ልጥፎች

ካሜራ ለምን ተሰራ?

ምስል
      እንዴት ናችሁ ማህበረ ቅንነት? ይህ እዚህ ሲዊዝ ዙሪክ ውስጥ ሳኡ የሚባል የስደተኛ መጋዚን ነበር። ሚዲያ ግሩፕ የሚባል ቲም ነበር። እዛም ለሶስት ዓመት ያህል ተሳትፌያለሁ። ግን የሠራሁት በነገረ ኢትዮጵያ ነበር። ዛሬ ያሉት የሰባዕዊ መብት ኮሚሽን የተከበሩ ዶር ዳንኤል በቀለን ሥም ታገኛላችሁ ለአቶ እስክንድርም ከዛን ጊዜ ጀምሮ ታግያለሁ። ለማድመጥ ባይፈቅድም። ዕውነት ልንገራችሁ ደክሞኛል። እና አንዳንድ ጊዜ መተራረፊያ የሚሆን ነገር ስሰራ በሰጨኝ የሚሉ ጓደኞች ገጥመውኛል። ግሉባሉ ከፎቶ ውጪ ምን እዬሠራ ነው? ካሜራ ለምን ተሰራ? በዬዓመቱ አድባንስድ የሚሆኑ ቴሌፎኖች ለምን ተግባር ተሰሩ? ኢኒስተግራም ሆነ ሌላው ሚዲያ ሥራው ምንድን ነው? ቪዲዮ ለምን ተፈጠረ? ፎቶ እኮ አርት ነው። የሚሰለጥኑበት ሙያ። ሞድ ኢንደስትሪ ምንድን ነው? ህሊናቸውም፣ መንፈሳቸውም ጥብብ ያሉ ሰብዕናወች ይገርሙኛል። ለዛውም ፕሮፋይላቸው ፎቶ ሆኖ። ምንስ እንደ ቅቤ ያንጨረጭራል? በዘጠኝ ወር አንድ ቀን ቀርቶ በዬለቱ ያሻኝን ብለጥፍ በቤቴ ምን ይጨንቃል። ኦ !ኢትዮጵያ መጥኒ ላንች። እኔስ ዘመኔ እያለቀ ነው። ኖሪቱ አንቺ ግን ታሳዝኚኛለች። ዓይነ ጠባቦች ቤታቸው ቢኬድ ምን ሊሆኑ ይሆን።? ለኦክስጅን ቢያመለክቱ ይሻላቸዋል። አጤ ኦክስጅን ሆይ ለሁሉ ፀጋ የሆነውን ስጦታህን እባክህ ለሥርጉትሻ ንፈጋት ብለው ያመልክቱ። ተረበኞች። በፌቡ በዩቱብ ቻናል ቀደም ባለው ጊዜ በድህረ ገፄ እስካሁን በፀጋዬ ራዲዮ ታገሉ። ፀጋ ሰጩ ተቋቁሞ የበለጠ ዕድል እዬሠጠኝ ኖርኩኝ። በዚህም ተቀጥል። እኔ ፌቡ እኮ እጅግ ዘግይቼ እናቴ ነው ያስጀመረችኝ። ቲኪክቶክ ገብቼ አላውቅም። ሰሞኑን ነው ያስጀመሩኝ። ሳዬው ብዙ አማራጭ አለው። ጥበብ ገፊዋ ብዛቱ። ጠሚር አብይ ጥበብን አሰሩ ብዬ አዝን ነበር። የፌ

