ልጥፎች

ዛሬ የምትሞግትለት ነገ አይገኝም። ጣሪያ ላይ ተንጠልጥሎ የራሱን #ኢንፓዬር ሲያንጽ ነው የሚገኜው።

 ፍቅር ሲጨንቀው ይጨንቃል። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 26/02/2022  ኢትዮጵያ ውስጥ ጭካኔ #ደልቧል ። #ፋፍቷልም ። ጨካኞች እንዲጨክኑ ኢትዮጵያ በጨካኝ መንፈስ እንድትታወክ ሊፈቀድ አይገባም። ፈጽሞ። የኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያዊነት #መለያ #ዓርማ ጭካኔ እንዲሆን በፍጹም ሊፈቀድ አይገባም።  ኢትዮጵያን ከየትኛውም ጥቃት ተባብረን ልናድናት የምንችለው በኢትዮጵያ ውስጥ ተሰግስገው የሚገኙትን የጭካኔ ሃሳብ አራማጆችን #ሃግ ባይ ንጹህ ተቋም ሲኖር፤ በተጨማሪም፤ ጨካኞች እንዳይደላቸው ሰዋዊ ህጎችን ሥራ ላይ ለመዋል ሲወሰን፤ ለተግባራዊነቱ አብይዝም #ቁርጠኛ ሲሆን ነው።  በቃን! ጭካኔ። በቃ! መጨካከን። ሰው ከማትረፍ፤ ጓድን ከማዳን ይልቅ አሳልፎ መስጠት መንፈሱ ጲላጦሳዊ ነው። #ማዳን ቢያቅት የጭካኔ ማዳበሪያ መሆን #ይሰቀጥጣል ። የእኔ ክብሮች የኔወቹ ክፋ ሃሳብ እና ማህበርተኞቹን ቢያንስ #ሃግ እንበላቸው።  ሥርጉትሻ 27/02/2026    ከሥርጉትሻ ቤት የየትኛውም የፖለቲካ ድርጅት ደጋፊ መሪ ሊሆን ይችላል፤ ስድብ፤ ዘለፋ፤ ንቀት፤ በፎቶ ላይ ኤክስ ማድረግ፤ ፎቶ መዘቅዘቅ፤ የሰውን ልጅ እንሰሳዊ አድርጎ በፎቶ ሾፕ መስራት፤ ፆታዊ ያልተገቡ ቃላት፤ እያሉን ግን ነውረኛ የሆኑ ቃላት ልንጠቀምባቸው የማይገቡ ለምሳሌ "ጋለሞታ" ወዘተ አይፈቀድም። መራራ ስንብት ይሆናል። ይህ ትውልዱ በትክክለኛ የኢትዮጵያኒዝም ኦርጋኒክ ተፈጥሮ ልክ የሚበጅ ሃሳብ የሚያስተናግድ ፔጅ ነው። ወገንተኝነቱ ለመርህ እና ለፋክት ብቻ። #ሥርጉትሻ በነጣ አገልጋይ። መልካም ቀን። አሜን።  27/02/2026   ለኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ፖለቲከኞች ሰው ልጅ ብልህነት፤ ትጋት፤ ቅን ዕ...

