ልጥፎች

10 ጎል ከመረብ ጋር #የተጋባበት የደረጃ ጨዋታ።

  10 ጎል ከመረብ ጋር #የተጋባበት የደረጃ ጨዋታ።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   የመጀመሪያው ግማሽ ጨዋታ በእንግሊዝ 4 ፈረንሳይ ምንም በሆነ ውጤት ፈረንሳዮች ምን ነካቸው የሚል የቤት ሥራ ለተመልካች #ሸልመው ግራ ቀኙ ተጫዋቾች ወደ እረፍት አመሩ።   ከእረፍት መልስ ፈረንሳዮች ተጠናክረው ገብተው ሦስት ጎል አስገቡ። እንግሊዞች #የቅጣት ምት አገኙ እና ከ4 ወደ 5 ከፍ አሉ። ፈረንሳዮች የማጥቃት እንቅስቃሴያቸውን ቀጥለው አንድ በመጨመር ወደ 4 አደጉ። ይህን ጊዜ ጨዋታው ሊራዘም ይችላል የሚል ተስፋ ቢጤም ነበር። ነገር ግን እንግሊዞች 1 አክለው 6 እንዳሉ ጨዋታው #ተጠናቀቀ ።   በደረጃ ጨዋታ ይህን ያህል ጎል በጣም ብዙ ነው። የእንግሊዞች በአርጀንቲና መሸነፍ፣ የፈረንሳይ ደረጃውን ስፔኖች መውሰድ #የመድከም ፣ #የመዛል ሊሆን ይችላል።   በዚህ ጨዋታ #ማፔ ሁለት ጎል አስገብቷል። ቢጠነክር ዛሬ ተጨማሪ ጎሎችንም መጨመር ይችል ነበር። #የወርቅ ጫማዋ ብትቀናው ምኞቴ ነው።   #የወርቅ ቀለበትም ተዘጋጅቷል አሉ። እኔ አይደለም ያልኩት። ቢቢሲ ነው። ነገ ለፍፃሜ አርጀንቲና እና ስፔን ይጋጠማሉ። የነገ ሰው ይበለን። አሜን። ጨዋታው በመደበኛ ጊዜ ነው የተጠናቀቀው። #ደክሟቸዋል #ይረፋ ። የእንግሊዞች የደረጃ ሽልማት እዬተሰጠ ነው። #ሦስተኛ ደረጃ ይዘው።   ጨዋታውን ይህ ዓይነት ነበር ለማለት አልቻልኩም። ደንብ እና ህግ ስለሆነ ብቻ የከወኑት ነው የሚመስለው። #የማይቀርበት ስለሆነ።   ሥርጉተ©ሥላሴ። Sergute©Selassie. 19/07/026

ለኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር #ህሊናው ሊሆን የሚገባው #ኦርጋኒክ ሰብዕና ያለው አቶ ኦባንግ ሜቶ ነበር።

  ለኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር #ህሊናው ሊሆን የሚገባው #ኦርጋኒክ ሰብዕና ያለው አቶ ኦባንግ ሜቶ ነበር።   "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"   #ምዕራፍ ፲፱።   ኦባንግሻ #ለፈላስፊት ኢትዮጵያ #ኦርጋኒክ ማንነት፣ #ልኩ ኦርጋኒክ ሰብዕናው የሚመጥን ነበር። ሁልጊዜ ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት እነቃለሁ። እንደ ነቃሁ የሚያስቀጥል ሃሳብ አዕምሮዬ ካመነጨ ይህንኑ አዲስ ሃሳብ እያጠናሁ ይነጋል።   ዛሬ ሌሊት ኦባንግሻን አሰብኩት #ዘለግ አድርጌ። ሁልጊዜም አስብለታለሁኝ። ምክክሩ ከወደ ጋንቤላ አዲስ "ምክክር" የሚባል ቤቢ አግኝቷል። ስሙም " #ምክክር " ነው። ይደግልን። አሜን።    ከንቲባ ወሮ አዳነች አበቤ የአራስ ወጉን ሲያደርሱ አይቻለሁ። ይህ መልካም ነገር ነው። መልካም ነገርን የማነወር ሰብዕና የለኝም። እንዲለመልም መመኜት እንጂ።    ለነገሩ አንዷ አክስቴ #መልካም ሰው፣ ሌላዋ #ደግ ሰው ይሉኝ ነበር። ጸጥ ያልኩ፣ ያለኝን ሁሉ የምሰጥ የልጅነት ጊዜ ነበረኝ። አዲስ ለተገኜው የጋንቤላው ልዩ ህፃን የተደረገው እንክብካቤ #ማለፊያ ነው። የዓለምን የሚዲያ አውታር ያጨናነቀው የስፔኑ ያማል ታናሽ ወንድም ነው። ብርቅ ድንቅ ደጋፊነቱ ልዩ አትኩሮት ስቧል። ሁለቱንም ዓለም አደነቀ።   ልዩ የሰብአዊነት አቅም የኢትዮጵያ #አንከር አቶ ኦባንግ ሜቶስ? ለአዲሱ ቤቢ ክብር፣ እንክብካቤ ጥሩ ነገር ነው። የትናንቱ የኢትዮጵያ ባለውለታ መኖሩን እንኳን ለማወቅ አለመቻላችን ያሳስባል።   ኦባንግሻን የበላ ጅብ አልጮኽ አለ። አይደለም ኢትዮጵያ #አህጉራችን ሊወክል የሚችል #አብነታዊ ሰብዕና ያለው። አምኖ፣ አገሩ ገብቶ፣ ንጹህ #መታመን ከድቶት እንዲህ ዝግትግት ባለ መረጃ አልቦ...

