#ፋኖ የአማራ ህዝብ የተፈጥሮ #የቀይ ደም #ሴሉ ነው።

 

#ፋኖ የአማራ ህዝብ የተፈጥሮ #የቀይ ደም #ሴሉ ነው። እኔም ፋኖ ነኝ። ክብሬን እማላስጠቀጥቅ። ግን የፖለቲካ ድርጅቴ ብዕሬ የሆነ።
ፋኖ ያበራል። ተሽሎክሉከን ሳይሆን ገጥ ለገጥ ወጥተን። ተጠማኝ ጥገኛ ሳንሆን እኔም ፋኖ ነኝ እንለዋለን። ውጠነዋል። ስንፈጠር ሳይሆን ስንጠነሰስ ከፋኖ መንፈስ ጋር ነው። መለያችን አርማችን ፋኖነት ነው።
እኔ እራሴን ችዬ ፋኖ ነኝ። አንገቴን አልደፋበትም። በብእሬ እሞግታለሁ። ብዕሬ ሃቅን ታበራለች። እኔ አቶ እከሌ ወይንም ወሮ/ እከሊት አይደለሁም። እኔነት በብድር አይሆንም።
እኔ እኔ ነኝ። እኔ እራሴም ፋኖ ነኝ። ብዕሬም የቀለም ባሩድ አላት። ይህን ለሁለም እጽፋለሁኝ። ፋኖነት የጊዜ ኩርፍርፍ አይደለም። የቤተሰብ ውርስ እንጂ። አወን እኔ ሥርጉተ ሥላሴ፤ ሰብለ ህይወት ፋኖ ነኝ። መሳሪዬ ሃሳቤ ነው። ድልድዬ ብዕርና ብራናዬ።
ፋኖ የፖለቲካ ድርጅት #መጂ አይመራውም። ሲፈጠር በባህሉ፤ በወግ በልማዱ በህግ አምላክን ጠጥቶ የተፈጠረ ነው። በተፈጥሮው ልክ የኖረ ለወደፊትም የሚኖር አልፋ - ኦሜጋ። የአማራ ህዝብ ቀይ የደም ሴል ፋኖነት።
"የቤትህ ቅናት በላኝ።"
ሥርጉተ©ሥላሴ
Sergute©Selassie
15/06/2023

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።