ህሊናዊነት ሲያቃትት በአንድአፍታ ሚዲያ። #ጠና #ያለ #መርኃዊ #ሙግት በፓርቲ አወቃቀር። 14.12.2020
ህሊናዊነት ሲያቃትት በአንድአፍታ ሚዲያ። #ጠና #ያለ #መርኃዊ #ሙግት በፓርቲ አወቃቀር። #እፍታ ። ከትናንት በስቲያ ዕለተ ቅዳሜ ይመስለኛል የኦህዴድ ልሳነ ምድር አንድ አፍታ ሚዲያ አንድ አሽሙራዊ ሀተታ በአቶ ልደቱ አያሌው ላይ ሠርቷል። አርብ ተፈተው ማለት ነው። ሰውነት ከገዳዊ መንፈስ ባልጠብቅም ገረመኝ። አቁነጠነጠው ማህበረ ኦሮሙማ። አሽሙሩ "ትዕቢቱን አስተነፈስነው፣ ቀመሳት ዓይነት ነው" በማን ላይ ቁመሽ ነው ነገሩ። "መደመር" የመድሎት ቅጂ፣ "መደመር" የሦስተኛ አማራጭ መንገድ ተቀረጣጥፎ፣ በኮፒ ራይት ዝርፊያ ተወራርዶ ስለመሆኑ የፖለቲካ ሊቃናቱ ሲናገሩት ቆይተዋል። የምናዬውም ይኽው ነው በቃላት ቢሽሞነሞንም። አሁን እንኳን የዚህ ሁሉ ድቀት መሠረቱም አንድ ኃላፊነት የሚሠማው ሙሉ መንግሥታዊ አካል በብዙ ወዘተረፈ ባለሙያ የሚያሰናዳውን በአንድ ሰው የህሊና ቅባዕነት መንጭቶ የሽግግር ሰነድ ተዘጋጅቶ የሚቀበለው በመጥፋቱ ነው። ለእናንተ ለማህበረ ኦሮሙማ ቀላል ነው የዚህ ሁሉ ህዝብ ሞት፣ ስደት፣ የአገር ኃብት ውድመት፣ የቂም በቀል መፈልፈል፣ የሥነ - ልቦና ጉዳት። ጨካኞች። ወደ ቀደመው ምልሰት ሳደርግ ዘመንን አንብበው ጉዳት በሚቀንስ መልኩ፣ በትንሽ የመሸነፍ ኪሳራ አገር እንዲተርፍ ሰነድ ተዘጋጄ። ለሽ ብሎ የባጀው ሁሉ ባትቶም መሰናዶ ጀመረ የፋክክር በሚመስል መልኩ። … ያ ብቁ፣ ብጡል፣ ጥበብ ህሊና ደግሞ የአቶ ልደቱ አያሌው ነው። አሁን ያ ዝርክርክ፣ ያ ዝልግልግ፣ ያ ዝርግፍግፍ የኦህዴድ የትቢት ግብረ ኃይል ከአቅም ተቆጥሮ ለእሱ ጥብቅና መቆም ዝልብነት ነው። ምን አለውና ኦህዴድ? ቢነሳ ቢወደቅ አንድ ሰው ነው ያለው፣ ያም አንድ ቀን የታሰበው በሌላው ቀን በጥሰት መጪታ ሲያሽካካ፣ ሲያ