ለቅኖች፣

ምስል
      ለቅኖች፣ ለዓይነ፣ ልቦና፣ ዕዝነ ህሊና ሰፊወች እንጂ ለዓይነ ጠባቦች ለቅንጣቷ እንኳን ለሚጠዘጥዛቸው ኩርኩዶች አይደለም። ትንሽ ስለ ደጋግ የሲዊዝ ልጆች። ቤተ እግዚአብሄር በህብረት፣ ሰላማዊ ሰልፍ እና ህዝባዊ ጉባኤ በህብረት አውቶብስ ተከራይተው አገልግሎት የሚሰጡ ቅኖችም አሉን። በጉዞ ወቅት ፈቅጄ ከሄድኩ አንድም ቀን ከፍዬ አላውቅም። በወረፋ ነው የሚከፈልልኝ። የውነት ነው። ለሽያጭ ዕቃ የሚያቀርቡትም በነፃ ነው የሚሰጡኝ። እየሩሳሌም የሚሄዱ በረከቱን ይዘውልኝ ይመጣሉ። ጥፍት ስል ቤቴ ድረስ መጥተው ደህና መሆኔን ጠይቀው የሚሄዱም ቅዱሳን አሉን። የእኛ ፖለቲካችን ነው ያልታረመው። ሰብዕናችን በክፋነት ተክል ኮትኩቶ የሚያሳድገውም ይሄው ነው። ፖለቲካ የውቀት ዘርፍ መሆኑን ባለመረዳት ይመስለኛል። ለማንኛውም የእኔ አቋጣሪ ደጎቼ ሁሉ ኑሩልኝ። አንድ ቀን እንገናኛልን። እሺ። ኑሩልኝ እመ እና አበው። አሜን። ዓለም ዓቀፋ የፎቶ ኤግዚቢሽን በዙሪክ የኢትዮጵያ ውክልና ይህን ይመስል ነበር። ኑሩልኝ። ሥርጉትሻወሰብሊ። 13/06/024

ዓለም ዓቀፍ የፊደላት ቀን ከተመረጡት ባለ ፊደል ቋንቋወች ውስጥ አጤ አማርኛ ቋንቋ አንዱ ነበር።

ምስል
  ዓለም ዓቀፍ የፊደላት ቀን ከተመረጡት ባለ ፊደል ቋንቋወች ውስጥ አጤ አማርኛ ቋንቋ አንዱ ነበር። "የገደል "ማሚቶ" በሚለው ትረካም ላይ አጤው ነበር። የራሱም ዕልፍኝ ነበረው። ታሪክ እራሱን ይቀርጣል። ሥርጉ13/06/024 ኑሩልኝ። አሜን።  

የፀጋዬ ራዲዮ፤ የፀጋዬ ድህረ ገጽ ግብዣ።

ምስል
  የፀጋዬ ራዲዮ፤ የፀጋዬ ድህረ ገጽ ለሲዊዝ የጀርመንኛ ተናጋሪ ክፍላተ አገራት የልምድ ልውውጥ ግብዣ። "አድርገኽልኛል እና አመሰገንኃለሁ።"   ስደተኛ ካንፕ ነበርኩ። ካንፔ ክላይነአንደልፊንገንባድ የሚባል ትንሽዬ ገጠር ከተማ ውስጥ ነበር። ቤቱ የ300 ዓመት ዕድሜ ያለው ይመስላል። ምዕራፍ በሚል ትንሽ ፁሁፍ አለችኝ። ለትረካ የምትሆን። ሲቻል ስዕላዊ ድርሰቱ ሲቀርብ የቤቱ ገፀ ባህሬ ይገለጥላችኋል። አደራጅነት ጥሩ ነው። ሙያውን ማለቴ ነው። እና ቀዝቃዛው ኤክሲሞ፤ ምድረ በዳው ሳህራም ቢሆን ማደራጀት ሸካራውን ልጎ ሐሴት ያስኮመኩማል። እንገዶች ሲመጡ ከተረክሽው ታሪክ ጋር ቤትሽ ግን ይላሉ። ይህ ቤት ግን ከዚህ ህንፃ ውስጥ ነውን ይላሉ። ቀለም መቀባት እወዳለሁ። በዲዛይን። የዛሬን አያድርገውና ቤቴ ሙሽራ ነው እማደርጋት። እረፍት እማልሻውም ቤቴን ቤተ - መቅደስ አድርጌ መኖር ስለምችል ነው። እና በዚህ ህንፃ ኢንተርኔት የለኝም፦ ኢሜል የለኝም። የገዘፈ ስምንት መምሪያ ያለው ድህረ ገጽ፤ ሦስት መምሪያ ያለው ራዲዮ መሰናዶ ግን እመራለሁ በብላቴ ሎሬት ለውለታው ክብር በሥሙ በመሠረትኳቸው ሚዲያወች። ። ለእግዚአብሄሩ ጠረጴዛ እንኳን የለኝም። በቀን ሆም ፔጁ ላይ ዘጠኝ አውዲዮ ያከለ ቴክስት ይለጠፋል። ኮንፒተር እኮ የለኝም። እና ይህ ፕሮጀክቴ ነው "ሚዲያ ሚዲያን ይሠራል" በሚል ሮሜሮ ሃውስ ከቆንጂት ሉዘርን ከተማ በተዘጋጀው ዓውደ ጥናት ልምዴን እንዳካፍል የተጋበዝኩት። ወጩ ተችሎ። ሆቴሉ ተከፈሎ ነው ታዲያ። በጋራ አንድ ዝግጅት ነበር። ከዛ በተመደብልን የመግለጫ ሩም በስላይድ የተደገፈ መግለጫ ነበር። ብዙ እንግዶች ወደ እኔ ክፍል መጡ። የተመድ የዩኒሴፍ መሥራች ቤተሰቦች፤ የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ዘጋቢ ጋዜጠኛ ቤተሰቦች ነበሩ።