ግን የት ደረሰ?

  "ኑ አገራችሁን ግቡ።" ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ። "ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ኢትዮጵያ ነን።" ግን የት ደረሰ?   "ቀን የሚያመጣውን ምን እንደሆነ አታውቅምና ነገ በሚሆነው አትመካ።" (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳፯ ቁጥር ፩)   #ምዕራፍ ፲፱።   "ኑ አገራችሁን ግቡ። #ስንኖር ኢትዮጵያዊ፤ #ስንሞት ኢትዮጵያ" በምልሰት የሚጠይቅ አገላለጽ ነው። ብለህ ነበር፤ ያልከው ሆኖን፤ ምን አሳካህ፤ ምንስ አጎደልክ የሚል የህሊና ሙግት ጋር እራስን #ያገጣጥማል ።   ስንኙ - ያማልላል። ውስጥን - ይደላል። ግን ገቢር ላይ ተፈትኖ የወደቀ ጽንሰ ሐሳብ ነው። በውስጡ የሌለ ጭብጥ ዕውንነቱ ከመፈጠሩ በፊት #ክስመቱን ስለሚያውጅ።   ቀድሞ ነገር ኢትዮጵያ #የማን ናት? ኢትዮጵያን #የሚያዝባትስ ማነው? ለኢትዮጵያዊነት ዜግነት ሰጩ፤ #ነሹስ ማን ነው? #ኢትዮጵያዊነት በገብያ ንግድስ ይተዳደራልን?   የገዘፋ ጥያቄወችን በዚህ ዙሪያ በብዙ ማንሳት ይቻላል። መላሽ ካገኙ። እንደ እኔ እምነት ኢትዮጵያዊነት በገብያ ህግ ሊተደደር አይችልም። ኢትዮጵያም የኢትዮጵውያን ናት። ኢትዮጵያን የሚያዛት፤ መታዘዝ ካለባት ህዝቧ ብቻ እንጂ አንድ የፖለቲካ ድርጅት ወይንም፤ አንድ ዞግ ሊሆን አይችልም።    ለኢትዮጵያ ዜግነት ሰጩም ነሹም፤ ውጡ ግቡም ብሎ የመበየን የአንድ የፖለቲካ ድርጅት መሪ ሥልጣን በፍጹም አይደለም። ሊሆንም አይችልም።    በማንነት ጉዳይ የሚሰጠው ብይን የግንዛቤ እጥረት ወይንም አቃሎ የማየት፤ ወይንም የውስጥ ቀውስን ለማስታገስ ካልሆነ በስተቀር የማንነት ጉዳይ አገር፤ አህጉር፤ ሉላዊ በሆነ መንፈስ ስናዬው ለሰው ልጅ የተሰጠው የነፃነት መንበር፣ ላዕላይ የሆነ የክብሩ መገለጫ፣...

#ጉግሱ #በአርጀንቲና አሸናፊነት ተጠናቀቀ።

  #ጉግሱ #በአርጀንቲና አሸናፊነት ተጠናቀቀ።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።   ጉዳዩ ፖለቲካል ኢሹም የታከለበት ስለሆነ የመጀመሪያው የጨዋታ ጊዜ አየሩ አግሬሲብ ነበር። የማሸነፍ እና የመሸነፍ ጉዳይ ሌላ የውስጥ አጀንዳ ስለነበረበት ከበድ ይል ነበር።   የሆነ ሆኖ ከግማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በኋላ ቀድሞ እንግሊዝ ባስገባው ጎል ሌላ ትዕይንት ተፈጠረ። ውጤቱም የአርጀንቲና #ሁለት እንግሊዝ #አንድ በማግኜት በመደበኛ የጨዋታ ጊዜ ተጠናቀቀ።   የመጀመሪያው ግማሽ የጨዋታ ጊዜ #አስፈሪ ነበር። አየሩ እራሱ አግሬሲብ ነበር። የአርጀንቲናው 17 ቁጥር ነገረ ሥራው ያስፈራ ነበር። በኋላ ተቀይሯል።   አየሩ ረጋ ያለው፤ ትንሽ ሻል ያለው ከመጀመሪያው #ከውሃ እረፍት በኋላ ነበር። እስከ ውሃ እረፍት በነበረው ጊዜ በሁለቱም ተፋላሚ ቡድኖች ማህከል ግብ አካባቢ ሙከራ አድርገዋል።   ከመደበኛ እረፍት በኋላ 54.27 ደቂቃ ላይ እንግሊዞች ከመረብ ጋር #የታረቀ አንድ ጎል አስቆጠሩ። ይህን ጊዜ አርጀንቲናወች አቅማቸውን ጨምረው ፍልሚያውን #አፋሙት ።   አርጀንቲናወች ብዙ #የማዕዘን ምት ዕድል አግኝተዋል። በተጨማሪም የእጅ ኳስ ውርወራም ዕድል በስፋት ቀንቷቸዋል። ግን መረብ እና ኳስ ለረጅም ጊዜ #መታረቅ አልቻሉም ነበር።   እንግሊዝ ቡድን አንድ ጎል #ቀድሞ ካስገባ በኋላ ግን በተከታታይ በእንግሊዝ መረብ ላይ አርጀንቲናወች ጥቃቱን ቀጠሉ። በተከታታይ እና በትጋት የእንግሊዞችን መደበኛ ሜድ ከበው ተከታታይ ጥረት አደረጉ። አሳኩም።   አርጀንቲናወች በብዙ #አታካች ሙከራ #ላባቸውን ጠብ አድርገው በጥረታቸው የመጀመሪያውን የአቻነት ችቦ 85...