ልጥፎች

የሌሊቱ የመሬት መንቀጥቀጥ እና #ድብ ያለው የኢትዮጵያ ፖለቲካ።

ምስል
  የሌሊቱ የመሬት መንቀጥቀጥ እና #ድብ ያለው የኢትዮጵያ ፖለቲካ።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"     በክርስትና ሆነ በእስልምና መሠረቷ በጸናው ኢትዮጵያ አገራችን በተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ እዬታዬ ነው። ዘለግ ላለ ጊዜ የቆዬ ንዝረት ሌሊት እንደ ነበረ ዘገባወቹ ይናገራሉ። #ሰውኛነቱ ፈተና ውስጥ ያለው የኢትዮጵያ ሁኔታ ደግሞ በሰው ሰራሽ ድሮን የአማራን ህዝብ #እያፈለሰ ፤ #እያሸበረ ፤ #መጠጊያ እያሳጣ ነው።   ዛሬ ሌሊት የአዲስ አበባ ነዋሪወችን በማስደንገጥ የቀሰቀሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ብዙ የአገራችን በዕቶች እንደነዘረ ባለሙያወች ይናገራሉ። በአዲስ አበባ አካባቢ የሚገኙትን ከተሞች እና እንዲሁም በአዋሽ፦ ጭሮ ዙሪያ፤ በድሬድዋ፤ ናዝሬት፤ ደብረዘይት፤ ደብረብርሃን፤ መተሃራ፤ ከሚሴ፥ ደሴ ወዘተ ተከስቷል።    ይህን ሰማያዊ የማስጠንቀቂያ #ቃል #ባሊህ ብሎ በፆም በጸሎት፦ በድዋ፦ በሱባኤ ለላይኛው አቤት ማለት ሲገባ በገፍ የአማራ ልጆች #ይታሰራሉ ፤ በገፍም ወደ ጦርነት በሚያመሩ ጉዳዮች ሰፊ ሽፋን እዬተሰጠ ይገኛል። #ጭካኔው ፤ #ጥላቻው ፤ #የአለመደማመጡ ሁኔታ አይሎም በኢትዮጵያ ፖለቲካ ጎልቶ ይታያል።    ኢትዮጵያ ሰውኛ፤ ተፈጥሮኛ ፖለቲከኛ ቢኖራት አገራዊ የፀሎት ጊዜ ሊታወጅ በተገባ ነበር። አደብ ገዝቶ ይህን ወቅት በራሱ ወደ ዘላቂ #መፍትሄ ለማምራት ትልቅ አጋጣሚ ነበር።    የሰማይ ቁጣ ማስጠንቀቂያ ከመጋቢት 18/2010 ዓም ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ወደ ሥልጣን ለመምጣት ዋዜማ ላይ እያሉ ነበር ሌሊት በዋዜማው በመቀሌ አቅራቢያ የመሬት ንዝረት የተከሰተው። ከዛም የዶር አብይ የ100 ቀናት ሳይጠናቀቅ ነበር መሰል የሰማይ ማስጠንቀቂያ በጉ...

የሰባዊነት ልዩ #ዓርማ የነበሩት የሆኑትም የቀድሞዋ የጀርመን ካንስለር የዶር አንጌላ ሜርክል ፓርቲ (CDU+ CSU)ወደ ቁልፍ ሥልጣን ተመለሰ።

