ ገልፃለች። አዳዲስ ቅዱሳን ሰማዕታት ማግኜቷን ቤተክርስትያኗ መጽናናትን ማግኜቷ ገልፃለች። ቅድስታችን ግልፅ እና ቀጥተኛ ጥበባዊ መካች ትሁታዊ አቋምን ገልፃለች። የክልል መንንግሥታዊ አስተዳደርን አድንቃለች ሱማሌ፤ ቬንሻንጉል፤ ደቡብ ምዕራብ፤ ደቡብ፤ ድሬደዋን፤ ሀረሬ፤ አፋር፥ ሲዳማን አስተዳደሮችን አመስግናለች። ሌሎች ተቋማትንም ትብብራቸውን ለገለፁ ዬኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ዕውቅና ሰጥታለች። ህገ ወጦችን ዕውቅና በመንግሥት ዕውቅና መሰጠቱ፤ ዬተሰጠው መግለጫም ቅድስት ቤተክርስትያናችን አለመቀበሏን በሃዘን ገልጣለች። ቃላት አጠቃቀሙም መልካም አለመሆኑ ገልፃለች። #መግለጫው ። መንፈሱ ……… ለኢትዮጵያ መንግሥት …… በደላችን ለዓለምዓቀፋ ማህበረሰብ ለማሳወቅ ተገቢውን ጥበቃ እንዲያደርግልን መፍቀድ ወይንም ያቀረብነውን ቅድመ ሁኔታ ማሟላት እንጂ ሰማዕትነታችን ደስ ብሎን እንቀበላለን። ልጆቻችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የታሠሩ እንዲፈታ፤ ካሳ እንዲከፍል ለበደለው፤ አገር አቀፍ ሰልፋችን በራሳችን አደ

የዶ/ር ወዳጄነህ መልዕክት‼️

ምስል
ምስክርነት። ተመስገን። የዶ/ር ወዳጄነህ መልዕክት "እኔማ የኢትዬጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያንን የማውቃት ይመስለኝ ነበር። ባለፉት ሦስት ቀናት እንደተረዳሁት ግን ስላንቺ የነገሩኝ ሰዎችና መጻህፍት ሁሉ ካለሽ ክብር፣ ሞገስና ዝና ከፊሉን እንኳን እንዳልነገሩኝ ነው። ተዋህዶ ሆይ!" "ንፁህ እምባ፣ ጥልቅ ትህትና፣ ብርቱ ትዕግስት፣ ታላቅ ጥበብ፣ ብዙ እውቀት፣ ሰፊ ማስተዋል፣ የሚያስፈራ ግርማ አየሁብሽና ተገረምኩኝ፣ ልቤ ተደነቀ፣ እጄን በአፌ ላይ ጫንኩኝ! የጸሎትና የምልጃሽ እጣን የልዑል እግዚአብሔርን ቤተመቅደስ ሲያጥነው፣ ዙፋኑን ሲያውደው ማየት እንኳን እኔን ደካማውን ሰው ይቅርና ቅዱሳን መላዕክቱን ያስደንቃል።" " በነቢዩ በዳንኤል መፅሃፍ እንደሚነበብ እጅ ያልነካው ድንጋይ ከሰማይ ወርዶ ሳይፈርስ ፣ ሳይከፈል፣ ሳይቆረስ ታላቅ ተራራ ሆኖ ጸንቶ እንደኖረ አንቺም በኢትዮጵያ ምድር ላይ ታላቅ ተራራ ሆነሽ ለአፍሪካ ትምክህት፣ ለመላው አለምም ክብር ሆነሽ ትኖሪያለሽ። ከእግዚአብሔር የተማሩት፣ ትሁታንና ብሩካን የሆኑት፣ ማቅ የለበሱልሽ የተወደዱ ልጆችሽ እንዴት የታደሉ ናቸው! ከሩቅ እያየሽ የሚወድሽና የሚያከብርሽ ዶ/ር ወዳጄነህ መሐረነ"  

ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ የገባው በ4ኛው ዓ.ም የዛሬ 2019 ዓመት

በሉ እንግዲህ የምትወዱኝ አንብቡ የምትጠሉኝ በግዜ ጥፉ! ተቀራራቢ ትርጉም ኮፒ 1. የመጀመሪያዎቹ ጋላዎች (ኦሮሞዎች) ጣዖት አምላኪዎች፣ የአምልኮ ዛፎች፣ ወንዞች፣ ተራራዎች፣ ፀሀይ፣ ጨረቃ እና ከዋክብት ነበሩ፣ እና ብዙዎቹ ጋላዎች እስከ ዛሬ እነዚህን ያመልካሉ። ለእነዚህ አማልክት እንስሳት፣እህል፣እቅፍ አበባ እና የደም መስዋዕት ያቀርባሉ።ሃይማኖታቸው እንስሳዊ ነው።በአባይ ወንዝ ምንጭ ላይ ያሉ ነዋሪዎች ወንዙን ያመልኩታል፣እልፍ ከብቶች ደግሞ ለምንጩ መስዋእት ያቀርባሉ። ኮፒ 2. ጋላዎች ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የቅርብ ጊዜ ስደተኞች ናቸው።ጋላዎች እራሳቸውን በጋላስ ስም አይጠሩም ነገር ግን እራሳቸውን ኦሮሞ ብለው ይጠሩታል።በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን እንደኖረ የሚነገርለት ኦሮሞ የሚባል ቅድመ አያት እንዳላቸው ይናገራሉ።ኦሮሞ ኃያል አለቃ ነበረ። ስምንት ወንዶች ልጆችም ነበሩት። ኦሮሞ እና ልጆቹ በመጀመሪያ በአፍሪካ ደቡባዊ ሞቃታማ አካባቢዎች ይኖሩ ነበር እና ተባዝተው ታላቅ ሀገር ሆኑ። እራሳቸውንም ኦሮሞ ብለው ይጠሩታል ምክንያቱም ኦሮሞ ማለት "ጠንካራ ወይም ጎበዝ" ማለት ሲሆን ጋላ ማለት ደግሞ "ወራሪዎች ወይም መጤ" ማለት ነው። .............................................................................. ይህንን ፅሁፍ ከሁለት ዓመት በፊት አውጥቸው ነበር።ፅሁፉን ያወጣሁበት ግዜ የዘመነ #NoMore ዋዜማና እኔም ጁንታነት ማዕርግ የተሰጠኝ ግዜ እነ ዘር ለገበሬ ኢትዮጵያኒስቶች ያየሉበት አምልኮተ አብይም ከአምልኮተ ተዋህዶ. ኦርቶዶክስነት ለብዙው ሰው በልጦ ሰማየ ሰማያት የተሰቀለበት ግዜ ስለነበር ከጥቂት ሰዎች በስተቀረ ጉዳየ ያለው አልነበረም። ፅሁፉ በኦሮሞዎች እንደማይወደድ አው