የሥርጉትሻ ቅኔወች። ታይታ የጤዛ ጎፈሬ ነው። ቃል የፈጠረው ሰው በቃሉ ውስጥ መኖርን ፈራው - ሳ? የፍቅር ተፈጥሮ ትምህርት ቤት ገብተው ሊማሩት የሚገባ ጥበብ ነው።

  

 


በራስ ውስጥ ያለ እርቀሰላም ታማኝነት ነው። ቢያንስ ለራስ ፍላጎት እና ራዕይ ታማኝ መሆን።

በመሪነት ውስጥ መታመን ከሌለ ተስፋ አረረ።

ውሸት ጣፋጭ የሚሆነው ሃቅን እንደ ጦር በሚፈራ ህሊና ብቻ ነው።

የካህዲ ህሊና ደብዳቢው እራስ በራሱ ነው።

በመኖር ውስጥ ያለ ድንግልና መታመን ነው።

ለዛሬ ብቻ የሚኖር ሰብዕና ለማግሥት የህሊና ስንቅ የለውም።

እራሱን ያጣ የነጣ።

በሂደት ውስጥ ወጣገባ መኖሩ ላወቀበት የብስለት ማሳ ነው።

ለማድመጥ ያልታደለ የአገር መሪ ዕውቀትን የመቀበል መክሊቱ የነፈሰበት ነው።

ለአዲስ ነገር ብቻ አትጓጓ፣ እርሾ ለሆነው የቀደመ ፀጋም ትኩረት ስጠው። መነሻ የሌለው መድረሻው መሃን ነውና።

ጥልቀት ከሃሳብ ምጥቀት፣ ጥበብ ከማስተዋል ይበቅላል።

በእምታ ውስጥ ያለ ምጣዊ አመክንዮ የእዮርን ደጅ የማስከፈት አቅም አለው። 

ፍቅርን ሳቅንነት ያለው ፍጡር ለትውልድ ልዩ የምሥራች ነው።ትኖርበት ፍቅርን መሸመትም ማቅናትም አይቻልህም። ምክንያቱም የድንግልና ህፃፅ ሊኖርብህ ስለሚችል።

 በቅንነት ውስጥ ያለ ፅኑ ሰላም የሚህል ዓለም የለም። ቅንነት 13ኛው ፕላኔት ነው።

 መልካም ሰው ስለሌላው ቀና መንገድ ይጠርጋል፣ ክፋ ሰው ግን መንገድ ለመዝጋት እንቅፋት ሲተክል ውሎ ያድራል።

 መደራጀት አቅምን ማማከል ነው። ስለሆነም የአማራ ልጅ መደራጀትን እንደ መደበኛ የህይወቱ ክፍል ማዬት ይኖርበታል።

 ቃል የፈጠረው ሰው በቃሉ ውስጥ መኖርን ፈራው - ሳ? 

 አጭርነት የአስተሳሰብ ድህነት ብቻ ነው። የሰው አጭር የለውም። የተፈጥሮም አጭር የለውም።

 በጭንቀት ውስጥ ጭንቀትን ከማስጨነቅ፣ በጭንቀት ውስጥ ሰባዊነትን ማበልፀግ ብልህነት ነው።

 ታይታ የጤዛ ጎፈሬ ነው።

 ሩቅ ያለ የምሥራች ባለቤቱ ካላወቀበት ይመንናል።

 ፈጣሪ የሰጠውን መልካምነት የሰው ልጅ ገደደው።

 የሰው ልጅ ሥጦታው ፈጣሪ/ አላህ የሸለመውን ዓውደ ጊዜ ለቸርነት ቢያውለው ፕላኔታችን ፊቷ አይበልዝም ነበር።

 በመከፋት ውስጥ ያለ ቸርነት ምርቃት ነው፣ ችግር ውስጥ እያለ ስለሰው ልጅ እንግልት የሚባዝን የትውልድ አብነት ነው።

በሰው ህይወት ከገባህ ጥንቃቄ ይኑርህ፣ ጥንቃቄ ከጎደለ ሰበቡ የዛን ሰው ጠቅላላ መዋለ ዕድሜ ከንቱ ሊያደርገው ይችላል እና።

ሚዛን ያለው ጊዜ ብቻ ነው።

የፍቅር ተፈጥሮ ትምህርት ቤት ገብተው ሊማሩት የሚገባ ጥበብ ነው።

የፍቅር ተፈጥሮ ረቂቅ ንጥረ ነገሮች የሰከኑበት ነው። ስለሆነም እንደ ማህበራዊ እና ተፈጥሮ ሳይንስ ሊመረቁበት የሚገባ የዕውቀት ዘርፍ ነው።

