ልጥፎች

ህሊናዊነት ሲያቃትት በአንድአፍታ ሚዲያ። #ጠና #ያለ #መርኃዊ #ሙግት በፓርቲ አወቃቀር። 14.12.2020

ምስል
  ህሊናዊነት ሲያቃትት በአንድአፍታ ሚዲያ። #ጠና #ያለ #መርኃዊ #ሙግት በፓርቲ አወቃቀር።    #እፍታ ። ከትናንት በስቲያ ዕለተ ቅዳሜ ይመስለኛል የኦህዴድ ልሳነ ምድር አንድ አፍታ ሚዲያ አንድ አሽሙራዊ ሀተታ በአቶ ልደቱ አያሌው ላይ ሠርቷል። አርብ ተፈተው ማለት ነው። ሰውነት ከገዳዊ መንፈስ ባልጠብቅም ገረመኝ። አቁነጠነጠው ማህበረ ኦሮሙማ። አሽሙሩ "ትዕቢቱን አስተነፈስነው፣ ቀመሳት ዓይነት ነው" በማን ላይ ቁመሽ ነው ነገሩ። "መደመር" የመድሎት ቅጂ፣ "መደመር" የሦስተኛ አማራጭ መንገድ ተቀረጣጥፎ፣ በኮፒ ራይት ዝርፊያ ተወራርዶ ስለመሆኑ የፖለቲካ ሊቃናቱ ሲናገሩት ቆይተዋል። የምናዬውም ይኽው ነው በቃላት ቢሽሞነሞንም። አሁን እንኳን የዚህ ሁሉ ድቀት መሠረቱም አንድ ኃላፊነት የሚሠማው ሙሉ መንግሥታዊ አካል በብዙ ወዘተረፈ ባለሙያ የሚያሰናዳውን በአንድ ሰው የህሊና ቅባዕነት መንጭቶ የሽግግር ሰነድ ተዘጋጅቶ የሚቀበለው በመጥፋቱ ነው። ለእናንተ ለማህበረ ኦሮሙማ ቀላል ነው የዚህ ሁሉ ህዝብ ሞት፣ ስደት፣ የአገር ኃብት ውድመት፣ የቂም በቀል መፈልፈል፣ የሥነ - ልቦና ጉዳት። ጨካኞች። ወደ ቀደመው ምልሰት ሳደርግ ዘመንን አንብበው ጉዳት በሚቀንስ መልኩ፣ በትንሽ የመሸነፍ ኪሳራ አገር እንዲተርፍ ሰነድ ተዘጋጄ። ለሽ ብሎ የባጀው ሁሉ ባትቶም መሰናዶ ጀመረ የፋክክር በሚመስል መልኩ። … ያ ብቁ፣ ብጡል፣ ጥበብ ህሊና ደግሞ የአቶ ልደቱ አያሌው ነው። አሁን ያ ዝርክርክ፣ ያ ዝልግልግ፣ ያ ዝርግፍግፍ የኦህዴድ የትቢት ግብረ ኃይል ከአቅም ተቆጥሮ ለእሱ ጥብቅና መቆም ዝልብነት ነው። ምን አለውና ኦህዴድ? ቢነሳ ቢወደቅ አንድ ሰው ነው ያለው፣ ያም አንድ ቀን የታሰበው በሌላው ቀን በጥሰት መጪታ ሲያሽካካ፣ ሲያ