ኢትዮጵያን ቁም ነገር የማድረግ ዓላማ በመሆን ውስጥ ይታያል።

ምስል
  ኢትዮጵያን ቁም ነገር የማድረግ ዓላማ በመሆን ውስጥ ይታያል።   ዕለተ አርብ ዕለተ ኢትዮጵያ! በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ።    „እግዚአብሄር የርስቴ እድል ፈንታና ጽዋዬ ነው።“ (መዝሙር ፲፭ ቁጥር ፭)     • መቅደመ ነገር። ቅኖቹ እኔ የምጽፈው ለቅኖቹ ብቻ ነው። የሰከኑ የረጉ መንፈሶች ብቻ ናቸው የመንፈስ ኃብታቴ ስኩን ታዳሚዎች። የቁጥር ተማሪ አይደለሁም። ለቁጥር ነዶ አይደለም እኔ እምተጋው። ለጥራት ፍሬ ዘር እንጅ።   በሌላ በኩል ጠማማ እቃናለሁ ካለ መብቱ ነው። ውሃ በቀጠነ ካለ አቅሙ እዬመጣ የአቲካራ አርኬቡ እክፍታለሁ ካለ ግን እልፍኜን ጥሎ ወለቅ ነው። የእኔ የህይወት ፍልስፍናም አይገባውምና። በመደዴ አይደፈርም። ስለዚህ ሜዳውም ፈረሱም …   … እልህ ፖለቲካ አይደለም። እልህ ምቹ ያልሆነ ገረጭራጫ የገረዘዘ ድወዬ በሽታ ነው። የእኔ ዕልፍኝ የጎንድ ተክለኃይማኖት ጠበል የለውም። ምን አልባት ለተደማሪ እና ለግንቦት 7 ቅሪተ አካል እዛ ኦዳ ቤተ -መንግሥት የተከፈተ የሥነ - ልቦና ማገገሚያ አለና ብቅ ይበል … ብራናዬን ለቀቅ።    • እፍታ።    አዎን ይታያል። አዎን የሚታይ ነው። አዎን መልክ ቅርጽ ገጽ አቋም አለው። አዎንታዊነት መነሻው ከአዎን ነው። አዎንታዊ ሰብዕናዎች ኢትዮጵያን ቁምነገር የማድረግ ዓላማ እና ግብ ያላቸው አሉ።   በአስተዳደግ መበደልም ይሁን በማላውቀው ሁኔታ ሙሉ ገጸ ባህሪያቸው አሉታዊ የሆኑ ደግሞ ይገጥማሉ። አዎን የሚሉት ጥፋትን ሊሆን ይችላል። ወይንም ክፋትን። ወይንም ጦርነትን። ወይንም ግጭትን። እንደዚህ ዓይነት ሰብዕናቸው ለአገር መድካማቸውም አይቀር...

ዓለማቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከላካይ ቡድን (ሲፒጄ)፣

  ዓለማቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከላካይ ቡድን (ሲፒጄ)፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት የበይነ መረብ ጋዜጠኞች ለሆኑት ጎበዜ ሲሳይ፣ መስከረም አበራ፣ ገነት እስማማው እና ዳዊት በጋሻው "ፍትሃዊ" እና "ግልጽ የሆነ" የፍርድ ሂደት እንዲያሠፍኑ ዛሬ ባስተላለፈው መልዕክት ጠየቀ።    አራቱ ጋዜጠኞች በአማራ ክልል በተከሠተው ግጭት ሳቢያ ለሦስት ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ በእስር ላይ መሆናቸውን የገለጠው ተቋሙ፣ ጋዜጠኞቹ የተከሰሱበት የሽብር ወንጀል የሞት ቅጣት ወይም የእድሜ ልክ እስራት ሊያስቀጣ የሚችል መሆኑን ጠቅሷል።    ተከሳሾቹ ጋዜጠኞች በመጪው ሚያዝያ 23 የክስ መከላከያቸውን እንዲያቀርቡ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ባለፈው ጥር 28 ቀን ባዋለው ችሎት ማዘዙን ዋዜማ በወቅቱ መዘገቧ አይዘነጋም።   ዋዜማ ራዲዮ February 24, 2026

በአሁኑ ወቅት ዶር ሲሳይ አውግቼው የት ናቸው???

  የፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው #የመታፈናቸው ጉዳይ እጅግ አሳስቦኛል።   "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"   #ይድረስ ስለ ሰው ልጅ የመኖር መብት ግድ የሚላችሁ ንጹሃን ሁሉ።   ታፋኙ ዶር ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው ንጹህ በሆነ ሆኔታ ሙሁሩ #የሰባዓዊ #መብት ሁኔታ ግድ የሚላቸው ናቸው። #አዛኝ እና #አጽናኝ የማይደክሙ ናቸው። የሠሩት ቤት የኦነግ አማጽያን ሲያፈርሱት መልሰው አስተባብረው ያስገነቡታል።   እንዲህ ዓይነት #እናት #አንጀት ፤ #ሩህሩህ ፤ አዛኝ እና አጽናኝ ሰብዕና በእስር ዘመኑን እንዲገፋ መደረጉ አልበቃ ብሎ ፍርድ ቤት ውሳኔ ሰጠው ተብሎ #አፋኝ አዘጋጅቶ ሌላ ትራጀዲ መሥራት፤ የዲፕሎማሲው መስመር ላቀ፤ አደገ፤ ተመነደገ ለሚል መንግሥት ኢሜጁን እራሱ በራሱ #ያበላሸዋል ። ከሁሉም እግዚአብሄር ያዝናል።   በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ያለችበት ወከባ ምርጫው፤ የአገራት ርብርቦሽ እና ጥድፊያ፤ ፍጥጫው አገር ውስጡም ውጩም የሰከነ የፖለቲካ መስመር ይጠይቃል። እንዲህ መንፈስን የሚገምስ አሳዛኝ ትራጀዲ የማስተዋል #ፍቀት እንጂ ብልህነት አይደለም።   አሁን ጭንቀቴ የእኔ መሰወሩ በዘለቄታ #እንዳይቀጥል ፤ አካላቸውን #እንዳያጎድሉት ፤ #አዕምሯቸውን #እንዳያበላሹት ነው። የእያንዳንዱ ያፈኝ ሥነ - ልቦና እንዴት እንደተዋቀረ ይታወቃል። እራስ እግሩ #ጥላቻ ፤ እራስ እግሩ #በቀል እና #ቂም የጠጣን መንፈስ ለማስተካከል ተቋም እራሱ የለም። ህወሃት ያበቀለው የክፋ ሃሳብ ድፍድፍ እንዳለ ነው። ከእነ ሙሉ መዋቅሩ። በዚህ ዙሪያ ምንም አልተሰራም።   ጨካኞችን፤ በቀለኞችን፤ #ሃግ የሚል ተቋም የለም። ያሻቸውን ባሻቸው ልክ እስከፈለጉ ድረስ የክፋ ሃሳብ ሠራዊቶች እንዲፈጽሙ ተፈቅዶላቸ...

