ልጥፎች

ህወሃት #ቤርሙዳ ትርያንግል ነው። ቀደምት ከተማዋ ናፍቆቴ ደብረታቦር #ጠቀራ መልበሱ ሐሤቱ ለማን ይሆን?

ምስል
  ቀደምት ከተማዋ ናፍቆቴ ደብረታቦር #ጠቀራ መልበሱ ሐሤቱ ለማን ይሆን?   ህወሃት #ቤርሙዳ ትርያንግል ነው።   "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"       #ምዕራፍ ፲፰።   እንዴት አረፈዳችሁ ውዶቹ ውቦቹ። የሚናፍቀኝ፤ የምሳሳለት የደብረታቦር ከተማ መንደዱን ሳደምጥ በሃዘን ውስጥ ሆኜ ነው። በብልጽግና እና በህወሃት መካከል የተደረገውን ጦርነት በሠላም ሲቋጭ ተረፋልኝ ብዬ ከደብረብርሃን ጀምሮ ያሉ ከተሞችን ስዘረዝር #ደብረታቦር ከተማ አንዱ ነበር። ሙሉ ለሙሉ በህወሃት ወረራ እና የበቀል እርምጃ ህወሃታውያን ሳያሳኩት ከቀሩ ከተሞች የደቡብ ጎንደር ርዕሰ መዲና የታሪክም #ቀንዲል ደብረታቦር አንዱ ነበር።    ይህ የሰሞኑ መጥፎ አጋጣሚ የታሪክ #ጠቀራን ሳደምጥ ውስጤ አዘነ። ደብረታቦር አልባሌ ከተማ አይደለም። በጣም ነው የማውቀው። ቀበሌ መንደሮችን ሁሉ። ዝክረ ታሪኩ ዘለግ ብሎ ከሚጠቀስባቸው ከተሞች አንዱ ደብረታቦር ነው። የታሪክ ድርሳንነቱ በክብር ጥበቃ ሊደረግለት ሲገባ እንዲህ አመድ ሆኖ ማዬት ውርዴት ብቻ ሳይሆን #ውርዴም ነው። ማን ይፈጽመው ማን አላውቅም። እኔ ከቦታው ስለለሁኝ፤ ማንንም ስለማላገኝ ትክክለኛውን መረጃ ለማግኜት አልችልም፤ ማን ምን ፈጸመ የሚለውን። በስማ በለው ደግሞ ለህሊና ዳኝነት ይቸግራል።   ግን ከአመድ፤ ከጭስ፤ ከውድመት የሚታፈስ ቅርስ እና ውርስ እንደሌለ ጠንቅቄ አውቃለሁኝ። ያሳዘነኝ ይህ ነው። ወረታም መቀጠሉን ሰምቻለሁኝ። ወረታ ወሳኝ ከተማ ነው። ይህ ለህወሃት ለተስፋው ጥሩ መደሊድል የሚፈቅድ ስትራቴጂያዊ የድል ብሥራትም ነው። ወደ አዲስ ዘመን፤ እንፍራንዝ፤ ጸዳ፤ ጎንደር ከተማ ለማቅናት፤ የአዲስ አበባ ጎንደር መንገድን ለመዝጋት፤ የ...