አክብሬ አመሰግናችኋለሁ

ምስል
  በዬሰከንዱ እናት አገሬ ከውስጤ ናት። ዛሬም ቢኖረኝ ባደርግላት አልጠግብም። ለሲዊዚሻ ውለታ ሳልከፍል በመቅረቴ ግን እጅግ አዝናለሁ። የሰው ልጅ ሲመረቅ ሲዊዝ ይመጣል። ቅዱስ በዓት። የሰላም አንባ። የህይወት መድህን። ጭምት ሥልጡን። ጨዋ ብቁ። ሰባዕዊ ባለማተብ ውድ ዕንቁ በዓት። በህይወቴ የገጠመኝን የማይገኝ ዕድል ገፍቼ ነው የተገኜሁት። ግን ንጽህናን በይበቃኛል ቃሉ እንደ ቃሉ ገድሞ መኖር። የበሞቴ ልዕልቴ አንድ ጊዜ ፀሎት ያስፈልገኛል አልኳት። "ሱባኤ" ላለ አለችኝ። አወን የሙሉ ዕድሜ የቁጥብነት ህይወት በብዕር ጠብታ ፍቅር ተነድፎ። በታቦቴ በብላቴ ፀጋዬ ገብረ መድህን ፃዕዳ ሩቅ በጣም ርቅ መንፈስን ተጠግቶ። ደፋሮች ይገርሙኛል። መረገምም ይመስለኛል። ታቦቴን ሲዳፈሩት። የሆነ ሆኖ ተመስገን ሲያንስ ነው። ከሰሞኑ በምለጥፋቸው ፎቶወች የተደመሙ ንፁኃን የሚልኩልኝ መልዕክት ፈውሶኛል። በውነቱ ጽናቱን አፍልቆታል። አክብሬ አመሰግናችኋለሁ ውዶቼ ክብረቶቼ። ቀሪው ጊዜ ታምቀው የተቀመጡ ልምዶቼ ምክሮቼ ፀጋወቼን ሁሉ አስረክባችኋለሁ። ኑሩልኝ። ሥርጉ14/06/024 ጥበብ ትጠራለች። ታከብርማለች። ታስከብርማለች። ውደዟት። አትግጿት። ምን አደረገች????

ኦባንግሻን የት አደረሱት???

ምስል
        እዚህ ዙሪክ በሰባዕዊ መብት ዙሪያ ይሠሩ የነበሩ ትጉኃን ነበሩ። እነሱ ስብሰባ ጠርተው ቅድስት ፀሐይ አለችኝ እራሷ ኢትዮጵያ ናት እሷ ጋብዛኝ እሷ ከፍሪቦርግ እኔን ከዙሪክ ለዙሪክ ሰብዓዊነት ጉባኤ። ኦባንግሻን በአካል ያገኜሁት ያኔ ነው። በሥራ አብረን ነበር። ደወል የምትባል ርዕሰ አንቀጽ ነበረቻቸው። በፀጋዬ ራዲዮ በመደበኛ አቅርባት ነበር። አዬ ዶር አብይ ያን ሁሉ ድካም ካለ ሰናፍጭ ታክል ጥረት ጠቀለሉት። ይገርማል። የሆነ ሆኖ ኦባንግሻን የት አደረሱት??? የት ነው ያለው ጠይሙ ዕንቁ??? ዕንቁአችን መልሱ ማህበረ ኦነጋውያን። ግዞትም ከሆነ ይነገረን። ቁርጥ ያጠግባል እንዲሉ። ሥርጉ በህዝባዊ ተሳትፎም ጀርመን ሙኒክ እና ፍራንክፈርት አማይን፤ ዴንማርክን ያካተተ፤ እዚህ ዙሪክ፤ ጀኔባ፤ በርን ጉልህ ተሳትፎ በዘጋቢነት በነጣ አገልግያለሁ። የደጉ ዘሐበሻ እና የሩህሩሁ ሳተናው ድህረ ገጽም ቁጥር የማይወጣላቸው ቋቯሚ አምደኛ፤ ሞጋችም ነበርኩ። ፌቡ እኮ አራት ዓመቴ ነው። ለዛውም በእምዬ ቸርነት ገፋፊነት። የእኔ ጠሐይ። የእኔ ቅን፤ የእኔ ደግ። የእኔ ለጋስ ኑሪልኝ። በራሷ ወጪ በጋዬን ታሳምረዋለች። ከ400 መቶ በላይ ፎቶወቼ የጠሐዬ ነው። የአዲስዬ ዕንቁ ጌጥም። ኑሩልኝ። ሥርጉ14/06/2024 ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው።

