ልጥፎች

• #ብሄዊ የምህረት ዓዋጅ አስፈላጊነት እና፤ ለአፈፃጸሙ አክብሮትን ስለመመገብ።

ምስል
  • #ብሄዊ የምህረት ዓዋጅ አስፈላጊነት እና፤ ለአፈፃጸሙ አክብሮትን ስለመመገብ።        #ብሄዊ የምህረት ዓዋጅ አስፈላጊነት እና፤ ለአፈፃጸሙ አክብሮትን ስለመመገብ።    የምህረት ዓዋጁ ዱርቤቴ ላሉት ብቻ አይደለም፤ ተንሳፎ ላለው የብልጽግና አካላቱ ጭምር ነው። በሌላ በኩል በፋኖ ምክንያት የታሠሩ የአማራ ልጆች የምህረቱ ማዕከላዊ እንብርት ሊሆን ይገባል። የአማራ ሊቃናት ወላጆች፤ ልጆች፤ ጉልቻወች፤ እጮኛወች፤ ሙያወች፤ ተመክሮወች ተሰቃይተዋል። ይህ ስቃይ በብሄራዊ ሃቀኛ ምህረት እልባት ሊያገኝ ይገባል።   አፋር በርሃ ላይ ታሥረው ስለነበሩት የአማራ የጸጥታ አካላትን ሁሉ ምህረቱ ሊያካታቸው ይገባል። በአማራ ክልል በባህርዳር፤ በዞን እና በወረዳ ያሉ ሺህ የአማራ እስረኞች በምህረት ከካቴና ጋር እንዲፋቱ ሊደረግ ይገባል። ዊዝደም ማለት ለመሪነት ብልህነትን መመገብ ማለትም ነው። ብልህነት ብልጠት አይደለም። ጥበብ እንጂ። ክህሎት እንጂ።    የአማራ እና ወህ ልትል ይገባል። እኔም እረፍት እፈልጋለሁኝ። በጣም ውስብስብ፤ የተፍተለተለ ችግር ውስጥ ነው ክልሉ ያለው። እንደ አገር ኢትዮጵያም የአማራን ህዝብ ቅንነት፤ ገራገርነት ልታጣ አይገባትም። አክብሮ መነሳት፤ ጠንክሮ በማስተዋል መትጋት፤ በብልህነት መከራውን እያዬ ያለውን ህዝብ አለሁልህ ማለት ይገባል። በጥልቀት እንሰበው። በሰፊነትም እንመርምረው። የፋኖ ውስጥነትን በአትኩሮት በፖለቲካ ልቅና ማስተዳደር ይገባል። የህዝባችን ውስጡ፤ ቃናው ምን ምን እንደሚል በእርጋታ፤ በተከታታይ አንዳንዱንም እየደገምኩኝ አዳምጨዋለሁኝ።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   ምዕራፍ ፲፯። በዚህ ዘለግ ባለ የወግ...

#የኤርትራ የፖለቲካ ሊቃናት መሻት የኢትዮጵያ ፖለቲካ #ማስተር ማይንድ መሆን ነው። የጹሁፌ መነሻ የBBC ዘገባ ነው። አያዠዋለሁም።

ምስል
  #የኤርትራ የፖለቲካ ሊቃናት መሻት የኢትዮጵያ ፖለቲካ #ማስተር ማይንድ መሆን ነው።    ዘገባው የBBC ነው። እንዳይቆራረጥ ተያያዥ ጉዳዮችን በዬሰዓቱ የወጡ መረጃውን ያካተተ ዘገባ ስለሆነ ይመለከተናል። ስለዚህ ሙሉውን አያይዤዋለሁኝ።   • የአሜሪካ መንግስት እስራኤል ለሱማሌ ላንድ የሰጠችውን እውቅና ካጸደቀ አሁን ያለው የዓለም ፖለቲካ መጨናነቅ ረብ ይላል። ይህ ደግሞ አይቀሬ ነው። አንድ ዴሞክራሲን ዕውን ያደረገ ራስ ገዝ አስተዳደር፤ ወሳኝ ለጂኦ ፖለቲክሱ ወሳኝ ሚና ያለው ቦታ የምኞቱ ስኬት ቅርብ ነው። ቢቢሲ ዛሬን አህዱ ያለበትን ተጨማሪ ማብራሪያ አክያለሁኝ። የሰሞናቱ መስማማት ግርም ብሎኛል።   https://www.bbc.com/amharic/live/cy8jldx8vp3t "የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት እስራኤል ለሶማሊላንድ እውቅና መስጠቷን ተከትሎ አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ" https://www.bbc.com/amharic/articles/c623py0j3xpo "የሶማሊላንድ የዕውቅና ጉዞ እና የእስራኤል ውሳኔ ቀጠናዊ አንድምታዎች #ቆራጣ ዕይታዬን አክላለሁኝ።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       ለሱማሌላንድ እስራኤል ከሰጠችው የዕውቅና ደፋር መግለጫ ባላነሰ ኢትዮጵያ ሰፊውን የዴፕሎማሲ ተግባር ሰርታላቸዋለች። ምርጫቸውን ዓለም በትጋት የተከታተለላቸው በኢትዮጵያ ምክንያት ነበር ብዬ አምናለሁኝ። ለአሁኑ የእስራኤል ውሳኔ አደፋፋሪው የኢትዮጵያ እና የሱማሌ ላንድ ለጋ ያልጠና ስምምነት ነበር ብዬ አስባለሁኝ።   የኢጋድ አቋም አልገባኝም። ባይቸኩል፤ ገለልተኛ ሆኖ ቢቆይ ጥሩ ነበር ብዬ አስባለሁኝ። በሌላ በኩል እስራኤል ለወሰደችው ደፋር ጥንቅቅ ያለ...