ልጥፎች

ፕ/ ዶር. ፍቅሬ ቶሎሳ።

ምስል
                     ብሩክ ቀን – ሥርጉተ ሥላሴ                   „ … እኔ ግን እግዚአብሄርን እለምን ነበር፥ ነገሬንም ወደ እግዚአብሄር አቀርብ ነበር።                                   ዬማይመረመረውን ታላቅ ነገርና የማይቋረጠውን ተአምራት ያደርጋል። …“                                                 ( መጽሐፈ እዮብ ምዕራፍ ፭ ከቁጥር ፰ እስከ ፱ ) ይድረስ ለኢትዮጲያኒዝም አባት እና የአብሮነት ሐዋርያ ለሆኑት ሊቀ – ሊቃውንት ፕሮፌሰር ዶር . ፍቅሬ ቶለሳ – ባሉበት። ሊቀ – ሊቃውንት ፕሮፌሰር ዶር . ፍቅሬ ቶለሳ እንደምን   ሰነበቱልን ፤ እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ።    „ የኦሮሞና የአማራ እውነተኛ የዘር ምንጭ “   በዚህ በአዲሱ መጸሐፍዎት ዙሪያ ከኢትዮዽያ ኃብታት ከሆኑት ሁለት ሊቀ – ሊቃናት ጋር ያደረጉትን ክርክር ግራ ቀኙን – ታደሜበታለሁ። ከሥር ዬሚታከሉ ዬአንባብያንን አስተያዬትንም በማከል ነበር – ዕድምታዬ። መጸሐፋን ባነበው ዬበለጠ ሊረዳኝ ይችል ዬነበረው በመጽሐፋ ውስጠት ዬግሌን ዕይታ በመንፈስ ሊያጎለብትልኝ ቢችልም፤ አደባባይ ወጥቼ   ዬሃያሳን ሊቃናትን ዬሙያ ድርሻ መጋፋት ተገቢ አለመሆኑን ስለማምንበት ፤ እምለው አይኖረኝም   ነበር።   ስለዚህም ዛሬ ልጽፍ ላነሳሳኝ ጭብጥ   „ የኦሮሞና የአማራ እውነተኛ የዘር ምንጭ “   መጸሐፍ አለማንበቤ ዬሚያጎድለውም ሆነ ዬሚሞላው ምንም አይነት አመክንዮ አይኖረውም። ጠብታ። ውስጤን ለውስጤ