ልጥፎች

የአቶ ታየ ደንዳአ (#ታየይዚም) #የግሉኮስ (ትንፋሽ ቀጥል) ስርጭት ዕውነትን #ያፈልቃል።

  • የአቶ ታየ ደንዳአ ( #ታየይዚም ) #የግሉኮስ (ትንፋሽ ቀጥል) ስርጭት ዕውነትን #ያፈልቃል ። ለትውልድም ፈውስ ይሆናል። የዶር ሚልኬሳ ሚዳጋ ቃለ ምልልስ በሆርን ኮንቨርሴሽን በአስፈለገኝ ነጥብ ብቻ። ተጨመሪም ተያያዥ ጉዳዮችን አክላለሁኝ።    "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   ማህበረ ቅንነት አብይዝምን በምዕራፍ ከፋፍየ ነው የተከታተልኩት። እንሆ ምዕራፍ ፲፭ በአብይዝም በራሱ የውስጥ ጠረኖች በአካሎቹ ምስክርነት ይጠናቀቃል። በጣም ዘለግ ባሉ ጹሁፎች ነው አብረን ምዕራፍ ፲፭ የቆየነው። እግዚአብሄር ይመስገን። አሜን። ጃዋሪዝም በሚገባ ተሞግቶበታል። ጥሞና ጊዜውን የጃዋርዚምን አድንቄ ወደ ፖለቲካው መለስ ሲል ግን በሙግት ነበር አቀባበል ያደረኩልት።   ከፍ ብ ሎ መታየት እራስ ባበጁት፤ በተረጉሙት የላቀ ተግባር እንጂ ቅኖች በእግዚአብሄር፤ በአላህ አቅም እርዳታ እጅግ ጥልቅ በሆነ ሚስጢር የተከወነን የዘመን ስኬት ደራሽነት፤ ቅጽበታዊነት፤ የመረረ ጥላቻ፤ ግብታዊነት እንዳልጎበኜው በሚገባ በህይወት እያለሁ መግለጥ ስላለብኝ ነበር "ካልኩሌተሩ፤ ሞተሩ አንተ አይደለህም" ማለት ይገባ ስለነበረ ጃዋሪዝም የተሞገተው።    ይህን ካለ አቶ ጃዋር መሃመድ (ሃጂ )መንፈቅ ሊሆነው ነው። ከቻለ ለምን ይህን ያህል ጊዜ ፈጀበት ሜዳውም ፈረሱም ተሰናድቶ እየጠበቀው አይደል? ካለስኩን ዊዝደም የሚሳካ ህልም ኑሮ አያውቅም። ለዛውም የመንግሥት ለውጥ። ወደፊትም አይኖርም። በዊዝደም በተበጀች ፈላስፊት ኢትዮጵያ ላይ ተቀምጦ ሲረማመዱበት የነበሩት ማህበረ ኦነጎች ኢትዮጵያዊነት ልቅናውም ልዕልናውም በዘመናችን ዲካ የለሽ እንደሆን ተከታታይነት እንዳለውም ማመሳጠር ይገባ ስለነበር ነው የተሞገተው።   በሚዲያ እንደ ...

ነገረ-ፋኖ: እድገት ወይስ ክስረት?| ፖለቲካችን እና የኃይል አሰላለፍ| የፖለቲካ ምህዳሩን የሚያኮስም አዋጅ?

ምስል

#የኩርፊያ #ፖሊሲ እና የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ።

  #የኩርፊያ #ፖሊሲ እና የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ።   "ለተከፋ ማጭድ አታውሰው።"    "ከፍትፍቱ ፊቱ።" "እንዳያማም ጥራው እንዳይበላም ግፋው።" የጤና ባለሙያወች ከጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ጋር የነበራቸው መቅድመ ግንኙነት እነኝህ ይተባህሎች ይገልጡልኛል።    "ጥበብን ከወደድሃት ትዕዛዙን ጠብቅ እግዚአብሄር ጥበብን ይሰጥሃል።" (መጽሐፍ ሲራክ ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፳፭)     ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ከማህበረ ቅንነት የጤና ባለሙያወች ጋር የሚያደርጉትን ውይይት በጥንቃቄ ስጠብቀው ነበር። ሕይወት፤ እስትንፋስ፤ ነፍስ፤ ሩህ፤ ሥጋ፤ ሰው፤ መኖር፤ ተስፋ ከእግዚአብሄር በታች ከሙያው ጋር በእጅጉ የተዋህዱ ስለሆነ በብርቱ ጥንቃቄ እና ማስተዋል ከጤና ጋር የተያያዙ ክስተቶች ሊያዙ ይገባል ባይም ነኝ።   በኢትዮጵያ የጤና ባለሙያወች ታሪክ ውስጥ " #እራበን ፤ ባለቤቴን #በሽሮ አረስኩ፤" ወዘተ የሚሉ የሁላችንም የህሊና ጓዳ የፈተኑ ክስተታዊ ሁነቶችን መከታተል የተገባ ስለነበር ተከታትየዋለሁኝ። በዚህ ዙሪያ በሌላ መድረክ "እኔም የደሞዝ ጥያቄ አለኝ" የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ሳስታውሳት #ውሽክ የምታደርግ ተረባዊ አገላለጽም ስትገርመኝ ሰነባብታለች።   እሳቸውም፤ ባለቤታቸው ቀዳሚ እመቤቱትም፤ እንዲሁም የካቢኔ አባሎቻቸውም #የሞድ ዲዛይነር ሲሳይ ሆነው እንደባጁ ልባቸው ያውቀዋል። ቤተመንግሥታቸው ፕሮቶኮሉ የአመጋገብ ሥርዓቱ ቡፌ ነው። የሰርክ ቡፌ። በሌላ በኩል ክብራቸው ተጠብቆ፤ በፈለጉት ጊዜ ለአጫጭር አገራዊ ጉዞ ኤሊኮፍተር፤ ረጅም ጉዞውን በአውሮፕላን ዓለምን እያዳረሱ የሚገኙት ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ፤ የኖቤል ተሸላሚ፥ እኔም የደሞዝ ...