#ህልውና እንዴት ይቀጥል? #መቅድመ ሟተት። 14.12.2019

ምስል
  #ህልውና እንዴት ይቀጥል? #መቅድመ ሟተት።   የአማራ እና የአማራ መንፈሶች፣ የአማራ እና የአምርኛ ቋንቋ ወዳጆች፣ የአማራ እና የአማራ ወዳጅ ብሄረሰቦች ህልውና እንደምን ይቀጥል? የአማራ ትውፊት፣ ታሪክ፣ ባህል፣ ወግ፣ አስተሳሰብ፣ ጥሪት እንደምን ይቀጥል? በኽረ አጀንዳው ይህ ነው። ኦሮምያ በአንፃራዊ ጭፍጨፋው ቆሞ ወለጋን ሳይጨምር ቬንሻጉል ላይ ያለው የዘር ነቀላ ዘመቻ መንግሥታዊ ሆኖ ቀጥሏል። ጋንቤላ የተዳፈነ መከረ አለ። አንድ ቀን ይፈነዳል። የሳቢያ ቀውስ ይደራጅለት እና ቀስቱ በአማራ እና በአማራ ወዳጆች እሳት ለብሶ እሳት ጎርሶ ይስተናገዳል። ጠብቁት። #ውቅረ - ሂደት፣ ለቅሶ፣ ድንኳን ተከላ፣ ቹቻ እና ሰኔል ዛሬ ላይ ወግድልኝ እዬተባለ ነው። ይህን ማስቆም ዬሚቻለው በዓለም ዓቀፍ ህግ ብቻ ነው። ህወሃት ስለተወገደ የአማራ እና የወዳጆቹ ህልውና ተረጋገጠ ማለት አይደለም። የ50 ነቀርሳ ከእነ መርዝ አከፋፋዮች ጋር አብሮ አለ። በውስጥ የጣዖቱ ምስረታ እና ፅናት ህሊና ውስጥ አለ። ኢብን ህገ መንግሥቱ ሙሉ ለሙሉ ቢሰረዝ ሙሉ ፈውስ አይገኝም። መርዙ ከደም ጋር ተዋህዷል። እሰቡት የሰኔ 15/2011 የጠቅላዩን ንግግር ዓለም ዓቀፋዊ ዘመቻ፣ እሰቡት የባልደራስ ምስረታ እና የጠቅላዩ በሰጨኝን። በሰጨኝ በጠቅላይ ሚኒስተርነት ላለ አያምርም ብዬ በወቅቱ ፅፌያለሁኝ። ጠቅላዩ ምን ሲሆን ደማቸው ይፈላል፣ ቱግ ይላሉ ቢባል ነገረ አማራ ሲነሳ ብቻ። ከጠቅላይነታቸው በፊት መንፈሳቸው ርህርህና የዘለቀው ሰውነት ነበራቸው። ቃናው እራሱ አይጠገብም ነበር። የአኖሌ ሃውልት መሥራችነታቸውን ቸል ትሉት ዘንድ ያስገድዳል። #ፍትኃት ከአሰኜ። ፍትኃት ካማረ መፍትሄው ከላይ እንደጠቀስኩት በታሪክ ጉዳይ፣ በህግ ጉዳይ፣ በሰባዕዊ መብት ጉዳይ የሚያተኩሩ ቅኖች ሰብሰብ ብለ

"መተከል ዞን አማሮችን አርደው እጃቸውን አድርቀው የጉምዝ ከበሮ መምቻ አድርገውታል" (ያለለት ወንድዬ፦ ጋዜጠኛ)

ምስል
  "መተከል ዞን አማሮችን አርደው እጃቸውን አድርቀው የጉምዝ ከበሮ መምቻ አድርገውታል" (ያለለት ወንድዬ፦ ጋዜጠኛ) ~~     ለመስማት ለማሰብ የሚከብድ ግፍ በመተከል ዞን (የቀድሞው የጎጃም ክፍለ ሀገር አካል አሁን ወደ ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የተካለለ) እየተፈፀመ ነው። እናት አይኗ እያዬ ልጇ በፊቷ እየታረደ በጉምዝ ታጣቂዎች ሲበላ ታያለች፣ አባት ልጆቹ ታርደው ደማቸው እየተቀዳ እንዲጠጣ ሲደረግ ይመለከታል፤ በተራው እሱም ታርዶ ጉበት እና ኩላሊቱ ለሰው መሳይ ሰው በላ ፍጡሮች አሳልፎ ይሰጣል። ህፃናት በመርዘኛ ቀስት ተወግተው ተነፋፍተው እንዲሞቱ ይደረጋል፤ አልያም እምብርታቸው ከጀርባ አጥንታቸው ጋር በቀስት ተሰፍቶ ይሞታሉ፣ ሌሎቹ በህይወት እያሉ ብልታቸው፣ ምላሳቸው እና ጡታቸው ይቆረጣል። "መተከል ዞን ቡለን ወረዳ ኤቆንጢ ቀበሌ ዛሬም ንፁሃን በግፍ ታርደዋል። በአከባቢው ታዋቂ የሆነ አንድ የሽናሻ ብሄር ተወላጅ እና አምስት አማራዎች በግፍ ታርደዋል። የሽናሻው ወንድማችን አስከሬን ብቻ ሲገኝ የተቀሩት አስከሬኖች መበላታቸውና ቅንጥብጣቢ ቅሪት ብቻ መገኘቱን ከስፍራው መረጃ ደርሶኛል።" የሚለን ጋዜጠኛ ያለለት ወንድዬ በመተከል ዞን በየቀኑ በአማካኝ 40 እና 30 አማራ እየታረደ እንደሚበላ ነግሮናል። በቤንሻንጉል ጉምዝ መተከል ዞን ሰው እያረዱ የሚበሉ ሰው በላ ፍጡሮች ሰው የሚበሉት ለፖለቲካ ብለው ሳይሆን ቀይ መግደል እንደ ጀግንነት ስለሚቆጠር፣ የቀይ ሰው ደም መጠጣት፣ ኩላሊት እና ጉበት መብላት ከበሽታ እንደሚያድን ስለሚታመን እና የቀይ ሰው አካላትን ተቃርጦ መብላት ሙሉ ሰው እንደሚያደርግ ስለሚታሰብ ነው። ይህን የጭራቆች አመለካከት ተጠቅመው አማራን ከመተከል ዞን (ከርስቱ) እንዲጠፋ ለማድረግ የሚሰሩ አማራ ጠል ፖለቲከኞች

