ልጥፎች

የፋክት #ፍልሰት #በፍድሰት።

  የፋክት #ፍልሰት #በፍድሰት ።    "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   መጥኒ ላንች ማህፀንሽ ማገዶነቱ አባርቶ ለማያውቀው ገራገሯ የአማራ እናት። ከዬት እንደምጀምር አላውቅም። ሰሞኑን ዶር ዳኛቸው አሰፋ የአማራ የማንነት እና የህልውና ተጋድሎ በሚመለከት የራሳቸውን ዕይታ አቅርበዋል። በህዝቡ መንፈስ ውስጥ እራፊ መሬት ካገኙ ጊዜ ይዳኜው። እንደ እኔ ግን ኮነሬል ደመቀ ዘውዱ የተመሰጡበት ዴሞክራሲያዊ አቋም የፋክት ፍልሰት እና ፍድሰት ሆኖ ነው ያገኜሁት። ይህን ያህል ከገዢው ድርጅት " ከብልጽግና" መንግሥት ጋር መተማመኑ ካለ ስለምን ባጀት አይለቀቅላችሁም????   ዶር ዳኛቸው አሰፋ በንግግራቸው ውስጥ ብዙ የማያውቁትን ማብራሪያ ሲሰጡ ሰምቻለሁኝ። ከዚህ ቀደምም። እሳቸው ያልፈፁምትን፤ ወይንም ያላስፈፀሙትን ጉዳይ እንደ ፍልስፍና ሙሁርነታቸው እንደዛ ደፍረው ሲናገሩ ገረመኝ። "አወዛጋቢ ቦታወች" የደቡብ አፍሪካ ስምምነት ያመነጨው ነው።    " ምዕራብ ትግራይ" የሚለው ግን ጥቅምት 2022 ስምምነቱ ተከናውኖ፤ እስከ ሰኔ 2023 ድረስ ከተከበሩ አንባሳደር ማይ ሃመር ኤክስ ገፃቸው ላይ ሄደው ይፈትሹ። ይህም ብቻ አይደለም የኤርትራ መንግሥት እንደ መንግሥት፤ የኢትዮጵያ መንግሥት እንደ መንግሥት፤ ህወሃት እንደ ክልል ባልተጠዬቁበት ሦስት ወንጀል የአማራ ልዩ፤ ኃይል፤ ፋኖ፤ እና የአማራ ሚሊሻ በሦስት ጣምራ ወንጀል ነበር ሲከሰስ እማዳምጠው። ከቦታው ስላልነበርኩ ዕውነቱን ማወቅ አልችልም።   በሰው ልጅ ላይ ግፍ የፈፀመ መጠዬቅ ግድ ነው። ማንም ይሁን ማን። ተጣርቶ ብዬን ከተሰጠበት። ግን ሁለቱም መንግሥታት እና ህወሃት በጦር ወንጀል ብቻ ሲከሰሱ ዬአማራ ፀጥታ ኃይል ግን #በሦስት ወንጀል ተከሳሽ ነበር።

የመልካም ዜና ነዶዬ። (Rosinenpoesie.)

ምስል
·         ንጋት - ፍካት። ·         ከብረቶቼ እንዴች ናችሁ። ·         አገር ለውጥ የላትም። ·         ግራጫማ ገረጭራጫው ዘመን ያልፋል። ·         ጥበብ እና ብልህነትን ይጠይቃል። ·         አይዞን። ·         ሸበላ ቀን። ·         ኑሩልኝ። አሜን።   ሥርጉትሻ2024.10.15

የሰው ልጅ ሁልጊዜ ለዘመን ሰጥ ስልጡን አዲስ እሳቤ በህሊናው ውስጥ የእንግዳ መቀበያ ክፍል ሊኖረው ይገባል። Ide...

ምስል

መንግስት በIMF ጉድ ተሰራ ተረክ ሚዛን Salon Terek

ምስል

"የኢትዮጵያ ፖለቲካ እና የአፍሪካ ቀንድ ሁኔታ"፣ ውይይት ከፕሮፌሰር ብሩክ ሃይሉ ጋር

ምስል

ነፃነት በራስ የመተማመን አቅም ነው፥ ምንጭም ነው። Eigenständigkeit. Freiheit. Selbstvertr...

