ልጥፎች

በእምዬ ሲዊዘርላንድ፤ ዙሪክ ክፍለአገር፤ በዙሪክ ከተማ በራዲዮ ሎራ የብላቴ ሎሬት ጸጋዬ ራዲዮ ከተመሰረተ ዛሬ #መስከረም 18.2025 ልክ ፲፯ (17) ዓመቱ። ተመስገን። አሜን።

ምስል
  በእምዬ ሲዊዘርላንድ፤ ዙሪክ ክፍለአገር፤ በዙሪክ ከተማ በራዲዮ ሎራ የብላቴ ሎሬት ጸጋዬ ራዲዮ ከተመሰረተ ዛሬ #መስከረም 18.2025 ልክ ፲፯ (17) ዓመቱ። ተመስገን። አሜን። #ምንጊዜም ኢትዮጵያ!   "አድርገህልኛል እና አመሰግንኃለሁ።"      ይህ ቀን ለእኔ ልዩ ነው። ይህ ቀን ለእኔ ትርጉሜ ነው። ይህ ቀን ለእኔ ሚስጢሬ ነው። ይህ ቀን ለእኔ ከእናት አገሬ ጋር ቃሌን በማዘውተር የማስርባት ዕለቴ ነው። ምንጊዜም #ኢትዮጵያ !   የጸጋየ ድህረ ገጽም በተመሳሳይ ዓመት ሰኔ 18 ነበር የጀመርኩት። በቲም ይሠራ ስለነበረ መቀጠል አልቻለም። የእኛ ነገር እንዲህ እና እንዲያም ነውና። ዛሬ የአባይ ሚዲያ ያለበትን ደረጃ ተመልከቱት። በተመሳሳይ ዘመን ነው የበቀሉት። ዛሬ አባይ ሚዲያ ቢጠሩት አይሰማም። አጋዥ ያገኜ ሚዲያ የት እንደደረሰ ተመልከቱት። መዝኑትም። ያ ብሩክ፤ ትሁት ሰው አክባሪው ባለቤቱም የአይቲ ባለሙያ ስለሆነ ጥገኝነት የሙያ አላስፈለገውምና። አስቀጠለው። እንኳንም ቀናው።    የሆነ ሆኖ የጸጋየ ራዲዮን ብቻየን ስለምሰራው #ህልውናው ቀጥሏል። የጸጋዬ ራዲዮ በጭምቷ በእምየ ሲዊዘርላንድ፤ ዙሪክ ክፍለአገር፤ ዙሪክ ከተማ በተናፋቂው እና በተወዳጁ፤ 24 ሰዓት በሚተጋው #በራዲዮ #ሎራ በ97.5 መካከለኛ ሞገድ በወር ሁለት ጊዜ በዕለተ ሃሙስ የቀን ቅዱስ #ከ15 .00 እስከ 16.00 እንደ አውሮፕውያኑ ሰዓት አቆጣጠር በአማርኛ ቋንቋ ይቀርባል።   ይህን ተግባር ስደተኛ ካንፕ ውስጥ የምትኖር አንዲት ባተሌ ስትወጥን በባከነ ጊዜ የሚባዝን መንፈስ ራዲዮ ፕሮግራሙ #ተከሰሰ ። የሚገርማችሁ ከዚህ ቀድሞ ሌላ ክፍለ አገር ሄጄ በነፃ ስሰራም ኃላፊዬ ተከሳ ነበር። ከሳሾቹ የእኛው ጉዶ...

#የጨመተው ደቡብ እና ስኬቱ። • እቴጌ ጎንደር ሆይ! ከዚህ የብልህነት #ልዕልና ምን ተማርሽ?