መደበኛ ሥራም ጥንቅር በል

ምስል
      ቤት ለመጣ እንግዳ ሥነ ግጥም አይቀሬ ነው። እናታችን ጥንቅቅ አድርጋ ነው ያሳደገችን። ክርክም አድርጋ። ጎንደር ማደግ ጥቅሙ መኖርን በጥዋቱ ትማራለህ። ሴቶች ኮንፊደንሳቸው ያለው ሚስጢርም ይህ ይመስለኛል። ሰባት ዓመት ቀጠሮው የሚጀመርበት ነው። የሴትነት ኃላፊነት እና ተጠያቂነት የፊደል ገበታ ለጎንደሬ። የባላባቶች ደግሞ ወጭታቸው ሞሰባቸው ይለያል። እንግዳ ክብሬ ነው። ለእንግዳ መደበኛ ሥራም ጥንቅር በል ይባላል። ጎንደር እና እንግዳ ቅኔ እና ድጓ፣ ተመስጦ እና ድዋ። ሁሉም አልቀረብኝም። ተመስገን አምላኬ። አሜን። ሥርጉ 14/06/024

የውድድር ተሳትፎ ነው።

ምስል
      የውድድር ተሳትፎ ነው። በቴክኒካል ችግር ምክንያት ባይሳካም የአገሬ የኢትዮጵያ ሥም፣ የባዕቴ የሲዊዝሻም በዛ ታሪክ ውስጥ አሻራ አለው። የሚገርመኝ ፈጽሞ እምለው ነገር አለመኖሩ። ኦ! ትዝ ካለኝ ትናንት አንድ ትሁት ሩህሩህ ወጣት ጋር ቻት ሳደርግ ትጥቅ እንዳልፈታ ሲያበረታታኝ ነበር። ቃል ገብቼለት ነበር። ሰባተኛ "ርግብ በር" መጸሐፌ ጀርባ ሽፋኑ ላይ የተፃፈ ነው። #ፈጽሞ ! ማንነት ያለው ተስፋ ስላለኝ የመንፈስን እስር የመፍታት አቅሙ ፈተና ላይ አይወድቅም። ይልቁንም ማንነት ያለው $መፍትሄ የመፍጠር አቅሙ ጉልበታም ነው። ጉልበታሙ ማንነቴ ወደፊት የሚፈጥረው ግፊትና የሚጨበጥ ራዕዩ ደግሞ ትጥቅ እና ስንቄም ነው። በተሟላ #ስንቅና #ትጥቅ የተሰናዳ ማንነት ደግሞ ጉልህና - አሸናፊ ነው። ከዚህ በኋላ ወይንም ከእንግዲህ ወዲያ በቃኝ ብሎ፣ ለስንፍና እና ለፍርኃት #እጁን #አይሰጥም እና #ፈጽሞ ! ይላል። እና ሰኔል እና ሳጥን ብቻ ነው እኔን የሚያስቆመኝ። በብዙ የጤናም የሀዘንም የፈተና ድባብ አልፌያለሁ። ወጁብም ቁርም ፈትኖኛል። ግን ንፁሁ ቅንነቴ ጠግኖ ይዞኛል። ተመስገን። ሥርጉ14/06/024 ቅንነት ዓራት ዓይናማው መሪዬ፣ የእብዬ የ እናቴ ውርስ ስጦታም።