ምስል
  የሰባዊነት ልዩ #ዓርማ የነበሩት የሆኑትም የቀድሞዋ የጀርመን ካንስለር የዶር አንጌላ ሜርክል ፓርቲ (CDU+ CSU)ወደ ቁልፍ ሥልጣን ተመለሰ።   "የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል፤  እግዚአብሄርግን አካሄዱን ያቃናለታል።"  (ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱)       በእኔ ዘመን ከተከሰቱ ድንቅ #ክስተት መሪወች፤ #ዕንባን አድማጭ የዓለም ሊሊቀ - ሊቃናት፤ ለየትኛውም አገር የሰባዕዊነት፤ የየንግሥታት ችግር ልዩ #አትኩሮት እና #ቅድሚያ ከሰጡ መሪወች በቁጥር አንድ የእኔ ልዕልት ዶር አንጊላ ሜርክል ናቸው። ፍፁም ሰውኛ፤ ፍፁም ተፈጥሮኛ #በ100 ዓመት ፕላኔታችን ደግማ የማታገኛቸው ልዩ የዓለም #ሥጦታ ናቸው። እኔ ቀጣዩን #የተመድ #ቁልፍ ቦታም ቢሰጣቸው የዓለማችን ምስቅልቅል ፖለቲካ #ፈውስ ያገኛል ብዬ አምናለሁኝ። አድማጭነታቸው፤ የእናትነት ፀጋቸው የመሰጠታቸው አቅም ልዩ ነውና። እኔ በክብርትነታቸው ሁልጊዜም ለምንጊዜም አምላኬን መማኑኤልን አመሰግናለሁኝ።    የሆነ ሆኖ በዚህ ዓመት የጀርመን የምርጫ ሂደት ልብ አንጠልጣይ ስለነበር፦ በተወሰነ ደረጃ ተከታትዬው ነበር። ትናንት ከምወደው የጀርመን ሚዲያ ውስጥ አንዱ በሆነው #በRTL ሂደቱን ተከታትዬው ነበር። ነፍሴ ተንጠልጥላ። ግሩንም እድገት ማሳዬቱን ተመልክቻለሁኝ። የሰብዓዊ መብትን ጥሰት፤ ድህነትን ሽሽት ወደ አውሮፓ የሚጎርፈው ስደተኛ ህይወት እንዴት ይሆን በማለት ነበር የተከታተልኩት።   እርግጥ ነው ስደተኛ የየአገሮችን #ህግ በማክበር፤ በጨዋነት፤ በዲስፕሊን፥ #ዕድልን በማክበር፦ መኖር ሲገባ ጭራሽ በወንጀላዊ ድርጊት መሳተፍ፤ ያስጠጋን አገር ህዝብ ስለስጋት መዳረግ፤ ተጨማሪ ጫና መፍጠር፤ #ህይወትን #ያስቀጠ...

????? #አገራዊ #የምክክር #ኮሚሽኑ #በኽረ #ተልዕኮ #ምን #ይሆን?????

ምስል
  ????? #አገራዊ #የምክክር #ኮሚሽኑ #በኽረ #ተልዕኮ #ምን #ይሆን ?????   #ዓለም #ዓቀፍ #ሰውኛ #ጉባኤ #ባለፈው #ሳምንት #ያስተናገደችው #ኢትዮጵያ #በገዢዋ #የብልጽግና #መንግሥት #በአማራ #ህዝብ #ላይ #የድሮን #ናዳ #ሲፈስ #መዋሏን #ዓለም #ዓቀፋ #ሚዲያ #ቢቢሲ #ዘገበ ።    "በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ትናንት ሐሙስ የካቲት 13/2017 ዓ.ም. ተያይዘው በተሠሩ አራት ቤቶች ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 16 ሰዎች ሲገደሉ 10 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ቤተሰቦች እና የዓይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ።   ጥቃቱ በዞኑ ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ እነገሽ ቀበሌ (ሐሙስ ገበያ) በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ ሐሙስ ረፋድ 5፡00 ሰዓት አካባቢ በሦስት ሱቆች እና ሻይ ቤት ላይ መድረሱን ቢቢሲ ያናገራቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል።   "[ድሮን] ስትዞረን ነበር" ያሉ አንድ የዓይን እማኝ ጥቃቱ ከደረሰበት ስፍራ በግምት 100 ሜትር ርቀት ላይ እንደነበሩ ጠቅሰው፤ የጥቃቱ ሰለባዎች መንገድ ላይ ሲጫወቱ የነበሩ ህፃናት፣ ገበያተኞች እና ሻይ እየጠጡ የነበሩ ሰዎች ናቸው ብለዋል።   "ከፍተኛ ፍንዳታ" መፈጠሩን የሚናገሩት እማኙ፤ ወዲያው "አካባቢውን አቧራው፤ የቤቱ ፍርስራሽ በጭስ" እንዳፈነው እና ድንጋጤ እና ግርግር እንደተፈጠረ ገልፀዋል።   ሌላ የዓይን እማኝም በፍንዳታው አካባቢው በአቧራ ጭስ መሸፈኑን ጠቅሰው፤ በስፍራው ለመተያትም አስቸጋሪ እንደነበር ተናግረዋል። በደቂቃዎች ውስጥ ጥቃቱ ወደ ተፈፀመባቸው ቤቶች ደርሰው የቆሰሉ ሰዎችን እንዳወጡ እና አስከሬን እንዳነሱ የተናገሩት ሌላ የዓይን እማኝ "የሚጫወቱ ህፃናት እና ቆርቆሮ ሊገዙ የመጡ ሰ...