ምስል
  • #የጨመተው ደቡብ እና ስኬቱ። • እቴጌ ጎንደር ሆይ! ከዚህ የብልህነት #ልዕልና ምን ተማርሽ?   #ምዕራፍ ፲፯   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።        #መቅድም ።   በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ክስተታዊ ውሳኔ የወሰነ የፖለቲካ ኢሊት የሚገኝበት የደቡብ ክልል ነው። የቀድሞው ጠቅላይ ሚር አቶ ኃይለማርያም ደስአለኝ ብዙወቹ ቁምጥ የሚሉለትን የ፬ ኪሎ የክብር፤ የማዕረግ ሥልጣን፤ የጠቅላይ ሚኒስተርነትን ቦታ በፈቃዳቸው የለቀቁ ታላቅ ሰው ናቸው።    የተከበሩ አቶ ኃይለማርያም ደስአለኝ ለትውልዱ የፖለቲካ ሥልጣን ማለት ከህዝብ ፍላጎት በላይ እንዳልሆነ ተቋም፤ ሐዋርያ ሆነው በተግባር አሳይተዋል። አብነትም ናቸው። በዘመናቸው ለአጎደለቱ፤ ለጠቀሙት ጉዳይ ዘመን የሚፈታው አመክንዮ ነው። እኔ እራሴ ብርቱ ሞጋቻቸው ነበርኩኝ። አቶ ኃይለማርያም ደስአለኝ በፈቃዳቸው ሥልጣናቸውን ካለምንም ቅድመ ሁኔታ መልቀቃቸ ግን የሚያሸልም የልዩ የታሪክ ክስተት መሥራች ናቸው።    #የደቡብ ህዝብ።   የደቡብ ህዝብ ለስላሳ ህዝብ ይመስለኛል። የደቡብ ህዝብ የማይቸኩል ዝግ ያለም ይመስለኛል። የደቡብ ህዝብ ያስተዋለም ይመስለኛል። የደቡብ ህዝብ #ዕድሉን #የማያፈስ ይመስለኛል። ይመስለኛል እምለው ኑሬ ስላላየሁት፤ በጥናትም መረጃውን በዳታ ሰለአላቀነባበርኩት ነው። በኮርስ፤ በሥራ ዓለም ግን ደቡቦችን በተወሰነ ደረጃ አውቃቸዋለሁኝ። ለዚህም ነው #የጨመተ የሚለውን ኃይለ ቃል የተጠቀምኩት።   የደቡብ ህዝብ ኢሊቶች ህዝባቸውን #በመገበር አይታወቁም። የደቡብ ህዝብ የፖለቲካ ኢሊቶች የህዝባቸው የውስጥ ሰላም እንዲታወክ አይፈቅዱም። ይልቁንም መሻታቸውን፤ የት...

የኢትዮጵያ #ኦርጋኒክ ተፈጥሮ #ያልከበዳቸው ሊቀ - ሊቃውንት #የኔታ ኢኒጂነር ጌዲዮን አስፋው።

ምስል
  የኢትዮጵያ #ኦርጋኒክ ተፈጥሮ #ያልከበዳቸው ሊቀ - ሊቃውንት #የኔታ ኢኒጂነር ጌዲዮን አስፋው።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       https://www.youtube.com/watch?v=2i3_8noLNN0&t=11s የህዳሴ ግድቡን ዶሴ የያዙት ኢንጅነር https://www.youtube.com/watch?v=b8O3hEhsM0k ግብፆች አንድ ሳተላይት መድበው ይከታተላሉ ኢ/ር ጌዲዮን አስፋው ‪@ethiopian_reporter‬   #ጠብታ ።   • ይህን ደርባባ የትውልድ የሆነ ሊቀ - ክህሎት ብጽፍበት ነው የሚሻለኝ። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።   አንድ የወግ ገበታ መፃፍ ያንሰዋል። ይህ ለዘመኑ የምርምር መዕከል የሚያስከፍት #ተቋማዊነት ነው። ይህ በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ #ካሪክለም ተነድፎለት ልጆች ሊማሩት የሚገባ ስኩን የክህሎት ሂደት ነው። ይህ ኢትዮጵያ የተረጋጋ መንፈስ መጠነ ሰፊ ህሊና እና የመቻል አቅም ያላቸው ልጆች እንዳሏት የሚያስነብብ፤ የሚተረጉም፤ የሚያመሳጥር የቅኔ #ቀንዲል ነው።   እንዲህ ዓይነት ስኩን ተግባር ይከውኑ የነበሩ እኔን በቅርበት ሙሉ ጊዜያቸውን ሰጥተው የቀረጹኝ በዘመነ ኢሠፓ የጓድ ገብረመድህን በርጋ፤ የቺኮዝሎባካያ እና የሃንጋሪ አንባሳደር የነበረው የአንባሳደር ወንድወሰን በዘመኑ የነበሩ የሌሎችም የፖለቲካ ሊቀ- ሊቃውንታት የሙያ ርጉ አባቶቼ የተግባር አምሳያ ነው። ስለሆነም እያንዳንዱን ክፍል ሦስት /// ሦስት ጊዜ አዳምጨዋለሁኝ።   ኢትዮጵያ ህግ ናት። ኢትዮጵያ ፍልስፍና ናት። ኢትዮጵያ ሳይንስ ናት። ኢትዮጵያ ዩንቨርስ ናት። ኢትዮጵያ #ይሉኝታም ናት እያልኩ በድፍረት መፃፍ ከጀመርኩ ወደ ፲፭ ዓመታት ተጠግ...