እርገት ላይ ስለለው ኮሮና - በኢትዮጵያ። #እፍታ። 14.12.2019

ምስል
  እርገት ላይ ስለለው ኮሮና - በኢትዮጵያ።   #እፍታ ። ስለ ኮሮና መከላከል ማሰብ ቅንጦት ይመስለኛል። ከአዕምሮ ከተሰደደ ቆዬ። * በጥሞና ብታነቡት ስል በትህትና ለቅኖች አሳስባለሁኝ። #ትርታ - በፋታ። በሸኜነው ሳምንት እማከብራቸው ዶር ልያ ታደሰ ብቅ ብለው በኮሮና ዙሪያ ያለው ጥንቃቄ ማነስ፣ ማገገሚያ ክፍሎች እዬሞሉ ስለመሆኑ ገልጠዋል። አስፈሪ የሆኑ ጭንቀታቸውን ነግረውናል። በፈጣሪ ቸርነት እንጂ እንደ ሁሉም ነገር ድብልቅልቅነት የሚተርፍ ነፍስ በኢትዮጵያ ቢኖር የጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ ካቢኔ ብቻ ነበር። ያው እሳቸው እና ባለቤታቸው የማስክ ሞድም ላይ ናቸውና። ሌላው የደን ተከላው ኮሮናን ሊከላከል እንደሚችል እኮ አዳምጠናል። ይህም ብቻ ሳይሆን የሰኔው፣ የጥቅምቱ ግርግር ኮሮናን ዌልካም ያለ ፕሮጀክት ነበር። በአርቲስት ሃጫሉ ግድያ ከአዲስ አበባ ጀምሮ በመላ ኦሮምያ ያን ያህል መሬት እዬተደበደበ ማዕት አውርድ ሲባል፣ በርከት ያሉ ወገኖች በገፍ ሲዘርፍ፣ ሲያዘርፍ፣ ሲገድል ሲያስገድል፣ ሲያሳድድ፣ ሲሳዳድ፣ ሲያነድ፣ ሲያወድም፣ ሲነቅል፣ ሲያፈልስ ኮሮና ኢትዮጵያ ውስጥ ተኖ ወይንስ አርጎ ይሆን? የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፍወርቂን ጉብኝት አስመልክቶ ስለወጣው ህዝብስ ምን እንበለው? ሌሎችንም የድጋፍ ሰልፎችን በገፍ አይተናል፣ ካለ ጥንቃቄ። በተፈጥሮ አደጋ፣ በአንበጣ፣ በጎርፍ በውኃ ሙላት ኢትዮጵያ ስትናጥ ስለቅድመ ጥንቃቄ አጀንዳ ነበርን? ጦርነቱን አቶ ሴኩትሬ እኛው ጀመርነው ብለውናል። ብዙ ድካም ስላቃለሉ እኔ አመሰግናቸዋለሁ። ዳግሚያ ሽሜ ብያቸዋለሁ። እንዲህ ዘርግፍ ደጎችን ፈጣሪ አያሳጣን። ምርኩዝ ሸላሚዎች ወይንም ባትሪዎች። #እም ። … ምንም እንኳን የስሜን እዝ ቀሪ ክፍል ቀድሞ በበራሪ ፁሁፍ የሚገደሉት ዝርዝር ደርሶን ነበር፣ ዝግጅቱ ዓ

