ልጥፎች

የተፃፈው ሁሉ እየሆነ ነው || ዶ/ር አብርሃም አምሃ

ምስል
ፈቃዱ ዛሬ ነበር። ቤቴ ውስጥ የተከወነውን ልክደነው። ዊዝደም ለናፈቃችሁ የዕውቀትም የርጋታም የኔታን እንሆ። መጨረሻ ላይ አለቀስኩ። ስለእኛም ስለኢትዮጵያም። በርቀት ስለ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራም አሰብኩ። ሥርጉትሻ ደህና እደሩልኝ። ሰላም ካደርኩ ነገ አገኛችሁአለሁ። 11.06.024

ይድረስ ለኢትዮጵያ ሰባዕዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር ክቡር ዶር ዳንኤል በቀለ፦ ይድረስ ለሰባዕዊ መብት ተሟጋች ክቡር አቶ ያሬድ ኃይለማርያም፦

ምስል
  ይድረስ ለኢትዮጵያ ሰባዕዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር ክቡር ዶር ዳንኤል በቀለ፦ አዲስ አበባ። ይድረስ ለሰባዕዊ መብት ተሟጋች ክቡር አቶ ያሬድ ኃይለማርያም፦ ካሉበት። "የቤትህ ቅናት በላኝ።"     ጉዳዩ፦ የሰማዕቱ ኢሳያስ በላይ ቤተሰቦችን እና አብረው እስረኛ ስለሆኑ ጓዶቻቸው #ቀጣይ #ሕይወት ይመለከታል። አሁን በመረጃ አቀራረብ ጥራቱ እና ቅልጥፍናውም፦ በሚዛናዊነት አቅሙም ተስፋ ከማደርግበት ሚዲያ አንዱ ኢትዮ ኒዊስ ነው። ከደማችን ጋር እንዲዋህድ በተገደድነው #ዘወትራዊ " #ሰበር " #አስደንጋጭ ዜና እንደ ተለመደው በዛሬ ኢትዮ ኒዊስ ረፋድ ዜና ደነገጥኩኝ። ሰውነቴም #ተንዘፈዘፈ ። መቀመጥ ተስኖኝ ጋደም ብዬ ነው የምጽፈው።   ሰማዕቱ ሟች አቶ እያሱ በላይ አሰቃቂ በሆነ ድብደባ እና ዘለፋ በታከለበት ሁኔታ ህይወታቸው ማለፋን የእሥር ቤት ጓዶቹ መሠከሩ ይላል ዘዬዘገባው ዕድምታ። #አስፈሪው ጉዳይ ተረኞች ሊኖሩ እንደሚችሉም #ዛቻ እንደሚደርስባቸው የእስር ጓዶቻቸው ገልፀዋል ይላል ኢትዮ ኒውስ በስደት ባለበት አገር አሁን በሰማሁት ዘገባ።   #ህም ! #አማጥኩኝ ።   1) እነኝህ ዛቻ ስንቃቸው እንዲሆን የተገደዱት እስረኞች ለቀጣይ ህይወታቸው ማን ዋስትና ይስጥ? እንዴትስ ማፍትሄ ማግኜት ይቻል ይሆን? 2) ቁጥራቸው በውል ለማይታወቀው የአማራ ህዝብ ሊቃናት እና ሊሂቃን እስረኞች በቀጣይ እንደምን ጥበቃ ሊደርግላቸው ይችል ይሆን? ስጋቴ አይሏል። 3) በሻለቃ ናሆሰናይ ጉዳይ የታሰሩት ባለፈው አጭር ዘገባ በመንግሥት የተሠራባቸው ወገኖች እና እስሩም በዚህ ዙሪያ ከቀጠለ ልቁን ጭካኔ ማን ሊገድበው ይችል ይሆን?   4) የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መጠናቀቁ ሆነ መቀጠሉ መቼ ነው ይፋዊ መግለጫ በጠሚር አብይ መንግሥት አገዛዝ የሚገ

ከስቃይ ወደ ሰላም የሚወስድ እውቀት | ዶ/ር አብርሃም አምሃ እና ገነት አህፈሮም | Manyazewal Eshetu...

ምስል

የኢትዮጵያ ፖለቲካ መለያ ባህሬ #ስስታምነት ብቻ አይደለም #ቆንቋነትም።።

ምስል
  የኢትዮጵያ ፖለቲካ መለያ ባህሬ #ስስታምነት ብቻ አይደለም #ቆንቋነትም። ። "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሶሻሊዝምን ርዕዮት መከተል ከጀመረበት ጀምሮ ስስታም የሆነ ይመስለኛል። ባለፈም ቆንቋነነት። ከስስታምነት ያለፈ #ስግብግብነት ። ተዳብለህ በተወሰነ ደረጃ ህሊናህ የሚልህን አድምጥ እንኳን አይፈቀደም። #ልጠቅልልህ ፤ #ልሰልቅጥህ የተሰጠህ ህሊና በእኔ ቁመና ከሆነ ይሁን በስተቀር ቆልፈህ ተቀመጥ። የአንተ ህሊና በእኔ ህሊና ይመራ ነው መከራው። ይህ የሁሉም የፖለቲካ ድርጅቶች በሽታ ሲሆን ወታደሮች ደግሞ ደጋፊወች ናቸው። አይታወቃቸውም እንጂ ሳይለንት ዲስክርምኔሽንም ነው። በራሱ ህሊና ሊመራ የወሰነ፤ አለኝ የሚለው የራሱ የሆነ ነገር ያለው ባይፈጠር ይሻላል። ተረባርበው ድራሹን ያጠፋታል። ይህ ስልጣን ላይ ሆነ ስልጣን ላይ አልሆነ የሁሉ ድዌ ነው። #ወረርሽኝ ። አሻም ያሉ እንደ እኔ አፈንጋጮች ህሊናቸውን ያላከራዩ ወይንም ያልገበሩ በውራጅ ማንነት ፋንታዚ ያለቀዘፋ ወይንም የማይቀዝፋ በስውር እስከ ቤተሰባቸው ይመነጠራሉ። ከእስር ሳንፈታ እናልፋለንም። እስሩ ቤት ለቤት ስለሆነ ብቻችን እንዳአዝን ይሆናል እምናልፈው። በዚህ መሰል ህይወት ለመጣው ለሄደው ያላደገደጉ የእኔ መሰል መከረኞች አሉ። ትልቁ ፀጋቸው ግን በነፃነታችው ልክ መኖርን ፈቅደው ማሸነፋቸው ነው ሳይገብሩ። ስለዚህም ኢትዮጵያ ጥሪ ይዘው ከሚወለዱ ልጆቿ በረከት #እዬተነፈጋት አሁን ካለችበት ደርሳለች። በጥንት ዘመን በ13ኛው መቶ ክ/ ዘመን ጎንደር ያደገው በሊሂቃኑ፤ በሊቃናቱ የመጠቀም ደንበር የለሽ መብት ስለነበረ ነው። እኔ ሳድግም የጎንደር ትውፊቱ ብልህ ሰው ከተገኜ ወደ እትብቱ ወደ ተፈጠረበት እንዳይሄድ #በጋብቻ ይያዛል። የጎንደር ስልጣኔ ሁለገብነቱ