#ድርድር እና የሰው ልጅ። ሕይወት #አናጋሪም #ተናጋሪም፤ #አናባቢ #ተነባቢም ና
#ድርድር እና የሰው ልጅ። ሕይወት #አናጋሪም #ተናጋሪም ፤ #አናባቢ #ተነባቢም ና ት። (ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱) "የሰው ልጅ መንገድ ያዘጋጃል እግዚአብሄር ግን አካሄዱን ያዘጋጃል።" እጽዋት ቅኖች ናቸው። ቅን ባይሆኑ ፍሬ ሳይሆን ትል ያፈሩ ነበር። እኛስ???? ድርድር የፈጣሪ ሥጦታ ነው። ፈጣሪ ሠራሽም ነው ለእኔ። የመኖር ጥበብ ነው። ከቀስት እንድን ዘንድ የመዳንም ምልክት ነው ለእኔ።። ህይወት ድርድር ናት። የድርድርም ውጤት ናት። የሰው ልጅ እና ድርድር አብረው የተፈጠሩ ናቸው። ድርድሩን ስታፈርሰው ቅጣት ይኖራል። አዳም ከፈጣሪ አምላክ ጋር የነበረውን ድርድር አፍርሶ ነው የሃጢያት መርገም የወረደው። አባ አባት ነውና በፍጥሮቹ ስቃይ ደስተኛ አልነበረምና ስቃዩን እንደ ሰው ሆኖ አይቶ ስቅለትን መረጠ። ስቅለቱ የኃጢያትን ግድግዳ ሰብሮ የእርቅ ድልድዩን ትንሳኤን ሰጠን። የዚህ ትርጉም ማመሳጠር የኔ ፀጋ አይደለም። በቁሙ ንባቡ የሰማያዊ ግርማ ሞገስ ድርድር ሂደቱ ከተሰጠን ስጦታወች የመኖር ጥበብ ውስጥ አንዱ ነው። ለድርድር ልኩ ማስተዋል፤ ጥሞና፤ ፀሎት እና ፈቃደኝነት ነው። ሦስተኛው የግጥም መዐሐፌ "ውል" ነው እርዕሱ። #ውል ። የድርድር አስኳል ነው። ውል ላልቶ ሲነበብ ትዝታ፦ ሽውታ ይሆናል። ሽውታም በራሱ ጠብቆ እና ላልቶ ሲነበብ የራሱ ትርጉም አለው። ሽውታ ቅፅበታዊነትንም ያመለክታል እንደማለት። ውል ዘመኑ በትርፍ ስሌት የተመሰጠረ ነው። ወይንም ሰጥቶ በቀበል የእኩልዮሽ መርህ። እናት እና ልጅ ውል አላቸው። እንቁላሉ ሰው ለመን ጽንሱ ሀሌት ካለበት ጀምሮ። በመኖር ውስጥ ውል - ድርድር - ስምምነት የሌለበት፤ ክርክር - ሙግት የሌለበት የመኖር ዘይቤ አይገኝም። ዕብን የሚባሉት እንሰሳት ውሻ፤ ደሮ፤ ፈረስ