• #ብሄዊ የምህረት ዓዋጅ አስፈላጊነት እና፤ ለአፈፃጸሙ አክብሮትን ስለመመገብ።
• #ብሄዊ የምህረት ዓዋጅ አስፈላጊነት እና፤ ለአፈፃጸሙ አክብሮትን ስለመመገብ። የምህረት ዓዋጁ ዱርቤቴ ላሉት ብቻ አይደለም፤ ተንሳፎ ላለው የብልጽግና አካላቱ ጭምር ነው። በጣም ውስብስብ፤ የተፍተለተለ ችግር ውስጥ ነው ክልሉ ያለው። እንደ አገር ኢትዮጵያም የአማራን ህዝብ ቅንነት፤ ገራገርነት ልታጣ አይገባትም። አክብሮ መነሳት፤ ጠንክሮ በማስተዋል መትጋት፤ በብልህነት መከራውን እያዬ ያለውን ህዝብ አለሁልህ ማለት ይገባል። በጥልቀት እንሰበው። በሰፊነትም እንመርምረው። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። ምዕራፍ ፲፯። በዚህ ዘለግ ባለ የወግ ገበታዬ ምዕራፍ ፲፯ ይጠናቀቃል። ከጥቂት የጥሞና ቀናት በኋላ ምዕራፍ ፲፰ ይመጣል። #መኽራዊ አትኩሮት። ጤና ይስጥልኝ ማህበረ ቅንነት፦ እንዴት አደራችሁ? እንደምንስ - አረፈዳችሁ። እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። በክሪስማስ ሰሞናት ለእኔ አሸወይና ነበር። የመጸሐፍቶቼን ስክሪፕት እማርምበት። በዚህ ሰሞን ነፍስ በምድር ላይ ሥራውን ያቆመ ያህል ጸጥ ስለሚል በርካታ ያላጠናቀቅኳቸውን የአዕምሮ ተግባራት የምከውንበት የመኽር ወቅቴ ነው። በዚህ ዓመት ደግሞ በተለያዩ ሚዲያወች የወጡ የአማራ ህዝብ ድምጾችን ለማድመጥ ፈቀድሁኝ። ዜናወችንም ውይይቶችንም በእኔነት ሙሉ ስሜት ተከታተልኩ። #ውስጤ ። ገና ቀንበጥ ሳለሁኝ ሰፊ ዕድል አግኝቼ ምን ላድርግልሽ ስባል ወደ ገበሬዬ መልሱኝ ነበር ያልኩት። እኔ ጎንደር ከተማ ተወልጄ ነው ያደግኩት። ቤተሰቦቼም እንደ እኔው። የከተማ ልጅ ሆኜ ገበሬን እንደ ነፍሴ የመውደዴ ሚስጢር የገበሬው ተፈጥሯዊነት ነበር። ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ 100 ቀናታቸው...