#የሃሳብ #ጭስ እና ዓለማችን። #በእኛ ባልሆነ ጊዜ አለመኖራችን ያመሳጠረ ክስተት። #ፈጣሪ አምላክ በካህሊ ሥልጣኑ ለዓለማችን #ሰላም ያውርድ። አሜን።

ምስል
  #የሃሳብ #ጭስ እና ዓለማችን። #በእኛ ባልሆነ ጊዜ አለመኖራችን ያመሳጠረ ክስተት። #ፈጣሪ አምላክ በካህሊ ሥልጣኑ ለዓለማችን #ሰላም ያውርድ። አሜን።   #ምዕራፍ ፲፰።   "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውለውምጽ።"   ግን ሦስት ዕርዕሰ ጉዳይን በአንድ የወግ ገበታ። እችለው ይሆን????   #የ27 /02/2026 የደጓ ቪንተርቱር የጨረቃ ነገር።   ዕለተ አርብ ከውጭ ቆይቼ ወደ ቤቴ ስገባ ሰማይ ማዬት ስለምወድ ዋና በራችን እዬከፈትኩ ሰማይን ተመለከትኩ። #ጨረቃ ወጥታለች። በእስልምና ዕምነት ዘንድ ረመዳን ተናፋቂ ፆም ነው። ፆሙ መጠናቀቁ የሚታወቀው ጨረቃ ከወጣች ነው። አሁን ፆሙ አጭር ጊዜ ላይ እያለ ስለምን ጨረቃ #እንደወጣች በቀን አልገባኝ ስላለ ቲክቶክም፤ ፌስቡኬ ላይም አጋራሁኝ። ጨረቃ ከወጣች ፆሙ ይቀጥላል፤ ወይንስ ይጠናቀቃል? እሱ ግራ ገብቶኝ ነበር ፖስት ያደረኩት።   የሆነ ሆኖ ሰላምሽ #ይባካን ወይንም አይረጋ የተባለችው ዓለማችን ጭስ ውስጥ ናት። በሃሳብ #ጭስ ውስጥ። ወይንም በዚህ ሂደት ዘላቂ ሰላም ይረጋገጣል ይሁን የፋመ ጦርነት ላይ በሁሉም አቅጣጫ ዓለማችን ተወጥራ ትገኛለች። ጦርነት ከማባራት ይልቅ እራሱን እያራባ፤ እራሱን እያሰፋ የዓለም ህዝብ በጦርነት ስጋት ላይ ይገኛል። ፈጣሪ አምላክ የዓለምን ሰላም መርቆ ያጽናልን። አሜን።   #የዕለቱ መሪ ዕርዕስ።    የኢራኑ ቁንጮ የሃይማኖት መሪ በሥጋ እንደተለዩ የዓለማችን በኽረ መሪ ዜና ሆኗል። ከምን ተነስተው የት እንደደረሱ፤ ፍፃሜውን አካቶ BBC ዘግቦታል። ይህን ዜና በብሥራትነት የሚዩት የመኖራቸውን ያህል፤ ይህን ዜና ሲሰሙ የሚደነግጡ፤ የሚያነቡ፤ የሚበሳጩ፤ እንደ ...