የሥርጉትሻ ቅኔወች። ታይታ የጤዛ ጎፈሬ ነው። ቃል የፈጠረው ሰው በቃሉ ውስጥ መኖርን ፈራው - ሳ? የፍቅር ተፈጥሮ ትምህርት ቤት ገብተው ሊማሩት የሚገባ ጥበብ ነው።

ምስል
      በራስ ውስጥ ያለ እርቀሰላም ታማኝነት ነው። ቢያንስ ለራስ ፍላጎት እና ራዕይ ታማኝ መሆን። በመሪነት ውስጥ መታመን ከሌለ ተስፋ አረረ። ውሸት ጣፋጭ የሚሆነው ሃቅን እንደ ጦር በሚፈራ ህሊና ብቻ ነው። የካህዲ ህሊና ደብዳቢው እራስ በራሱ ነው። በመኖር ውስጥ ያለ ድንግልና መታመን ነው። ለዛሬ ብቻ የሚኖር ሰብዕና ለማግሥት የህሊና ስንቅ የለውም። እራሱን ያጣ የነጣ። በሂደት ውስጥ ወጣገባ መኖሩ ላወቀበት የብስለት ማሳ ነው። ለማድመጥ ያልታደለ የአገር መሪ ዕውቀትን የመቀበል መክሊቱ የነፈሰበት ነው። ለአዲስ ነገር ብቻ አትጓጓ፣ እርሾ ለሆነው የቀደመ ፀጋም ትኩረት ስጠው። መነሻ የሌለው መድረሻው መሃን ነውና። ጥልቀት ከሃሳብ ምጥቀት፣ ጥበብ ከማስተዋል ይበቅላል። በእምታ ውስጥ ያለ ምጣዊ አመክንዮ የእዮርን ደጅ የማስከፈት አቅም አለው።  ፍቅርን ሳቅንነት ያለው ፍጡር ለትውልድ ልዩ የምሥራች ነው።ትኖርበት ፍቅርን መሸመትም ማቅናትም አይቻልህም። ምክንያቱም የድንግልና ህፃፅ ሊኖርብህ ስለሚችል።  በቅንነት ውስጥ ያለ ፅኑ ሰላም የሚህል ዓለም የለም። ቅንነት 13ኛው ፕላኔት ነው።  መልካም ሰው ስለሌላው ቀና መንገድ ይጠርጋል፣ ክፋ ሰው ግን መንገድ ለመዝጋት እንቅፋት ሲተክል ውሎ ያድራል።  መደራጀት አቅምን ማማከል ነው። ስለሆነም የአማራ ልጅ መደራጀትን እንደ መደበኛ የህይወቱ ክፍል ማዬት ይኖርበታል።  ቃል የፈጠረው ሰው በቃሉ ውስጥ መኖርን ፈራው - ሳ?   አጭርነት የአስተሳሰብ ድህነት ብቻ ነው። የሰው አጭር የለውም። የተፈጥሮም አጭር የለውም።  በጭንቀት ውስጥ ጭንቀትን ከማስጨነቅ፣ በጭንቀት ውስጥ ሰባዊነትን ማበልፀግ ብልህነት ነው።  ታይታ የጤዛ ጎፈሬ ነው።  ሩቅ ያለ የምሥራች ባለቤቱ ካላወቀበት ይመንናል።  ፈጣሪ የሰጠውን መልካምነት የሰው ልጅ ገደደ