#ሰብአዊነት ከምህረት #ይጀመር። #መሪነት ከሰዋዊነት ነው የሚጀምረው።

  #ሰብአዊነት ከምህረት #ይጀመር ። #መሪነት ከሰዋዊነት ነው የሚጀምረው። #መሪነት ራስን በዲስፕሊን ለማስገዛት ከመፍቀድ ይመነጫል። #ማዳንን ማዳን የማይቻለው ስለምን ይሆን?   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   #ምዕራፍ ፲፰   በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች ካሉ ነዋሪወች ጋር ብልጽግና ያደረገውን ውይይይት በሙሉ አዳመጥኩት። አንዳንዱ ሙሉ ሳይሆን ከፊሉ ተቆርጦ በዜና መልክ ይቀርብ ስለነበር እሱንም ታግሼ በጥሞና ተከታተልኩት። ግብረ መልሱ #ወጥ ነው። ህዝቡ "መከላከያ፤ ፋኖ፤ ሚሊሻው፤ አድማ በታኙም ልጃችን፤ ወንድሞቻችን፤ የእህት የወንድሞቻችን ልጆች፤ የአክስት አጎቶቻችን ልጆች፤ የኛው የራሳችን ወገኖች ናቸው።" ሲሉ ነው ያደመጥኩት።    ይህ ማለት ሃዘኑም፤ ደስታውም የጋራ እና የወል ነው የሚል ዕድምታ አለው። ስለሆነም ከግብረ መልሱ የተረዳሁት የመፍትሄ አቅጣጫ ብሄራዊ የምህረት ዓዋጅ ቢታወጅ #ወጥ የሆነ የውስጥ መረጋጋትን ይፈጥራል ብዬ አሰብኩኝ። ስለሆነም ይህን ጉዳይ የመጀመሪያ ረድፍ እርምጃ የብልጽግናን መንግሥት ይወስድ ዘንድ ጠየቅኩኝ። አቤቶ ብልጽግና ሊሰማኝ ፈጽሞ አልፈቀደም። የተፃፈው ለብልጽግና ሆኖ #ፋኖ ግን ሰምቶ የምህረት ዓዋጅ ማወጁን አዳመጥኩኝ።   በገዢው ፓርቲ ቁብ ያልተሰጠው ቁምነገር ከፋኝ ብሎ ዱር ቤቴ ባለው ፋኖ መደመጡ ጥሩ ነገር ነው። የእኔ ጉዳዬ መኖሩ ሰላም ላጣው የአማራ ህዝብ እና የክልሉ ነዋሪ የውስጥ #መረጋጋትን በአንፃራዊ ሁኔታ ያመጣ ዘንድ ነበር ብሄራዊ የምህረት ዓዋጅ ያስፈልጋል ያልኩት። እርግጥ ነው ብሄራዊ የምህረት ዓዋጅ፤ ለሚያውጀው አካልም አቅም፤ ኃይል ያሰባስባል። የመረጃ #ፍሰቱንም ያጠናክራል። መተማመንም #በአንፃራዊነት ይፈጥራል።  ...

የብልጽግና የስንዴ #ነዷዊነት የጉዞ ቁመና በሥርጉትሻ ዕይታ።

ምስል
  የብልጽግና የስንዴ #ነዷዊነት የጉዞ ቁመና በሥርጉትሻ ዕይታ።   መጽሐፈ ሩት ምዕራፍ ፪ ቁጥር ፯ …    «እርስዋም። ከአጫጆቹ በኋላ በነዶው መካከል እንድቃርምና እንድለቅም፥ እባክህ፥ ፍቀድልኝ አለች፤ መጣችም፥ ከማለዳም ጀምራ እስከ አሁን ድረስ ቆይታለች፤ በቤትም ጥቂት ጊዜ እንኳ አላረፈችም አለው»        #ምዕራፍ ፲፰   ይህ የፖለቲካ ፓርቲ የአደረጃጀት፤ የመርህ አፈፃጸም ጉዳይ #የተማርኩትም ፤ #የሠራሁበትም ስለሆነ ትዝብቴን እንሆ … የዕለቱ አትኩሮቴ፣ #በምርጫ ምልክቱ እና #በማንፌስቶ ዙሪያ ይሆናል። #ምንጭ ፎቶውን ጨምሮ ፋና ቴሌቪዥን እና የብልጽግና ፖለቲካል ፓርቲ ፌስቡክ ፔጅ ላይ ነው የወሰድኩት። ከሥር ተያይዟል።   • #የምርጫ ምልክቱ እና ማንፌስቶውን ማንስ ያጸድቀዋል?    አጽዳቂው የአባላት ጠቅላላ ጉባኤ ብቻ ነው።    1) ድርጅት ምንድን ነው? በቀላል አገላለጽ ሁለት እና ከዚያ በላይ ሰወች፤ ተቋማትም ሊሆኑ ይችላሉ፤ በፆታቸው፤ በዕድሜያቸው፤ በሙያቸው፤ በሃይማኖታቸው፤ በኢኮኖሚ አቅማቸው፤ በራዕያቸው ዙሪያ በሚያስማማቸው፤ በሚያግባባቸው ዓላማ እና ግብ፤ ወይንም ፍላጎት የሚፈጥሩት አቅምን፤ ኃይልን እና ጉልበትን የሚያማክሉበት ሥልጡን የሆነ የተቋም፤ የሥርዓት ለመመሥረት የመሰባሰቢያ ስልት ነው። መንግሥት እራሱ ድርጅት ነው።    2) የፖለቲካ ድርጅትስ?   የፖለቲካ ድርጅት የዓላማ እና የግብ ጥምረት ሳይሆን፤ ውህደትን የሚያበስር ተቋም ነው።   3) አንድ የፖለቲካ ድርጅት አካላት አሉትን።   አለው። የመጨረሻው የሥልጣን አካል ብሄራዊ ጉባኤ ሲሆን፤ መሰረቱ አስኳል ከሥር...