#በቁሙ #ቀብር #ላይ #የዋለ #ብትክትክ እንኮሸሽሌ #ዕሳቤ።

ምስል
  #በቁሙ #ቀብር #ላይ #የዋለ #ብትክትክ እንኮሸሽሌ #ዕሳቤ ።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"       Anchor Media ''ጦርነቱ ቢጀመር ደስ ይለኝ ነበር። ...ከዚያን በኋላ የኢትዮጵያ ህዝብ እፎይታን ያገኛል'' ፕ/ር መሀመድ ሀሰን» https://www.youtube.com/watch?v=XotdIljSVEA   ይህቺ አገር ኢትዮጵያ ስንቱን ዝክንትል ዕሳቤ፤ ስንቱን ድሪቶ ምልከታ፤ ስንቱን ስቃይ #ጠሪ ዕሳቤ እንደ ተሸከመች አመላካች ነው። እርእሱን በቁሙ ያለ ተርጓሚ ስታነቡት። ጥገኝነትን ተጠይፋችሁ አመሳጥሩት። የጦርነት ናፍቆት ለእኔ ጭካኔ ነው። በዚህ ጭካኔ ውስጥ ኢትዮጵያዊነትን እስቲ አፈላልጉ? ግን ማህበረ ቅንነት እንዴት ናችሁ? ከሠራተኛ መሪነት፤ ከሊቃውንትም፤ ከዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሥመጥሩነት፤ ከቀደምት የነፃነት ታጋይነት፤ ከመሪነትም ጎራ የሚመደቡት ባለሁለገብ የልምድ ባለቤቱ ፕሮፌሰር መሐመድ ሃሰን በጦርነት " #እፎይታ " ይገኛል ይሉናል። ማን በሚመራው ጦርነት ብላችሁ ጠይቁልኝ በትህትናም። ሎቱ ስብኃት።    ለእኔ ዝርግ ዕሳቤ ነው። ለእኔ ይህ አንካሳ ዕሳቤ ነው። ፍላጎቱ በግራ ቀኝ ቢኖር እንኳን ይህን ኩፍኝ መንገድ ማበረታት፤ ከጃርታዊው ጦርነትም ተስፋን መጠበቅ እርቃኑን የቆመ ምኞት ነው። እርግጥ ነው አጃቢ ይኖረዋል። ለእሳት ማገዶ እንደሚቀርበው። ግን ለትውልድ ፀር የሆነ አጥፊ ዕሳቤ ነው።   ፕሮፌሰር አንድ ጊዜ አንከር ሚዲያ ላይ "ኢትዮጵያ የሚለው ሥያሜ #ባይስማማን ልንቀይረው ተነጋግረን እንችላለን" ሲሉ #እግዚኦ ብዬ ነበር። ጋዜጠኛ አቶ መሳይ መኮነንም እናቱ ማንነቷን ሊገፍ የሚችል እጮኛ ግን ድውይ ሃሳብ ሲፈልቅ አልሞገተም። ዝም ብሎ አሳለፋቸው። እ...