#በአገራቸው ፓርላማ #ስደት ላይ የነበሩት የህዝብ ተመራጭ እንደራሴ ዶር ደስአለኝ ጫኔ #በቃኝ! አሉ።
#በአገራቸው ፓርላማ #ስደት ላይ የነበሩት የህዝብ ተመራጭ እንደራሴ ዶር ደስአለኝ ጫኔ #በቃኝ ! አሉ። "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።" #ምዕራፍ ፲፰። የዜግነት እርቦ፤ የዜግነት ሲሶ፤ የዜግነት እኩሌታ ያዬሁበት የፓርላማ ጊዜ ነበር ዶር ደሳለኝ ጫኔ እና አራት ጓዶቻቸው በህዝብ ሙሉ ድምጽ ተመርጠው አህዱን …… ክለቱን……… ሰለስቱ……… አርባዕቱ ………፭ኛው ዓመት እንሆ በጣት የሚቆጠሩ ወራት ቀሩ። ለኢትዮጵያ ፓርላማ #የመተንፈሻ #ቧንቧ የነበሩት የህዝብ እንደራሴው ዶር ደስአለኝ ጫኔ #በቃኝ ! ሲያንስ ነው ባይ ነኝ። ለምን? ያን ሁሉ ግልምጫ፤ ያን ሁሉ ስላቅ፤ ያን ሁሉ መዘባበቻነት፤ ያን ሁሉ ግልምጫ፤ ያን ሁሉ መታፈን፤ ያን ሁሉ የሰው ክቡሩነት የተናቀበት ሂደት ተሸክመው እዚህ መድረሳቸው የሚገርመኝ፤ የሚደንቀኝ ገጠመኝ ነበር። እኔ በተፈጥሮዬ መጀመሪያ የማዬው #ገጽን ነው። ገጹ የተከፋ የማንኛውም ሰብዕ ሁነት ከተመለከትኩ፤ ከዛች ቅጽበት ጀምሮ #ወራጅ አለ ነው። #እንዲህም ሆነላችሁ። በአንድ ወቅት ህዝባዊ ስብሰባ በርን ነበር። ከቪንተርቱር በርን በራሴ ወጪ ተጓጉዤ ሄድኩኝ። የጋበዙኝ ሰወች፤ ለማደሪያም ቦታ እንደተዘጋጀልኝ ተነግሮኝ ነበር የሄድኩት። ቃል የገቡት ግን አልተገኙም። እኔ ግን ቀድሜ ተገኜሁኝ። የተፈለግሁበት መሠረታዊ ምክንያት #አሽሙር እንዳደምጥ ነበር። እኔ ሥርጉተሥላሴ የየትኛውም የፖለቲካ ድርጅት ቁሮ እንጨት ወይንም ልጥፍ ከሰል ለመሆን መቼውንም አልፈቅድም። የራሴ እንደራሴ እራሴው ነኝ። እናላችሁማ #ቆፍጣናዋ ጎንደሬ የሄደችው " #የፈራ ይመለስ" 500 ወጣቶች ቲሸርት በራሳቸው ወጪ አሰርተው የበዓቴ አንበሶች ህ...