ልጥፎች

የኢትዮጵያ ሴቶችን የደህንነት ዋስትና የሚያስጠብቅ ክብራቸውን የሚያስጠብቅ #አዲስ #ህግ #በእናት #ሥም ለኖረችው ኢትዮጵያ ያስፈልጋታል።

ምስል
  የኢትዮጵያ ሴቶችን የደህንነት ዋስትና የሚያስጠብቅ ክብራቸውን የሚያስጠብቅ #አዲስ #ህግ #በእናት #ሥም ለኖረችው ኢትዮጵያ ያስፈልጋታል።   የመጀመሪያዋ #ትምህርት ቤት እናት ናት። የመጀመሪያዋ የፊደል ገበታም እናት ናት።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።        ምዕራፍ ፲፯   #ጠብታ ።   እንዴት ሰነበታችሁ የቅንነት ክብረቶች? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። የኢትዮጵያ ሴቶች የኢትዮጵያዊነት ጽንሰ ሃሳብ ከተጸነሰ ጀምሮ የጎላውን ድርብ ድርሻ የተወጡ ጀግና የማህበረሰብ አካሎች ናቸው። በዲፕሎማሲው ዘርፍም ቀደምት ናቸው። በአገር መሪነትም መቅድም ናቸው።   የሆነ ሆኖ የሴቶች እናትነት ጸጋ ለማናቸውም ችግር የመፍቻ ቁልፍ ነው። ይህ ደግሞ ሰው - ሰራሽ፤ ጊዜ - ሠራሽ፤ ሥልጣን - ሠራሽ፤ ስልጣኔ - ሠራሽ፤ ዘመን - ሠራሽ ጉዳይ አይደለም። በፈጣሪ አምላካቸው/ በአላሃቸው ተባርኮ እና ተቀድሶ የተሰጣቸው ሰማያዊ ምርቃታቸው ነው።   የእናቶች ምርቃታቸው እንከን የለሽ ነው። ምርቃታቸው ጊዜ የማይሽረው ዘመን የማያወይበው ነው። ሴቶች አገቡም // አላገቡም፤ ወለዱም // አልወለደሙ ሴቶች የተፈጠሩበት ታላቅ ሚስጢር #እናትነት ነው። እናታዊነት ከእነ ሙሉ ጸጋው በእያንዳንዷ አንስት ውስጥ ተለብጦ ሳይሆን ተዋህዶ ማንነቷን አብርቶ እና አፍክቶ እንዲገኝ የሚያደርግ ንጥረ ነገር ነው። የሴቶች የማንነት ገላጭ ምስክራቸው እናታዊ ጸጋቸው ነው።    #እናታዊነት ።   * እናታዊነት ርህርህና ነው። ** እናታዊነት አዛኝነት ነው። *** እናታዊነት አጽናኝነት ነው። **** እናታዊነት አይዟችሁባይነት ነው። ***** እናታዊነት ቅን...

ኢትዮጵያ የገነፈለ ሁሉ #ፍላት ማጠራቀሚያ በርሚል አይደለችም። ሁልጊዜም "ማህረቤን ያያችሁ" ሰለቸን። ገለማን!

ምስል
  ኢትዮጵያ የገነፈለ ሁሉ #ፍላት ማጠራቀሚያ በርሚል አይደለችም። ሁልጊዜም "ማህረቤን ያያችሁ" ሰለቸን። ገለማን!   "አቤቱ ንጹህ ልቦና ፍጠርልኝ።" አሜን።        #ምዕራፍ ፲፯   #ጠብታ ።   የኢትዮጵያን ልኳን በልኳ ልክ መጠኖ መነሳት ይገባል። ለኢትዮጵያ የክት እና የዘወትር፤ የእዳሪ እና የቤት፤ ምርጥ ዘር እና አልባሌ፤ ዓይነታ እና አሰርውሃ የሚባል ጉዳይ የለም። የዜግነት እርቦ እና ሲሶ የለውምና። ሺ ሚሊዮን ጊዜ ይመስጠር፤ ይከደን የሃቅ አቅም ይንደዋል። ሁልጊዜ ልበጣ በስልቃ #ቃ ያለ ጉዞ ነውና።    #ኢትዮጵያ ለከበደችው ስኬቱ አይደለም ተሸፍኖ፤ ገሃድ ሆኖም ጋዳ ነው፤ ገድጋዳ - ገዳዳም።   ሰሞኑን የልጅ ሞገስ ሚዲያ እንደ ነገረን፥ ሰነዱንም አንብቦልናል፤ አሜሪካ ላይ የተቋቋመው ልክ ግንቦት 7 "አገር ማዳን" በሚል ለዛውም ግለሰቦችን ሳይሆን ግንቦቲዝም ተቋማትን ነበር ያሰባሰበው። ያው በአሰልቺው ድግግሞሽ "ኢትዮጵያን ማዳን" በሚል እራሱን #የፈራ ፤ እራሱን የሸሸ ቡድን "አገርን ስለማዳን" ቅርንጫፋን አውሮፓ አምስተርዳም ላይ እንደ ፈጠረ ዜናውን ነግሮናል።    ልጅ ሞገስ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ በትጋት እየተሳተፈ፤ አውሮፓ ተቀምጦ ስለምን እንዳላከሉት አላውቅም። የሆነ ሆኖ በግልጽ ቀርቦ ቀጥተኛ ፍላጎትን፤ ዓላማ እና ግብን ማሳወቅ የቲሙ መብት ሳይሆን ግዴታው ነው።    እነኝህ ክንብንብ ያሰኛቸው እነማን ናቸው??? ኢትዮጵያ እኮ ሉዓላዊ የተከበረች አገር ናት። በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ዕውቅና ላላት አገር፤ በገሃድ ላለች፤ ዓለም በብዙ ሁነቶች ለሚያውቃት ቀደምት አገር በስውር ቲም ትንሳኤሽን እናመጣለን #ጠብቂኝ የገ...

#ወፍሽ።

  #ወፍሽ ። ምዕራፍ ፲፯ "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። ቀንሽ ራሄል … እንደ እኔው ሲዋልል ጥንካሬሽ ቢያባብል አሳሩ ግን #ድንብልብል ። የመከፋት ተራራ ዝልብልብ የሂደት ጉዞ ጉስቁልቁል። ልጄ ልብስ የለው መንገድ አዳሪ ዋስትና ያጣ መንገድ ላይ ቀሪ። ሞፈር ቀንበሩ ዝናብ ጠባቂ ምርተ - ውጤቱ ያልሆነ በቂ፤ #ጀንዴ የሌለው #ተስፋን ናፋቂ #ገሳ ለባሹ ለራብ ተጠቂ። ድሆኖው ባዶ ሲሳይ የነሳው ተምቹ ትንኙ ፋታ ያሳጣው፤ ጥማቱ #ጠኔው የሚነስተው በሽታ ዱላው የከተከተው። እልፈተ ቢሱ ያነ……… #ገበሬ ራዕዩን ሁሉ በላበት አውሬ። ላዋይሽ ራሄል እስኪ ነይ እባክሽ እናቴ አንድ በይ። ለምዕተ ዓመታት በአንድ #ከፈን አቶ #ማለፍን በመለመን፤ እህህ ሆነው የእሱ ዝግን የበሬው ጌታ ፍሬዘር። #የእናት አገር ምሬት። #ህዳር 3 ቀን 2001 ዓ.ም ሲዊዘርላንድ ሄርሽን ሆቴል። መክሊት የአዋቂወች የግጥም መድብል ከገጽ 98 -99 ለህትምት የበቃ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 23/10/2025 ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው።