"#ሁለገብ ትግል" እና ትውልዱ።
" #ሁለገብ ትግል" እና ትውልዱ። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። የማከብራችሁ የአገሬ ልጆች እንዴት አደራችሁ? #ምዕራፍ ፲፯ "የሁለገብ ትግል" መሠረተ ሃሳብ ጠንሳሹ ግንቦት 7 ነበር። በዛ ዘመን "ሁለገብ" የሚለው የመነሻ ሃሳብ እርሾ ነበረው። እኔ እንደማስበው ከቅንጅት መራራ ስንብት በኋላ የተፈጠሩት፤ አገር ውስጥ ይታገል የነበረው አንድነት የግንቦት 7 አዲስ የሁለገብ ፍልስፍና መንፈስ የመጋራት አቅምን አጠይቆ ይመስለኛል ግንቦቲዝም ሁለገብ ትግል ዶግማው የነበረው፤ ይመስለኛል። ይመስለኛል እምለው እራሱን ችሎ ጥናት ስላልተደረገበት ነው የአቀረብኩት አመክንዮ። አገር ውስጥ ግንቦቲዝምን በበዛ ጉጉት ይጠብቁ የነበሩ ተናጠላዊ መንፈሶችም ሊኖሩ እንደሚችሉ አስባለሁኝ። ግንቦቲዝም የቅንጅትን መራራ የስንብት መንፈስ ትንሳኤውን ያወጄ ንቅናቄ ስለነበር። ዲያስፖራ ላይ አንጃ አልተፈጠረም፤ ወጣ ገብም ሁነት አልነበረም። ግንቦት 7 ዲያስፖራውን በአካል የመምራት አቅም ስለነበረው ለሌላ ኃይል ድውለት አልሆነም። #ግን ሁለገብ ትግል የትኛውን የትግል መሥመር ሊከተል ይችላል? 1) ሰላማዊ ትግልን። 2) የትጥቅ ትግልን። 3) ከዚህ ውጪም ሌላ የትግል መስክ ሊኖር ይችላል በእኔ ዕይታ። #የዝምታ #ዕድምታ ። በዘመነ ህወሃት መራሹ ኢህአዴግ የሁለገብ ትግል አራማጅ ተብለው፤ "በአሸባሪነት" ተፈርጀው ብዙ በጣም ብዙ #ንጹኃን የጥቃት ሰለባ ሆነዋል። በተለይ በበዛ ሁነት የአማራ ልጆች። ሙየህወሃትን መንበር ከሥሩ የነቀለው ግን ከሁለቱም የትግል ስልቶች ውጪ የነበረ ዝቅ ሲል ጥቃት አሻም ያለ #ቅን መንፈስ፤ ከፍ ሲል #የዊዝደም ሙሉ አቅም...