#አስታዋሽ ያጣ ብሄራዊ ዕንቁ። የተዘለለ የጥበብ አገራዊ #ልቅና።
• #አስታዋሽ ያጣ ብሄራዊ ዕንቁ። የተዘለለ የጥበብ አገራዊ #ልቅና ። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። https://www.youtube.com/watch?v=TL-9-_wfJW4 «ተጋብዤም ተሸልሜም አላቅም | መጀመሪያ ፊልም ስሰራ 50 ሳንቲም ነው የተከፈለኝ አርቲስት አልማዝ አበበ» #asham_tv | #አሻም_ቲቪ አንዳንድጊዜ ኢትዮጵያ የጥበብ ባለሙያወች ብቻ #ሰገነት ትመስለኛለች። ክብሩ፤ መወደሱ፤ ድጋፋ አትኩረቱ፤ ሹመቱ ሽልማቱ፤ ዕድል እና እንክህ እንክህ መባሉ በአስተውሎት እከታተለዋለሁኝ። ለካስ ይህ ለሁሉም የጥበብ ሰወች አይደለም። በጥበብ ተሳትፎ ውስጥ የክት እና የዘወትር፤ የእዳሪ እና የቤት ልጅ፤ ዓይነታና እንጥፍጣፊ የሚል እጅግ የሰፋ የሚያስከፋ አድሏዊነት አለ? የክብር አንባሳደርነቱ፤ የማስታወቂያ ዕድሉ ሁሉ …………-------- #ለተወሰኑት ብቻ??? ፍትኃዊነት ቢያንስ በእጅ ባለ ነገር መተርጎም ምን ያቅታል? አሻግሮ ከመጠየቅ??? በመዳፍ ያለ አቅም ስለምን ያቅታል??? ብዙ በጣም ብዙ የጥበብ ጥሪወችን በእኩልነት ላስተናገደች #ዕንቋችን አትኩሮቱ ስለምን ተሰደደ? ተቋማት ሰው መሆን የመቻል አቅማቸው መለኪያው ለእኔ #ፍትኃዊነት ነው። ጉማ አዋርድ፤ ለዛ አዋርድ ወዘተ የሚባሉ ሥርዓት ሲከውኑ አያለሁኝ። የጥበብ ቤተኞችም ተሞሽረው ይገኛሉ። #ባሊህ #ባይ ያጡ ደግሞ እንዲህም የጥበቡ #ቀንዲሎች አሉ። ቢያንስ ለባዕሉ የታዳሚነት ጥሪ ምኑ አነሰ #የአርቲስት አልማዝ አበበ?? ክብርት አርቲስት አልማዝ አበበ በዩቱብ የተለቀቁ ተውኔት ላይ ተሳትፎዋን አያለሁኝ። ከእሷ የማየው ለየገጸባህሪው #ተፈጥሯዊነት ብቃት በጥቂቶች ብቻ የሚገኝ ጸጋ ይመስለኛል። ብዙ ጊ...