የእዮር አደባባይ ዬታምር ደወል አድማጭ አላገኜም። 14.12.2019

ምስል
  የእዮር አደባባይ ዬታምር ደወል አድማጭ አላገኜም።   በመጋቢት 18 ቀን 2010 የዶር አብይ አህመድ የኦህዴድ ሊቀመንበር የሹመት ዋዜማ አንድ የእዮር ደወል ተደመጠ፣ ልብ ያለው ስላልነበር እኔ በቀንበጥ ብሎጌ ታሪክን አጣቅሼ ፃፍኩበት። በመቀሌ አቅራቢያ ጉዳት ያላደረሰ የመሬት መናጥ ስለተዘገበ። ከዛ ቀጥሎ በጉራጌ ዞን ሦስት ታምራዊ ጉዳዮች በአንድ የጊዜ ዓውድ ተከወነ። ታይቶ የማይታወቅ ዶፍ፣ ተሰምቶ የማያውቅ የሰማይ ጩኽት፣ መሬት ከሁለት የመገመስ ትዕይንት። ይህንንም ኧረ ምን ምልክት ነው ስል ፃፍኩት። ለእህቴም ያስፈራል ስላት አታሟርቺ አለችኝ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሃይማኖታዊ ጉዳይ ወጥታ የአብይወለማ የገዱወአንባቸው ፍቅር ምርኮኛ ስለነበረች። ምልክቱ ቀጠለ እና እንጅባራ ሰማይ ላይ ተንቀሳቃሽ የብሄራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በሰማይ ቤት ተከበር፣ ብዕሬም እኔም ተስማምተን ብራናችን ላይ ኮለምን። መስከረም አምስት የሆነውን አይታችኋል። የዘንድሮ መስቀልም የብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማ የእስር ቀን ቢባል መልካም ነው። ደብረዘይትም በዓሉ ተዘጋ ብፁዕ አባታችንም ታግተው ነበር። ግፋ ጣሪያ ነክቷል። ይህም ብቻ አይደለም አድባራት በጅጅጋ ሲነዱ ያዬ እዮር ቁጣውን እሳት ሰማይ ላይ አዘነበ፣ ይህንንም ፃፍኩት፣ ከዛ በመቀጠል ቤት ከሁለት በደቡብ ዞን ተተረተረ እግዚኦ ብዬ ፃፍኩት። ከዚህ ሁሉ በኋላ ነበር መጋቢት አንድ በልደታ ሌላ ዓለምን በኃዘን ኩርምት ያደረገ፣ አውሮፕላን መሬትን ሰንጥቆ የገባበት መከራ በኢትዮጵያ የተስተናገደው። ያን ጊዜ አብይወለማ አመድ ነስንሰው ሱባኤ ይግቡ ብዬ የፃፍኩት። ፍርኃቴ እዬጨመረ ስለመጣ። አሁን በቅርብ ጊዜ ሽዋ ውስጥ ከተለመደው ውጪ የፀሐይ ብርሐን እንደታዬም አንብቤያለሁ ፌስ ቡክ። ፎቶውም አለ። ጥቅምት እና ለቅሶው ደግሞ ሌላ እዮራዊ ታምር

14,12,2019 ራስን የማዬት ጉዳይ የተዘለለ ይመስለኛል። ጥሞና የመኖር ኦክስጅን ነው።

  ራስን የማዬት ጉዳይ የተዘለለ ይመስለኛል። ጥሞና የመኖር ኦክስጅን ነው። ራስን የማዬት ጊዜ የቀደምት አገርን የማበጀት፣ የመምራት፣ የማሳደግ፣ የማሰልጠን ዓላማ የነበራቸው የፖለቲካ፣ የጥበብ፣ የሃይማኖት መሪዎች መለያ የመኖራቸውም ታላቅ ሚስጢር ነበር። በገለባ ሁኔታ መገለበለብ በበረከተበት በእኛው ቁንጥንጥ ዘመን ደግሞ እራስን የማዬት፣ የመርመር ጉዳይ የነጥብ ያህል ዕውቅና ያልተሰጠው ጉዳይ ነው። ጥሞና የራስን ህይወት ለመምራት እራሱ አስፈላጊ ጉዳይ ነው እንኳንስ ከ100 ሚሊዮን በላይ የሆነን ፍላጎትን አቻችሎ ለመምራት። ልክ እንደ ምግብ፣ መጠለያ፣ ከፈን ሁሉ። ጥሞና የመኖር ኦክስጅን ነው። ይህን ካጣ መኖር ድርቅ ይመታዋል። ዘመናችን በዚህ ምክንያት ድርቅ የመታው፣ መለመላውን የቀረ ግንድ ሆኗል። እግዚኦ። እጅግ የሚገርሙ ብቻ ሳይሆን የሚከረፋ ነገሮችን አስተውላለሁኝ። በፖለቲካ ሊሂቃኑ፣ በማህበራዊ አንቂው፣ በልሳናት በሚዲያዎች አዘጋጅ እና አቀናባሪዎች፣ በኪነጥበብ ሰዎች፣ በሃይማኖት አባቶች ሳይቀር፣ ጊዜ ሰጥቷቸው ተፅዕኖ ፈጣሪ በሆኑትም ሁሉ የሚታዬው የኃላፊነት ቁርጠኝነት፣ ከራስ ጋር ለመታረቅ የዳገቱ ዳጥ መሰረታዊ ችግር እራስን ለማድመጥ፣ ለማረቅ የጥሞና ጊዜ ከመኖር ሰሌዳ መሰረዙ ይመስለኛል። በዚህም ምክንያት እንደ ፈረሰኛ ውኃ ሙላት ግልቢያ ብቻ ሆነ ነገር ዓለሙ። ውጤቱም የሳሙና አረፋ። ማህከነ። አንዳንዱ ሰብዕናው ንግሥና ላይ፣ ሌላው አጥቢያ ደብሩ ላይ፣ ጥቂት የማይባለው ዞጉ ላይ፣ ብዙው አውራጃ ወረዳው ላይ፣ ያላነሰ ቁጥር ያለው በሙያው ውስጥ ተጠልሎ ወጀቡን ሲያዝ ውሎ ያድራል። በዚህ ማህል ትውልድ እና ተስፋ ዕብድ የዘራው አዝመራ ሆነ ዕጣ ፈንታው። ማረን። ከ20/30 ዓመት በኋላ የአደራ ተረካቢው መዳረሻ የት ላይ ይሆን አድራሻው የሚል የተመጣጠነ