በእኛነት ላይ ያለው ተፃራሪ መንፈስ ቀድሞ #የተረታ ነው።

ምስል
  በእኛነት ላይ ያለው ተፃራሪ መንፈስ ቀድሞ #የተረታ ነው። "አድርገህልኛል እና አመሰግንኃለሁ።"   አማርኛ ቋንቋን እና የአማራ ሥልጣኔ ኢትዮጵያን በማበጀት ረገድ ያለውን ሚና ለማደብዘዝ ብዙ ተለፍቷል። መንፈስ ቅዱስን የረታ ጥቁር መንፈስ ሆነ ጥቁር ቀን ግን የለም። የትም ቦታ፤ በማንኛውም ሁኔትታ ጠባቂ ሠራዊት አለው በቅንነት ለተከወነ ማናቸውም ጌጥማ፤ ፈርጣማ አሻራ። ትናንት የመጡት ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ የሺህ ዘመናትን ሥልጣኔ ደርምሼ እራሴን ቁብ አደርጋለሁ ብለው ቢታክቱም በአንድዬ ኃይል ቀድመው የተተገበሩ መሠረትም የያዙ መልካም ነገሮች አሉ። ሲዊዝ እጅግ ጭምት ገለልተኛ ቅድስት አገር ናት። በእሷ መሬት እንኳን ይህ ተሠርቷል በአንድ ክንድ። የያዝኩት መፀሐፍ "ፊደል" የልጆች የሥነ ግጥም መጸሐፍ ነው። ልጆቻችን እኛ ባለፍነው ትርምስ ማለፍ ስሌለባቸው እንካ ሥላንትያን እና ፊደልን ከመፃፌ በፊት በሱባኤ ነው። ቅንጣት ክፋ ነገር ሙግት ፖለቲካ የለበትም። የዝናብ ውሃ ጠበል ነው አይደል እንደዛ። ፊደል ሽፋኑ የአማርኛ ቋንቋ አልፋቤት ነው። በእኔ ዕውቀት ልክ ያሉ ነገሮች አሉበት። ሁለቱም የልጆች መፃህፍት መፍቻ አላቸው። ከኦስትርያ የመጣች የጓደኞቼ ቤተሰብ የወለጋ ልጅ ናት ለእኛም ስለሚሆን ለልጆች ለምን አልሽው ብላ ሞግታኛለች። ቅኒት ናት። ባህላችን፤ ወጋችን፤ ልማዳችን ተቀመርበታል። ብዙ የሲዊዝ የኢንተግሬሽን ቤተ መፃህፍቶች አማርኛ ቋንቋ ዲፓርትመንት አላቸው። ታግለናል አሳክተናልም። ለምን? አገራችን በክብሯ ልክ፤ በዊዝደሟ ልክ መቀጠል ስላለባት። ለዛውም ቸነፈሩን ተቋቁመን። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፍልስፍናው ክፋት ነው። ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚታመሱት ለክፋት አጤነት ነው። ግን ሲተኑ እንጂ ሲበቅሉ አላዬሁም። በአማራ

ተዘርፈው

  በተከፋች አገር ውስጥ የሚያድጉ ወጣቶች ሁለመናቸውን #ተዘርፈው ያድጋሉ። ወጣትነታቸውንም ይዘረፋሉ ከሞት ከተረፋ። ይህ ማለት ለምን #ተፈጠራችሁም ነው። ሥርጉትሻ 2024/06/15

#ፋኖ የአማራ ህዝብ የተፈጥሮ #የቀይ ደም #ሴሉ ነው።

  #ፋኖ የአማራ ህዝብ የተፈጥሮ #የቀይ ደም #ሴሉ ነው። እኔም ፋኖ ነኝ። ክብሬን እማላስጠቀጥቅ። ግን የፖለቲካ ድርጅቴ ብዕሬ የሆነ። ፋኖ ያበራል። ተሽሎክሉከን ሳይሆን ገጥ ለገጥ ወጥተን። ተጠማኝ ጥገኛ ሳንሆን እኔም ፋኖ ነኝ እንለዋለን። ውጠነዋል። ስንፈጠር ሳይሆን ስንጠነሰስ ከፋኖ መንፈስ ጋር ነው። መለያችን አርማችን ፋኖነት ነው። እኔ እራሴን ችዬ ፋኖ ነኝ። አንገቴን አልደፋበትም። በብእሬ እሞግታለሁ። ብዕሬ ሃቅን ታበራለች። እኔ አቶ እከሌ ወይንም ወሮ/ እከሊት አይደለሁም። እኔነት በብድር አይሆንም። እኔ እኔ ነኝ። እኔ እራሴም ፋኖ ነኝ። ብዕሬም የቀለም ባሩድ አላት። ይህን ለሁለም እጽፋለሁኝ። ፋኖነት የጊዜ ኩርፍርፍ አይደለም። የቤተሰብ ውርስ እንጂ። አወን እኔ ሥርጉተ ሥላሴ፤ ሰብለ ህይወት ፋኖ ነኝ። መሳሪዬ ሃሳቤ ነው። ድልድዬ ብዕርና ብራናዬ። ፋኖ የፖለቲካ ድርጅት #መጂ አይመራውም። ሲፈጠር በባህሉ፤ በወግ በልማዱ በህግ አምላክን ጠጥቶ የተፈጠረ ነው። በተፈጥሮው ልክ የኖረ ለወደፊትም የሚኖር አልፋ - ኦሜጋ። የአማራ ህዝብ ቀይ የደም ሴል ፋኖነት። "የቤትህ ቅናት በላኝ።" ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 15/06/2023 #ፋኖነት እኔው ነኝ! #ፋኖነት #የክብርት #ኢትዮጵያ #አለኝታነት !

