ልጥፎች

• #ብሄዊ የምህረት ዓዋጅ አስፈላጊነት እና፤ ለአፈፃጸሙ አክብሮትን ስለመመገብ።

ምስል
  • #ብሄዊ የምህረት ዓዋጅ አስፈላጊነት እና፤ ለአፈፃጸሙ አክብሮትን ስለመመገብ።        የምህረት ዓዋጁ ዱርቤቴ ላሉት ብቻ አይደለም፤ ተንሳፎ ላለው የብልጽግና አካላቱ ጭምር ነው። በጣም ውስብስብ፤ የተፍተለተለ ችግር ውስጥ ነው ክልሉ ያለው። እንደ አገር ኢትዮጵያም የአማራን ህዝብ ቅንነት፤ ገራገርነት ልታጣ አይገባትም። አክብሮ መነሳት፤ ጠንክሮ በማስተዋል መትጋት፤ በብልህነት መከራውን እያዬ ያለውን ህዝብ አለሁልህ ማለት ይገባል። በጥልቀት እንሰበው። በሰፊነትም እንመርምረው።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   ምዕራፍ ፲፯። በዚህ ዘለግ ባለ የወግ ገበታዬ ምዕራፍ ፲፯ ይጠናቀቃል። ከጥቂት የጥሞና ቀናት በኋላ ምዕራፍ ፲፰ ይመጣል። #መኽራዊ አትኩሮት።   ጤና ይስጥልኝ ማህበረ ቅንነት፦ እንዴት አደራችሁ? እንደምንስ - አረፈዳችሁ። እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። በክሪስማስ ሰሞናት ለእኔ አሸወይና ነበር። የመጸሐፍቶቼን ስክሪፕት እማርምበት። በዚህ ሰሞን ነፍስ በምድር ላይ ሥራውን ያቆመ ያህል ጸጥ ስለሚል በርካታ ያላጠናቀቅኳቸውን የአዕምሮ ተግባራት የምከውንበት የመኽር ወቅቴ ነው። በዚህ ዓመት ደግሞ በተለያዩ ሚዲያወች የወጡ የአማራ ህዝብ ድምጾችን ለማድመጥ ፈቀድሁኝ። ዜናወችንም ውይይቶችንም በእኔነት ሙሉ ስሜት ተከታተልኩ።   #ውስጤ ።   ገና ቀንበጥ ሳለሁኝ ሰፊ ዕድል አግኝቼ ምን ላድርግልሽ ስባል ወደ ገበሬዬ መልሱኝ ነበር ያልኩት። እኔ ጎንደር ከተማ ተወልጄ ነው ያደግኩት። ቤተሰቦቼም እንደ እኔው። የከተማ ልጅ ሆኜ ገበሬን እንደ ነፍሴ የመውደዴ ሚስጢር የገበሬው ተፈጥሯዊነት ነበር።   ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ 100 ቀናታቸው...

#የኤርትራ የፖለቲካ ሊቃናት መሻት የኢትዮጵያ ፖለቲካ #ማስተር ማይንድ መሆን ነው። የጹሁፌ መነሻ የBBC ዘገባ ነው። አያዠዋለሁም።

ምስል
  #የኤርትራ የፖለቲካ ሊቃናት መሻት የኢትዮጵያ ፖለቲካ #ማስተር ማይንድ መሆን ነው።    ዘገባው የBBC ነው። እንዳይቆራረጥ ተያያዥ ጉዳዮችን በዬሰዓቱ የወጡ መረጃውን ያካተተ ዘገባ ስለሆነ ይመለከተናል። ስለዚህ ሙሉውን አያይዤዋለሁኝ።   • የአሜሪካ መንግስት እስራኤል ለሱማሌ ላንድ የሰጠችውን እውቅና ካጸደቀ አሁን ያለው የዓለም ፖለቲካ መጨናነቅ ረብ ይላል። ይህ ደግሞ አይቀሬ ነው። አንድ ዴሞክራሲን ዕውን ያደረገ ራስ ገዝ አስተዳደር፤ ወሳኝ ለጂኦ ፖለቲክሱ ወሳኝ ሚና ያለው ቦታ የምኞቱ ስኬት ቅርብ ነው። ቢቢሲ ዛሬን አህዱ ያለበትን ተጨማሪ ማብራሪያ አክያለሁኝ። የሰሞናቱ መስማማት ግርም ብሎኛል።   https://www.bbc.com/amharic/live/cy8jldx8vp3t "የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት እስራኤል ለሶማሊላንድ እውቅና መስጠቷን ተከትሎ አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ" https://www.bbc.com/amharic/articles/c623py0j3xpo "የሶማሊላንድ የዕውቅና ጉዞ እና የእስራኤል ውሳኔ ቀጠናዊ አንድምታዎች #ቆራጣ ዕይታዬን አክላለሁኝ።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       ለሱማሌላንድ እስራኤል ከሰጠችው የዕውቅና ደፋር መግለጫ ባላነሰ ኢትዮጵያ ሰፊውን የዴፕሎማሲ ተግባር ሰርታላቸዋለች። ምርጫቸውን ዓለም በትጋት የተከታተለላቸው በኢትዮጵያ ምክንያት ነበር ብዬ አምናለሁኝ። ለአሁኑ የእስራኤል ውሳኔ አደፋፋሪው የኢትዮጵያ እና የሱማሌ ላንድ ለጋ ያልጠና ስምምነት ነበር ብዬ አስባለሁኝ።   የኢጋድ አቋም አልገባኝም። ባይቸኩል፤ ገለልተኛ ሆኖ ቢቆይ ጥሩ ነበር ብዬ አስባለሁኝ። በሌላ በኩል እስራኤል ለወሰደችው ደፋር ጥንቅቅ ያለ...