ልጥፎች

እስኪ ልጅ ጋሻው መርሻ ይሞገት። በምን የመረጃ ጥናት 95% የአማራ ክልል ሰላም ነው እንዳለ አልገባኝም።

ምስል
  እስኪ ልጅ ጋሻው መርሻ ይሞገት። በምን የመረጃ ጥናት 95% የአማራ ክልል ሰላም ነው እንዳለ አልገባኝም።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #እፍታ ።   አብን ነፍሱ ስለመኖሩ አላወቅኩም። ስለዚህ ሙግቴ በግለሰባዊ ዕይታ ብቻ ቢሆን እፈልጋለሁኝ። ግን ብዕሬ ከፈቀደች እና ካሰኛት ሳይለንት ዲስክርምኔሽን አልፈጽምባትም። እንዳሰኛ ትሰጥስጠው።   #ጠብታ ።   ልጅ ጋሻው መርሻ አንዳቤቴ ነው ሲባል ሰምቻለሁኝ። አንዳቤት ለእናት አገሩ ለኢትዮጵያ በየዘመኑ አርበኛ ማፍራት፤ የቤተክህነት ሊቀ - ሊቃውንትን ለእናታችን ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ማበርከት ተመክሮው ቢሆንም፤ እንደ ልጅ ጋሻው መርሻ #ፈንገጥ ያለ ሃሳብ አቅራባ ግን ሰምቼ አላውቅም። ስለሆነም አቶ ጋሻው መርሻን ሳዳምጠው ሁልጊዜ "የአንድአቤት" ሥያሜ ይገርመኛል።   አንድአቤትን በአካል አውቀዋለሁኝ። ብዙውን የጎንደርን ቀበሌ መንደሮች በእግሬ እየተጓዝኩ አውቃቸዋለሁ። የአንዳቤት የማይረሳኝ እርጎው ነው። ዛሬ የቅኒት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ቄራ የሆነው አርሲ ጢቾ አውራጃ አምኛ ወረዳ በተመሳሳይ የተመገብኩትን እርጎ አንዳቤት ላይ አግኝቸዋለሁ። እርጎ ከምለው አንጠልጥዬ በክብር የቅቤ እርጎ ብለው ዕውነቱን ያደረጀዋል።   የአንደቤትን ገበሬወች፤ የሴቶች ማህበር እና የወጣቶች ማህበርን አመራር ሳወያያቸው አንድአቤት እንደ ሥሙ ሆኖ ነበር ያገኜሁትኝ። እናቴን የእሽታ ልዕልቴን ለምን አንድአቤት ተባለ ብዬ ከሥራ ወደ ጎንደር ስመለስ ጠዬቅኳት። እሷም ከቤተሰብ የሰማችውን ነገረችኝ። በጥንት ጊዜ ገዢወች እየተዘዋወሩ ነበር ፍርድ የሚሰጡት።    አንድአቤትም እንደሌሎቹ ባድማወች የተጉላላ ፍትህ በማጣት የተቸገረ፤ ፍርድ የጎ...

