ልጥፎች

#ሰንበትን #ለመጠያዬቅ። #ኦባንግሻ የት ነው ያለኽው?

ምስል
  #ሰንበትን #ለመጠያዬቅ ። #ኦባንግሻ የት ነው ያለኽው?    ባለህበት እግዚአብሄር ይጠብቅህ። አሜን።   "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"     ሌሎች የሰብአዊ መብት ሞጋቾቼ ቀጣይ ተሰጣቸው ዕድል ለአንተ #ተነፈገ ወይንስ #ፈቅደህው ይሆን??? እነሱስ ስለምን ዝም አሉ። ብቻ የሰላም ያድርገው። አሜን።   #ምዕራፍ ፲፯   አንተ ብርቱ የሰላም ወዳጅ፤ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ፤ የኢትዮጵያዊነት #ዘብ #አደር አቶ ኦባንግ ሜቶ የት ነው ያለኽው?    #በህይወት አለህን? ጤንነትህ #ደህና ነው ወይ? ትዳርህ ተሳካን? ግን እንዴት አለህልኝ የምር ወዳጄ ኦባንግሻ??? አማኑኤል አባቴ ይጠብቅህ። አሜን።   የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችህን ኤክሱን እና ፌቡ አልፎ አልፎ መልዕክት ከፃፍክ ብዬ እጎበኛቸዋለሁኝ። ትንሽም #ፍንጭ የሚሰጥ ነገር አላገኜሁም።    በቃ! ኦባንግሻ የአንተ ታሪክ በዚህ መልኩ ቄሱም፤ መጸሐፋም #በዝምታ ይቋጭን??? ለነገሩ ኮነሬል ጎሹ ወልዴስ የት ናቸው። ስለ ክቡርነታቸውም ሰምቼ አላውቅም። ኢትዮጵያ እንደገቡ ደማቅ፤ ክብራቸውን የመጠነ አቀባበል በቤተ መንግሥት መደረጉን አይቼ ነበር። ከዛ በኋላ ግን??? ወፍ ዜና ነጋሪ የለም።   ወይ አጋጣሚ እነ ማህበረ - ሌንጮ ስኮዬር፤ ዶር ዲማ ነገዕወ በፓርላማ በሚንጎባለሉበት ዘመን፤ እነ አቶ ዳውድ ኢብሳ ያሻቸውን ባሻቸው ሰዓት በሚናገሩበት ዘመን፤ እነ አቶ ስብኃት ነጋ በክብር ወደ አሜሪካ ተልከው የኢትዮጵያን ፖለቲካ እንደ አሻቸው ሲያምሱት፤ ሲያተራምሱት እያዬንም ነው።    ከሳቸው ምን ብጣቂ #ርህራሄ ይገኛል ተብሎ የክብካቤ ሞዝቦልድ እንደ ተሰናዳ ባይገባኝም። የጭ...

Zufliegen. Gedicht. Danke.

ምስል
  Wie geht es euch, meine Lieben? Ich habe heute ein passendes Gedicht. Danke.       ·       Zufliegen Unterbrochen … Gehen und gehen und gehen noch mal gehen Fahren und fahren und fahren noch mal fahren Reisen und reisen und reisen noch mal reisen Immer noch immer wieder laufen Zweite hat keine Haltestelle Sie hatte Reiselust, die nicht wartete. Die Reisenden müssen unbedingt mitfahren Es gibt keine andere Möglichkeit. Sonst werde ich durchfallen Ja, aus -------, die Zeit vorbei Die Natur der Zeit ist fliegen Verfliessen verfliegen verfliessen Die Zeit fliesst wie ein Fluss Die Zeit fliegt wie im Flug Zeit macht Geschichte. Danke. Sergute © Selassie. 22.12.2025 (Schweiz, Winterthur.)  