በፍቅር ተፈጥሯዊ ህግጋት ፕላኔታችን መምህር፣ ኤክስፐርት፣ ሳይንቲስት፣ ፈላስፋ ስሌላት ለእኔ ፕላኔታችን አንገት ያልተሰራለት ሰው መስላ ትታዬኛለች። 

ውዷ ፕላኔታችን ልዕልት መሬት አንድም ቀን በፍቅር ተፈጥሯዊ ህግጋት ላይ አጀንዳ ኑሯት አያውቅም። ስለዚህም ነው አስፈሪ የሆነችው።

ንግሥት መሬት በፍቅር ተፈጥሯዊ ህግጋት ተኮር መጋዝን፣ የራዲዮ እና የቴሌቪዥን መደበኛ ፕሮግራም፣ ጋዜጣም ኑሯት አያውቅም። ስታሳዝን።

ፍቅራዊነት LoveIsm
ከተቃራኒ ፆታዊ ግንኙነት በላይ የሆነ መኖርን ለማኖር የተፈጠሩ የእግዚአብሄር የአላህ ፍጡራን ሁሉ የውስጥ
እርቀ - ሰላም አስከባሪ ፍልስፍና ነው። ደስታን የሚያስገኝ ነገሮች፣ ዕይታዎች፣ የእግዚአብሄር በረከቶች ሁሉ በህብረት የከተሙበት። አዲስ ቀለም። አዲስ ቀን። አዲስ ልሳን።
አዲስ መኖር፣ አዲስ ድንቅ ነገር ነው።
 
 

ፍቅራዊነት LoveIsm
የትምህርት ካሪክለም ሊነደፍለት ይገባል። ልጆች ከመዋለ ህፃናት ጀምሮ ሊማሩት ይገባል። ሊመረቁበትም ይገባል። ማሽን አምላኪ ትውልድ እንዳይኖር ዓለም ሊያስብበት ይገባል። ፍቅራዊነት እንደ ኮመን ሳብጀክት በትምህርት ቤት መሰጠት ብቻ ሳይሆን ወላጆች በቤት ውስጥ ሚኒ የውይይት መድረክ ሊያሰናዱ ይገባል።
 
ማህበረሰቡ የፍቅራዊነት ተፈጥሯዊ ማህበራትን በመፍጠር ትውልዱን አስተካክሎ የማብቀል ግዴታ ይኖርበታል። ለልጆች አንድ ዛፍ ሲተክሉና ሲነቅሉ ያለውን የመኖር ውበት በተግባር መሬት ላይ ማስተማር ይገባል። ለዚህ መዳህኒቱ ዓለማችን በፍቅራዊነት ተፈጥሮ ላይ አትኩሮት እንድታደርግ ዓለማችን የማዘዣ ጣቢያ የላትም። ለእኔ የመኖር የማዘዣ ጣቢያ ትውልድን የፍቅርን ተፈጥሯዊ ወተት መግቦ ማሳደግ ነው።
 
ፕላኔታችን ልዕልት መሬት በፍቅራዊነት LoveIsm ላይ ያተኮረ ዝክረ ትውፊት የላትም። ሙዙዬም የላትም። የምትናገረው ታሪክ የላትም። ያሳዝናል።
 
 
ንግሥት መሬት አንድም በፍቅራዊነት LoveIsm ላይ ዕውቅና የሰጠ ተቋም የላትም። ጭራሽ አስባውም አታውቅም።
ይልቅ እሷ ዘመን ሰጥ የሆኑ የክፋ እሳቤ መፈልፈያ የሆኑትን ፋሺዝም፣ ናዚዚም፣ ስታሊኒዝም፣ ቴሬሪዝም እያሉ ብቅ የሚሉትን ታስታም፣ መዳኛዋን፣ ፈውሷን ረስታ። ነገ ደግሞ በአዲስ ሥም ከች ይልላታል ተፈጥሮን የሚጣላ የሚያቃጥልም።
ለዛ ቪሊዎን ዶላር እያወጣች መከላከያ ታምርት። ልዕልቷ ብታውቀበት ልጆች አፍ መፍታት ሲጀምሩ የፍቅር ተፈጥሮ ህግጋት ማስተማር ብትጀምር በብዙ ሁኔታ የተሻለ ሞራላዊ ትውልድ መገንባት በቻለች ነበር። ስጋት እና ጭንቀትም ድርቅ በመታቸው ነበር። 
 
 ትውልድ ግዴታውን የሚወጣው የግዴታውን ጣሪያ እና ግድግዳ ሲያውቅ ብቻ ነው። ለዚህ ደግሞ ለአገሩ ህገ መንግሥታዊ ድንጋጌ ባይታዋር እንዳይሆን ማድረግ ነው።
 
 
 
 

ሥርጉተ©ሥላሴ
14.12.2019
Sergute©Selassie

 

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።