ብቃት እንደ ወንዝ አሽዋ ከሜዳ አይታፈስ። ከሥልጠናም መሰጠትን ይጠይቃል።
ብቃት እንደ ወንዝ አሽዋ ከሜዳ አይታፈስ። ከሥልጠናም መሰጠትን ይጠይቃል። "የቤትህ ቅናት በላኝ።" ዶር ለገሰ ቱሉ በተማሩበት ሙያ ለደረጃቸው በብቃታቸው ልክ ቢመደቡ ጥሩ ነው። የግድ እንደ ጋዜጠኛ፤ እንደ ሞጋች ማድመጥ ያለብኝን ጉዳይ #ችዬ ማድመጥ ግድ ይላል። የኮሜንኬሽን አገልግሎት ሙያ ብቻ ሳይሆን #መሰጠትን ይጠይቃል። አቅም፦ ችሎታ በሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃ የሚመጣ ነው። አንባሳደር ፍጹም አረጋ ቀዳሚው ነበሩ። የጨመቱም - ብቁም ነበሩ። ያው ቦታው ለኦሮሞ ሊቃናት #የተመደበ ነው። ከዬትኛውም ክልል ይወከል፦ ለዚህ የአብይዝም ሥርዓት የኦሮሞ ልጅነት መስፈርት ሆኖ ለስድስት ተከታታይ ዓመታት ቀጥሏል። እሺ ይሁንላችሁ ብንል፦ ግን ቢያንስ የሚደመጥ #ለዛ ያለው ሰብዕና፤ ለኢትዮጵያም የአቅም ልክ የሚደመጥ ሰው - ይመደብ። ትዕዛዝ አይደለም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ የግል ዕይታ ነው። የአቶ ለገሰ ቱሉ አንደበትም፤ የንግግር ጥበብ አቅምም ውሱን ነው። በቀላል አገላለጽ ለኢትዮጵያ ተፈጥሮ #ሸክም ነው። አብዝቶ በውስጡ የታጨቀ ቂም እና በቀል፤ #ጥላቻ እና #ማንአህሎኝነት የተከዘነበት ነው። ይህ ደግሞ ተፈጥሯዊ ለሆነችው ለልዕልት ኢትዮጵያ #የገጀሞ ያህል ነው። አንድአንድ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሊቃናት ጠሚር አብይን አላዳምጣቸውም ሲሉ አደምጣለሁ። እርግጥ ነው 365 ቀን ሙሉ የሳቸው ዲስኩር አለ። አንደበቶቻቸው ሚዲዮቻቸው፤ የጸጥታ አካሉ በሙሉ በአንድ መንፈስ ይናገራሉ። ሁሉን ለማዳመጥ የበዛ ታጋሽነትን እንደሚጠይቅ አውቂለሁኝ። ለታማሚው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ተስፋ ግን ማድመጥ የግድ ነው። ካልተደመጠ በያትኛው አመክንዮ የትግል ታክቲክ እና ስትራቴጅ ሊነደፍ ይችላል? ...