የአቶ ታየ ደንዳአ (#ታየይዚም) #የግሉኮስ (ትንፋሽ ቀጥል) ስርጭት ዕውነትን #ያፈልቃል።
• የአቶ ታየ ደንዳአ ( #ታየይዚም ) #የግሉኮስ (ትንፋሽ ቀጥል) ስርጭት ዕውነትን #ያፈልቃል ። ለትውልድም ፈውስ ይሆናል። የዶር ሚልኬሳ ሚዳጋ ቃለ ምልልስ በሆርን ኮንቨርሴሽን በአስፈለገኝ ነጥብ ብቻ። ተጨመሪም ተያያዥ ጉዳዮችን አክላለሁኝ። "የቤትህ ቅናት በላኝ።" ማህበረ ቅንነት አብይዝምን በምዕራፍ ከፋፍየ ነው የተከታተልኩት። እንሆ ምዕራፍ ፲፭ በአብይዝም በራሱ የውስጥ ጠረኖች በአካሎቹ ምስክርነት ይጠናቀቃል። በጣም ዘለግ ባሉ ጹሁፎች ነው አብረን ምዕራፍ ፲፭ የቆየነው። እግዚአብሄር ይመስገን። አሜን። ጃዋሪዝም በሚገባ ተሞግቶበታል። ጥሞና ጊዜውን የጃዋርዚምን አድንቄ ወደ ፖለቲካው መለስ ሲል ግን በሙግት ነበር አቀባበል ያደረኩልት። ከፍ ብ ሎ መታየት እራስ ባበጁት፤ በተረጉሙት የላቀ ተግባር እንጂ ቅኖች በእግዚአብሄር፤ በአላህ አቅም እርዳታ እጅግ ጥልቅ በሆነ ሚስጢር የተከወነን የዘመን ስኬት ደራሽነት፤ ቅጽበታዊነት፤ የመረረ ጥላቻ፤ ግብታዊነት እንዳልጎበኜው በሚገባ በህይወት እያለሁ መግለጥ ስላለብኝ ነበር "ካልኩሌተሩ፤ ሞተሩ አንተ አይደለህም" ማለት ይገባ ስለነበረ ጃዋሪዝም የተሞገተው። ይህን ካለ አቶ ጃዋር መሃመድ (ሃጂ )መንፈቅ ሊሆነው ነው። ከቻለ ለምን ይህን ያህል ጊዜ ፈጀበት ሜዳውም ፈረሱም ተሰናድቶ እየጠበቀው አይደል? ካለስኩን ዊዝደም የሚሳካ ህልም ኑሮ አያውቅም። ለዛውም የመንግሥት ለውጥ። ወደፊትም አይኖርም። በዊዝደም በተበጀች ፈላስፊት ኢትዮጵያ ላይ ተቀምጦ ሲረማመዱበት የነበሩት ማህበረ ኦነጎች ኢትዮጵያዊነት ልቅናውም ልዕልናውም በዘመናችን ዲካ የለሽ እንደሆን ተከታታይነት እንዳለውም ማመሳጠር ይገባ ስለነበር ነው የተሞገተው። በሚዲያ እንደ ...