ኢትዮጵያ ማለት

ምስል
ኢትዮጵያ ማለት  

፨፨፨፨፨፨፨፨፨ አዳኙ ዐፄ ፋሲልና ቆለኛው ፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ምስል
  ፨፨፨፨፨፨፨፨፨ አዳኙ ዐፄ ፋሲልና ቆለኛው ፨፨፨፨፨፨፨፨፨   ዐፄ ፋሲል እንደ ነገሥታት ልጆች ሁሉ ከአእምሮና ከመንፈሳዊ ትምህርት ጋራ ውሃ ዋና አደን ..... ሲማሩ አድገዋል።ከዚህ ሁሉ ይበልጥ ግን አጥብቀው ይወዱ የነበረው አደንን ነው።አደንም ሲባል በተለይ የሚወዱት ሊያስፎክሩ ከሚችሉት አራዊት ውስጥ አንበሳና ዝኆንን ነው። ከመውደዳቸውም የተነሣ ወደ አደን ሊሄዱ ባሰቡበት ቀን ሌሊቱን እንቅልፍ አይወስዳቸውም ነበር ይባላል።በታሪክ ነገሥታቸው እንደ ተጻፈው ከዕለታት አንድ ቀን ዠግኖችን አስከትለው ወደ ሰሜን የቈላ በረሓ ላደን ሄዱ።   በበረሓም ወዲያና ወዲህ ሲፈልጉ አንድ ባለትልቅ ጥርስ ዝኆን አገኙና በትልቅ ጨሬ (ረዥም ጦር) ከእልቀቱ ላይ ፈለሙት።ቀጥሎም ሩጫ ቢዠምር በፈረሳቸው ላይ እንደ ሆኑ ደግመው በወጉት ጊዜ ዝኆኑ ደም እያበረረው ወደ በረሓ ገብቶ ላይን ጠፋ።ንጉሡ ዐፄ ፋሲልም የተንጠባጠበውን የደም ምልክት እየተከታተሉ ካሽከሮቻቸው ተለይተው ብቻቸውን በግልቢያ ዝኆኑን ይፈልጉ ዠመር።ነገር ግን ዝኆኑ ድቡሽትና ረግረግ ባለበት ሥፍራ ስለ ሄደ የደሙን ምልክት ለመከታተል አልቻሉም ።ለመከታተልም ቢችሉ የረግረጉ ሥፍራ ፈረሳቸውን እስከ ለኮው ድረስ እየዋጠ መሄድ አቃታቸው። ቢሆንም ካንዱ ማጥ ወዳንዱ ማጥ ሲደርሱና ባሳር በመከራ ሲወጡ በመጨረሻው መግቢያ መውጫው ወደማይታወቅ ጭው ወደአለ በረሀ ገቡ።የመጡበትም መንገድ በፍጹም ጠፍቶ የሚያደርጉት ግራ ገባቸው።ብዙ ሰዓትም ብቻቸውን ዝኆኑን ፍለጋ ትተው መንገድ ብቻ ለመፈለግ ወዲያና ወዲህ ከባዘኑ በኃላ በመጨረሻ ባወጣው ያውጣኝ ብለው ወዳንዱ አቅጣጫ ዝም ብለው ይጋልቡ ዠመር።በዚህ ጊዜ እንዳጋጣሚ አንድ ከበረሓው ጌሾ ቈርጦ (አቤት የበረሀ ጌሾ ለጠላው ለጠጁ .....) ተሸክሞ የሚሄድ ቈለኛ ስላዩ ፈጣሪያቸውን

