ትምህርተ ማተብ።

ትምህርተ ማተብ።
"1. ሰባቱ አባቶች
ሀ. ሰማያዊ አባት እግዚአብሔር
ለ. የነብስ አባት
ሐ. ወላጅ አባት
መ. የክርስትና አባት
ሠ. የጡት አባት
ረ. የቆብ አባት
ሰ. የቀለም አባት
2. ሰባቱ ዲያቆናት
ሀ. ቅዱስ እስጢፋኖስ
ለ. ቅዱስ ፊልጶስ
ሐ. ቅዱስ ጵሮክሮስ
መ. ቅዱስ ጢምና
ሠ. ቅዱስ ኒቃሮና
ረ. ቅዱስ ጳርሜና
ሰ. ቅዱስ ኒቆላዎስ
3. ሰባቱ የጌታ ቃላት(እኔ ነኝ)
ሀ. የህይወት እንጀራ እኔ ነኝ
ለ. የአለም ብርሃን እኔ ነኝ
ሐ. እኔ የበጎች በር ነኝ
መ. መልካም እረኛ እኔ ነኝ
ሠ. ትንሳኤና ህይወት እኔ ነኝ
ረ. እኔ መንገድ እና ህይወት ነኝ
ሰ. እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ
4. ሰባቱ ሰማያት
ሀ. ጽርሐ አርያም
ለ. መንበረ መንግስት
ሐ. ሰማይ ውዱድ
መ. እየሩሳሌም ሰማያዊት
ሠ. ኢዮር
ረ. ራማ
ሰ. ኤረር
5.ሰባቱ ሊቃነ መላዕክት
ሀ. ቅዱስ ሚካኤል
ለ. ቅዱስ ገብርኤል
ሐ. ቅዱስ ሩፋኤል
መ. ቅዱስ ራጉኤል
ሠ. ቅዱስ ዑራኤል
ረ. ቅዱስ ፋኑኤል
ሰ. ቅዱስ ሰቂኤል
6. ሰባቱ አቢያተ ክርስቲያናት
ሀ. የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን
ለ. የሰርምኔስ ቤተ ክርስቲያን
ሐ. የጴርጋሞን ቤተ ክርስቲያን
መ. የትያጥሮስ ቤተ ክርስቲያን
ሠ. የሴርዴስ ቤተ ክርስቲያን
ረ. የፊልድ ልፍልያ ቤተ ክርስቲያን
ሰ. የሎዶቅያ ቤተ ክርስቲያን
7. ሰባቱ ተዓምራት
ጌታ እየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈፀሙ ተዓምራት
ሀ. ፀሐይ ጨልሟል
ለ. ጨረቃ ደም ሆነ
ሐ. ከዋክብት ረገፉ
መ. አለቶች ተሰነጣጠቁ
ሠ. መቃብራት ተከፈቱ
ረ. ሙታን ተነሱ
ሰ. የቤተ መቅደስ መጋረጃ
8. ሰባቱ የመስቀሉ ቃላት
ሀ. አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ
ለ. አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው
ሐ. ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ
መ. እነሆ ልጅሽ እናትህ እነሆት
ሠ. ተጠማሁ
ረ. ተፈፀመ
ሰ. አባት ሆይ ነብሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ
9. ሰባቱ ሚስጥራተ ቤተ ክርስቲያን
ሀ. ሚስጥረ ጥምቀት
ለ. ሚስጥረ ቁርባን
ሐ. ሚስጥረ ክህነት
መ. ሚስጥረ ሜሮን
ሠ. ሚስጥረ ተክሊል
ረ. ሚስጥረ ንሰሃ
ሰ. ሚስጥረ ቀንዲል
10. ሰባቱ አፅዋማት
ሀ. አብይ ፆም
ለ. የሐዋርያት ፆም
ሐ. የፍልሰታ ፆም
መ. ፆመ ነቢያት
ሠ. ፆመ ገሀድ
ረ. ፆመ ነነዌ
ሰ. ፆመ ድህነት
11. ሰባቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠሉ ነገሮች
ሀ. ትዕቢተኛ አይን
ለ. ሐሰተኛ ምላስ
ሐ. ንፁህ ደምን የምታፈስ እጅ
መ. ክፉ ሐሳብ የምታፈልቅ ልብ
ሠ. ለክፋት የምትፈጥን እጅ
ረ. የሐሰት ምስክርነት
ሰ. በወንድማማቾች መካከል ፀብን የምታፈራ ምላስ
12.ሰባቱ ፀሎተ ጊዜያት
ሀ. ነግህ (የጠዋት ፀሎት)
ለ. ሰለስት (የ 3 ሰዓት ፀሎት)
ሐ. ቀትር (የ 6 ሰዓት ፀሎት)
መ. ተሰዓቱ (የ 9 ሰዓት ፀሎት)
ሠ. ስርክ (የ 11 ሰዓት ፀሎት)
ረ. ነዋም (የመኝታ ፀሎት)
ሰ. መንፈቀ ሌሊት (የሌሊት ፀሎት)"





  •  
    Shared with Public
    ድንግል።

     

    አስተያየቶች

    ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

    ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

    እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

    አብይ ኬኛ መቅድም።