ምስል

"ህዝቡ ሁለቱንም አይፈልግም!" አምባሳደሩ ህወሓት መሳሪያ የቀበረበትን ቦታ አጋለጡ!

ምስል

ፋይዳ ቢስ የፕሬዝዳንት ፅ/ቤት፣ የፋኖ ድል ዜናዎች፣ የተሰነጠቀው የህወሓት ቤት #amhara #fano #tplf #...

ምስል

ኢትዮጵያ ህግ ናት። ይህን ማንነቷን ማስቀጠል የሁለችንም መብታዊ ግዴታችን ነው። Kinder; Die Alten, di...

ምስል

መርህ መኖርን ሥልጡን ያደርጋል። Prinzip. Gesetz. Regel. Dogma. Verfassung. Moralisc...

ምስል

ኮከቧ ኢትዮጵያዊ የR & B ዘፋኝ - የግራሚ አባል ናት፣ ከኩል ኤንድ ዘ ጋንግ እስከ ሀሊዉድ ተዋናይ ጋር መስራት...

ምስል

ፋኖ ባክግራውንዱ "ሽፍትነት" አይደለም። ፋኖ አፈጣጠሩ ሲፈረካከስ ውሎ የሚያድረው የውራጅ ፖለቲካ ርዕዮት አልፈጠረውም።

  ፋኖ ባክግራውንዱ "ሽፍትነት" አይደለም። ፋኖ አፈጣጠሩ ሲፈረካከስ ውሎ የሚያድረው የውራጅ ፖለቲካ ርዕዮት አልፈጠረውም።   ሰማዕቱ የተከበሩ ጄኒራል ሰኃረ መንፈሳቸው ምን ይታዘብ ይሆን????    በኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት፤ አሠራር፤ አቅም፤ አመራር እጅግ ጠንቃቃ እና ቁጥብ ነኝ። ዛሬ በዚህ ዕርስ ዙሪያ ስጽፍ የዜግነት #ተጋርቶዬ እራሱ እያሰቃዬኝ ነው። በአንድ ላይ ኢትዮጵያዊ መባል ምን ያህል ፈተና መሆኑን ያዬሁበት አጋጣሚ ነበር።    "አቤቱ ለአንደበቴ ጠባቂ አኑርለት።"   የማከብራችሁ የአገሬ ልጆች ዘለግ ያለ ሙግት ነው።   የማህበረ ኦነግ ፖለቲካ - ልቅነቱ ብቻ አይደለም የሚያስገርመኝ። ይልቁንም የቁንጮ መሪወቹ የህግ ጥሰት #ህጋዊነት እንጂ። ብልሽቱን እኮ አስተካክሎ ማቅረብ ለካስ ይህም መሰጠትን ይጠይቃል። ሳይመረኝም፤ ሳያንገፈግፈኝም የኢትዮጵያ ኢታማጆር ሹሙ ጄኒራል ብርኃኑ ጁላ ከሉዓላዊ ሚዲያ ጋር የነበራቸውን ቆይታ ሁለቱንም አዳመጥኩት። መጥኔ ለአንቺ ኢትዮጵያ አልኩኝ።    እነ ክቡር ጄኒራል ፈንታ በላይ እና ፍፁም ድንቅ እና ብቁ ጓዶቻቸው የነበሩባት አገር እንዲህ እና እንዲያ ስትንገላታ፦ ወጀብ ሲንጣት ማዘን የሚለው ቃል አይገልፀውም። አቅምስ አቅልስ የት ይሸመት??? ለምን ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ በዬጊዜው የሚበውዙት የካቢኒያቸው፤ እንዲሁም "የብልጽግናቸውም" #ኮሚሳርያት አድርገው ደርበው አይሾሟቸውም የኢትዮጵያን ኢታማጆር ሹሙን። የኢትዮጵያ አዬር መንገድን እና የኢትዮጵያ አዬር ኃይልን እንዳጣመሩት።    ሥርዓት ለኦነግ ፖለቲካ አጀንዳው አይደለምና። ወይንም ላም ጣም በሌላቸው የዶር ለገሰ ቱሉን #የኮሚኒኬሽን ቦታን አይሰጧቸው??? አንደበቴ፤ ልሳኔ ስለሆኑላቸው። ለነገሩ ጄኒራል ብ