የፈላስፊት ኢትዮጵያ ፁዑም ቃና፨

ምስል

አጤ ዴሞክራሲ ኢትዮጵያ ምድር ላይ እግር ጥሎህ ያየህ ሰው? ሽው ይለኛልም።

ምስል

#የጭካኔ ታሪክ እኩልነት መፍጠር አቀናባሪው እሳቸው ጠቅላዩ ሲሆኑ የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ልዩ መግለጫ ነው። #ባለፈው ዓመት ልደት እና ጥምቀት "የብልጽግና" ጉባኤ በባህርዳር እና በናዝሬት ነበር፤ ዘንድሮ ጦርነት እና የሊቃውንት ግድያ። በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የጭካኒኔ ግድያ #ምርቅ መሃንዲስ የዓለሙ ሎሬት ባለ ኖቢሉ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ ናቸው። በእኛ በኩል የአቅም #የደም ማነስ ህመም ጎልብቷል። ዘመኑ #መታነቁ በውል አልታወቀበትም። ቱሪዝምን #በምቀኝነት እና በበቀል የሚዩ በመሆናቸው #የሰላም ህውከቱ ፕሮጀክትም ከዚህ አንፃር ነው እኔ የማዬው።

ምስል
#የጭካኔ ታሪክ እኩልነት መፍጠር አቀናባሪው እሳቸው ጠቅላዩ ሲሆኑ የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ልዩ መግለጫ ነው። #ባለፈው ዓመት ልደት እና ጥምቀት "የብልጽግና" ጉባኤ በባህርዳር እና በናዝሬት ነበር፤ ዘንድሮ ጦርነት እና የሊቃውንት ግድያ። በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የጭካኒኔ ግድያ #ምርቅ መሃንዲስ የዓለሙ ሎሬት ባለ ኖቢሉ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ ናቸው። በእኛ በኩል የአቅም #የደም ማነስ ህመም ጎልብቷል። ዘመኑ #መታነቁ በውል አልታወቀበትም። ቱሪዝምን #በምቀኝነት እና በበቀል የሚዩ በመሆናቸው #የሰላም ህውከቱ ፕሮጀክትም ከዚህ አንፃር ነው እኔ የማዬው።    "የቤትህ ቅናት በላኝ።"       በሳቸው ዘመን ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶን በማዋረድ፤ በማቅለል፤ በማገት፤ በመረሸን፤ በማንደድ ባደራጁት ስውር አሸባሪ ተቋማቸው ሲፈጽሙ ቆይተዋል። ይህን በአብዛኛው በኦሮምያ እና በአዲስ አበባ በድፍረት ከውነውታል። አሁን ይህን የጭካኔ ድርጊት ደግሞ አማራ ክልል እኩል ረድፈኛ ይሆን ዘንድ እሳቸው ባሰናዱት ስውር ኃይል እያዬን ነው።   ለዚህ ነው እኔ #አሳቻው ጠቅላይ ሚር እና #አሳቻው #ዘመናቸው የምላቸው። ይህም ብቻ አይደለም አብይዝም #የመቃብር #ሥፍራ ብዬ የፃፍኩት፤ በድምጽም የሠራሁት አራት ዓመት ሆነኝ። ካለፈው ዓመት ጀምሮ ደግሞ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ #ቤርሙዳ ትርያንግል ብያቸዋለሁኝ።   እስልምና እና ክርስትና ለዘመናት በፍቅር ኑረዋል። በሳቸው ዘመን ግን አህቲ ሆነው በኖሩበት በዓት ሽብር አደራጅተው ተቋማቱን አስተጓጉለው፤ ፍርሰት ሸንቁረው፤ ጭካኔ ፈጽመው እራሳቸው ደግሞ ካቢኒያቸውን አሰልፈው ለእስልምና ሃይማኖት ብቸኛው ተቆርቋሪ ሆነው ወጥተው አስተውለናል። እያንዳንዱን ቀውስ በማደራጀት በመም