Elias and Tekle, on the disturbing draft proclamation ስለአስደንጋጩ የንብረት መውረ...

ምስል

የባላገሩ ምርጦች በመቄዶንያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን ድርጅት ልዩ ዝግጅት @BalageruTV

ምስል

Balageru Meirt ባላገሩ ምርጥ | ልዩ የኢድ አል አድሃ አረፋ የበዓል ጨዋታ ከባላገሩ ምርጦች ጋር ክፍል 1...

ምስል

ድብድቡ መቼ እንዴት ይቁም።

ምስል
  ድብድቡ መቼ እንዴት ይቁም። "አድርገህኛል እና አመሰግንኃለሁ።"   ክወና ነው። ለምን ማፍራት ተስኖን #ፈሰስን ? #ቀዳዳችን ስለምን በረከተ? #ቦክሱስ መቼ ይቁም? #ክፋነት መቼ ይቀበር? በራስ ላይ መዝመት ከተቻለ ሁለንም ብትክ ጉዳዮች ቀብረን ወደ ቀደመው ዊዝደማችን ጉዞ መጀመር እንችላለን። ዊዝደማችን ለተፈጥሯችን ዕውቅና ሰጥቶ በሱ ውስጥ ለመኖር መፍቀድ ነው። ወጪ አይጠይቅም። ትልም አይጠይቅም። ከራስ ጋር መታረቅ ብቻ ቁልፋን የመፍትሄ ትልምን ያስረክበናል። ስህተት ውስጥ ትናንትም፤ ዛሬም ብቻ ሳይሆን ስህተትን ለማስቀጠል ትጋታችን ሊገታ ይገባዋል። ሁሉም በግድፈት ተነክሮ ነው የኖረው። በሌላ በኩል ደግሞ ሁሉም አለኝ የሚለው አቅም አለው። ለድክመቱ መሻሪያው የራስ ዳኝነት ነው። ለአቅሙ ደግሞ በውጭጭ አቅም ቅንነትን መግቦ አገርን፤ አደራን፤ ትውልድን ማዳን ይገባል። የታሠሩ #እስረኞች ሁሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ሊፈቱ ይገባል። #ተኩስ #አቁም ሁሉም ሊያውጅ ይገባል። አቅምን ንቆ ከመነሳት ለአቅሙ ዕውቅና ሰጥቶ #በልኩ #ትኩረት ሊሰጥ ይገባል። #እላፊ መሄድም አይገባም። ስድብ፤ ማዋረድ፤ ማቃለል ለምን??? መውደቃችን ከውስጥ መቀበል አለብን። በመውደቃችን ልናፍር ይገባል። የሚሠሩ መልካም ነገሮችንም ዕውቅና መስጠት ይገባል። ግን ምንም ዓይነት ሥልጣኔ ከሰው ልጅ ህይወት፤ የመኖር ዋስትና በላይ ሊታይ አይገባም። ፈጽሞ። በጣም ስጋት አለኝ። የአማራን ህዝብ #አቅሎ የማዬት ፖለቲካ። በፍጥነት ሊታረም ይገባል። የሰይጣን ጆሮ ይደፈንና " የአማራ ህዝብ እገነጠላለሁ" ካለ ኢትዮጵያ #ባላ የሌለው ቤት ትሆናለች። የመካከለኛው ምስራቅ ፖለቲካም ሙሉ በሙሉ ይቀዬራል። ብዙ ያልነገርኳችሁ ተሳትፎ አለኝ። ብቻዬን የሠራሁት።