የዓድዋ ድል ሆይ #ይቅርበለን።

ምስል
  #የዓድዋ ድል ሆይ #ይቅርበለን ።   እኛነታችን በግርማ፤ በሞገሥ ያላቀ፤ የእኛነታችን ንጥረ ነገር ለዓለም የገለጸ #ራዲዮሎጂያችን የዓድዋ ድላችን።    "አድርገህልኛል እና አመሰግንኃለሁኝ።"      የዓድዋ ጥንካሬ፤ ብርታት፤ መንፈስ፤ ህይወት፤ አቅም እና ክህሎት #ዊዝደሙን አክሎ ከእኛ ጋር ይሁን። አሜን። አድዋ - ለእኔ፤ ዓድዋ - ለእኛ፤ ዓድዋ ለሁላችንም እኛነታችን የሰጠን፤ የማድረግ፤ የመሆን አቅማችን ለዓለም የገለጠ #ራዲዮሎጃችን ነው። እኛስ ለዓድዋ ድል ምን አደረግንለት?   እኛስ ምን ለዓድዋ #ዕውነት ምን ሆንለት? በጎሳ፤ በዞግ ተከፋፍለን የድሉን አልማዛዊ ብርኃን #አደበዘዝንበት ። የስላቅ መደርደሪያ ካንፓስ ሆንበት። እኛ ለዓድዋ ለተፈጥሯዊ አቅሙ #እንቅፋት ሆንበት። ይህ እርግጥ እና ዕውነት ነው። የአድዋን ክብር እና ልዕልና አብዝተን ተዳፈርነው። አንድነትን ዓድዋ ሰጠን። እኛ ግን ለመቆራረጥ ህግ አርቅቀን አጽድቀን #በአንቀጽ 39 ስንፎክር እንገናኛለን።    ጋዜጠኛ ሆኖ የአንቀጽ 39 ሞጋች ከመሆን በላይ ምን አሳፋሪስ፤ አንገት አስደፊ የታሪክ አሰርነት አለና? ኢትዮጵያ አጀንዳዬ አዬደለችም ማለትስ ከማን ከዬት የተወረሰ #ቋቁሻዊ ዕሳቤ ይሆን???? በውነቱ አውቀንም ይሁን ሳናውቅ፤ ልካችን ሳናውቅ በዓድዋ ድል #ክብር ዕውቀት የአመራር ክህሎት፤ ልቅና እና ልዕልና ልክ መሆን ላልቻልን የስንፍና #ግዞተኞች እግዚአብሄር አምላክ ማህሪ ነውና ምህረቱን ይላክልን። አሜን???    በውነት ተሳስተናል። በውነትም ከዊዝደማችን ጋር ፈቅደን #ተካክደናል ። ፈጣሪ መርቆ ከሰጠን ከብልህነታችን ጋር ወደን #ተላልፈናል እና የዓድዋ ድል ሆይ! ይ...

የዓለም አቀፍ ትኩረት በአቡ ዳቢ እና ዱባይ ጉርሻ page

ምስል
  "የዓለም አቀፍ ትኩረት በአቡ ዳቢ እና ዱባይ፡ ለታሪክ የሚቀመጥ ሰብዓዊ ውሳኔ የአየር ክልል መዘጋትን ተከትሎ በኤምሬትስ ተቀርቅረው ለነበሩ ከ20,000 በላይ ለሚሆኑ የውጭ አገር እንግዶች፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መንግሥት ላሳየው አርአያነት ያለው ተግባር ዓለም እያደነቀችው ነው።   "ማንም እንግዳ ከሆቴል አይውጣ!" የሚል ጥብቅ መመሪያ ለቱሪዝም ዘርፉ ተላልፏል። መንግሥት እንዳስታወቀው፣ የእንግዶቹ የሆቴል፣ የምግብ እና የሌሎች መሰረታዊ ፍላጎቶች ወጪ ሙሉ በሙሉ በመንግሥት ግምጃ ቤት ይሸፈናል።   መንግሥት ብቻ ሳይሆን፣ የግል ተቋማትም የድርሻቸውን ተወጥተዋል። በርካታ የቤት አከራይ ድርጅቶች እና ግለሰቦች ቤቶቻቸውን ለተቸገሩ እንግዶች በነጻ ክፍት አድርገዋል።   ከምንም በላይ "መንግስት እንግዶቹን በሰላም እስኪሸኝ ድረስ ዋጋ መጨመርም ሆነ በራሳችሁ ተቻሉ የሚል አሰራር አይኖርም" መባሉ፣ አገሪቱ ለሰው ልጅ ክብር ቅድሚያ መስጠቷን ያሳያል።" Via the National ጉርሻ page

#በአረብ #አገራት በስደት የምትኖሩ ወገኖቻችን ሁሉ #ፈጣሪ አምላክ ይጠብቃችሁ። አሜን።

ምስል
  #በአረብ #አገራት በስደት የምትኖሩ ወገኖቻችን ሁሉ #ፈጣሪ አምላክ ይጠብቃችሁ። አሜን።    #ጦርነት #ጨካኝ ነው። ከዚህ እሳት አማኑኤል #ሁላችሁንም ይጠብቃችሁ። አሜን።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።     ሥርጉትሻ 02/03/2026 #ሰላምን #ያሰማን ። አሜን።