#መጥኔ #ለኢትዮጵያ ፖለቲካ። #ተስፋዬ መዳህኒተ ዓለም ብቻ ነው።

ምስል
  #መጥኔ #ለኢትዮጵያ ፖለቲካ። #ተስፋዬ መዳህኒተ ዓለም ብቻ ነው።    "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   #ምዕራፍ ፲፯     የወጣትነ ዘመን፣ የጎልማሳነት ዘመን #ካቴና ? መጨረሻው መራራ ስንብት።   ለአንዲት ቀን የነፃነት ብርኃን የተነፈጉ ወገኖቻችን ከውስጣችን ብናስባቸው፣ እዮራዊ ምህረት #አይርቅም ነበር። #ሳቅ #ርቆናል ። ለምን? #ጭንቀት #ስንቃችን ስለሆነ። መፍትሄውም #ዝንቅንቅ ስላለ። ስለሆነም #እኔ #ተስፋዬ አምላኬ ብቻ ነው።   የሃይማኖት አቨው ጠንክረው ቢፆሙ፤ ቢሰግዱ፤ ሱባኤ፤ ድዋ ቢያደርጉ ጥሩ ይመስለኛል። ርህርህና ርቆናል። ከሳሽም፤ ተደሳሽም የእርግማናችን ስጦታ እንጂ ውስጣችን ሳይድን አገር ማዳን፤ ተስፋን ማዳን፤ ነገን ከጭንቀት መታደግ አይቻልም። ከሰሞኑ በአማራ ክልል ያሉ ህዝባዊ ውይይቶችን እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ባተሌ ዜጋ ሆኜ አዳመጥኩት። የቀሩኝ ስላሉ ስጨርስ እጽፍበታለሁኝ።    በፍጹም በፍጹም ሁኔት ብዙ ክስተታዊ ገጠመኞችን አናውቃቸውም፤ #ብናውቃቸውም አልገባንም። ለነገሩ እንዲገባን መፍቀዳችንም በሚመለከትም ዳታው የለኝም። የተራራቀ ፍላጎት እና ምኞት፤ ነፃነት እና ጎዳናው ሁሉም ክስተት ከእኛ የፖለቲካ ክህሎት አቅም በላይ ሆኖ ነው ያገኜሁት።   የሆነ ሆኖ የአውሮፓውያኑን 2025 ልንሸኝ ጥቂት ቀናት ይቀሩናል። ያው እኔ የተስፋ ተስፈኛ ነኝ እና እስር ቤት ላሉ የፖለቲካ እስረኞች መፍትሄ ጠባቂ ነኝ። አቤቱታም አቅራቢ ነኝ። ህልሜ ዕውን ቢሆን ዊዝደሟ ኢትዮጵያ ላይ #የፖለቲካ እስረኛ እንዳይኖር ነው። ይህ ደግሞ የገዢውን የብልጽግና የፖለቲካ ሙሉ አቅም ይጠይቃል። ፕሮፖጋንዳ አገር ሰርቶ አያውቅም። የፖለቲካ አቅም ማለት የጽንሰ ...

#ትውልድ እና የኢትዮጵያ #ፖለቲካ።

ምስል
  #ትውልድ እና የኢትዮጵያ #ፖለቲካ ።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"     #ምዕራፍ ፲፯   መስኪ ጠንካራ ጸሐፊ፤ ብርቱ ሞጋች፤ #በዕውቀት ላይ የተመሠረተ የፖለቲካ ተንታኝ ናት። ከ2013 እኢአ ጀምሮ ነው በብዕሯ የማውቃት። ትጉህ ናት። ትጋቷ #ተከታታይ ነው። ደራሽ ታጋይ አይደለችም። ባለቤቷ አቶ ፍጹም የፖለቲካ ሰው አይደሉም። የመኖር ነፃነቷን አላሰሩትም። ስለዚህ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ጉልህ ተሳትፎ ታደርግ የነበረች ባለትዳር፤ የሁለት ፍቅር የሆኑ ልጆች #ክብርት እናት ጸሐፊ እና መምህርት ስትሆን፤ የምታቀርባቸው ሃሳቦች #ጉልበታም ናቸው።   በጣም እንደ ታላቅ እህት #ስለምሳሳላት #ዩኒሴፍ የመሰለ የበጎ አድራጎት ድርጅት #ልጆች #ተኮር በፈለገችው ፎርማት በኢትዮጵያዊነት ወይንም በአማራነት ትጀምር ዘንድ የመነሻ ሃሳብ ጽፌ ነበር። ጓደኛየ ስላልሆነች ትየው፤ አትየው፤ ይድረሳት አይድረሳት አስተያዬቴ አላውቅም። ለጓደኞቿ ግን ይነግሯት ዘንድ በትህትና ነግሬያቸው ነበር። የሆነ ሆኖ ያን መንገድ ብትመርጥ #ተመራጭ ፤ #ፍጹም የተሻለም ይሆን ነበር። ለስኬቱም ጥርጥር አልነበረኝም።   #መምህርነት እኮ ሁለገብነት ነው። ሁሉን የሰጠው ሙያ ነው መምህርነት። አባቴ አቨይ፤ ታላቅ እህቴም መምህር ሆነው የዕውቀታቸውን ዲካ አውቀዋለሁኝ። የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አደራጅም ስለነበርኩኝ መምምህራን ልቅም፤ ክውን፤ ጠፈፍ ያለ ሥራ ይዘው እንደሚቀርቡ ምስክርም ነኝ። ድንቅ ሙያ ነው መምህርነት። የበጎ አድራጎት የልጆች ብትጀምር ታሳካውም ነበር። ለመብት ለልጆች የሚቆም ተቋም ኢትዮጵያ ያስፈልጋታል ብዬ በጽኑ አምናለሁ። ለዚህ ደግሞ ምርጫየ መስኪ ናት።    #የሆነ ሆኖ።   ብልጽግና...