• #ብሄዊ የምህረት ዓዋጅ አስፈላጊነት እና፤ ለአፈፃጸሙ አክብሮትን ስለመመገብ።
• #ብሄዊ የምህረት ዓዋጅ አስፈላጊነት እና፤ ለአፈፃጸሙ አክብሮትን ስለመመገብ። #ብሄዊ የምህረት ዓዋጅ አስፈላጊነት እና፤ ለአፈፃጸሙ አክብሮትን ስለመመገብ። የምህረት ዓዋጁ ዱርቤቴ ላሉት ብቻ አይደለም፤ ተንሳፎ ላለው የብልጽግና አካላቱ ጭምር ነው። በሌላ በኩል በፋኖ ምክንያት የታሠሩ የአማራ ልጆች የምህረቱ ማዕከላዊ እንብርት ሊሆን ይገባል። የአማራ ሊቃናት ወላጆች፤ ልጆች፤ ጉልቻወች፤ እጮኛወች፤ ሙያወች፤ ተመክሮወች ተሰቃይተዋል። ይህ ስቃይ በብሄራዊ ሃቀኛ ምህረት እልባት ሊያገኝ ይገባል። አፋር በርሃ ላይ ታሥረው ስለነበሩት የአማራ የጸጥታ አካላትን ሁሉ ምህረቱ ሊያካታቸው ይገባል። በአማራ ክልል በባህርዳር፤ በዞን እና በወረዳ ያሉ ሺህ የአማራ እስረኞች በምህረት ከካቴና ጋር እንዲፋቱ ሊደረግ ይገባል። ዊዝደም ማለት ለመሪነት ብልህነትን መመገብ ማለትም ነው። ብልህነት ብልጠት አይደለም። ጥበብ እንጂ። ክህሎት እንጂ። የአማራ እና ወህ ልትል ይገባል። እኔም እረፍት እፈልጋለሁኝ። በጣም ውስብስብ፤ የተፍተለተለ ችግር ውስጥ ነው ክልሉ ያለው። እንደ አገር ኢትዮጵያም የአማራን ህዝብ ቅንነት፤ ገራገርነት ልታጣ አይገባትም። አክብሮ መነሳት፤ ጠንክሮ በማስተዋል መትጋት፤ በብልህነት መከራውን እያዬ ያለውን ህዝብ አለሁልህ ማለት ይገባል። በጥልቀት እንሰበው። በሰፊነትም እንመርምረው። የፋኖ ውስጥነትን በአትኩሮት በፖለቲካ ልቅና ማስተዳደር ይገባል። የህዝባችን ውስጡ፤ ቃናው ምን ምን እንደሚል በእርጋታ፤ በተከታታይ አንዳንዱንም እየደገምኩኝ አዳምጨዋለሁኝ። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። ምዕራፍ ፲፯። በዚህ ዘለግ ባለ የወግ...