ልጥፎች

የመቶ አርባ ደቂቃ «ሁለት ሰዓት ከሃያ ደቂቃ» በቬንዙላ ዘጠና ደቂቃ በኢንተቤ ራሱን በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የደገመ ይመስለኛል።

ምስል
  የመቶ አርባ ደቂቃ «ሁለት ሰዓት ከሃያ ደቂቃ» በቬንዙላ ዘጠና ደቂቃ በኢንተቤ ራሱን በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የደገመ ይመስለኛል።   • መሪነት ጊዜን በማስተዋል መምራትን ይጠይቃል።   • የእኔ ዕይታ ሂደቱ ፍትሃዊ ነው ወይስ አይደለም የሚለው አይደለም። "ኦፕሬሽን አብስሉት ሪዞልቭ" (Operation Absolute Resolve) የኦፕሬሽኑ ቁመና የሰጠኝን ንድፈ ሃሳባዊ ግብረ መልስ የክንውን አቅም ነው የገለጽኩት። የዕይታየ መነሻ የBBC ዘገባ ነው። • ጫናን በሚመለከት፤ ወጀብ የሌለው፤ ሪስኩ የነጠፈበት የፖለቲካ ፍላጎት የለም። ፍትጊያ አለ። ፋክክር አለ። ሪስክም ይኖራል። በዚህ ውስጥ አልፎ ስኬቱ ዛን ሊመታ ስለመቻሉ ነው የቅድሚያ አትኩሮት ሊሆን የሚገባው። በአንድ ኦፕሬሽን ውስጥ መንሸራተትም ሊገጥም ይችላል። የመሪነት ልቅና የሚያስፈልገው ተዚህ ላይ ነው።   "አሜሪካ የቬንዙዌላውን ፕሬዝዳንት የያዘችበት ዘመቻ እንዴት ተከናወነ?"   https://www.bbc.com/amharic/articles/cedw940407go   «አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።» አሜን።   ይህን ረቂቅ ኦፕሬሽን ለውይይት ማቅረብ ከባድ ይሆናል። ፕሮሲጀራል ሂደቱን ህግ ተከትለን እናስኬደው ቢባል መስዋዕትነቱም ይከፋል፤ ግቡም ጎዳና ተዳዳሪ ይሆናል። የየትኛውም ከፍተኛ ኦፕሬሽን ስኬት ሚስጢር ነው። ሚስጢሩን ትንፋሽ እንስጠው ቢባል አይደለም ስኬት ራስን የማዳን ሂደቱ ይዝረከረካል ከምል ይዝለገለጋል።    አንድ ልዩ ኦፕሬሽን የቅድሚያ ቅድሚያ እራሱን የመጠበቅ፤ እራሱን የማዳን ቁመና ሊኖረው ይገባል። ለዚህ መሰል የበቃ የመምራት አቅም ደግሞ መሰጠትን ይጠይቃል።    ይህ ጥንቁቅ ኦፕሬሽን "ኦፕሬሽን አብስ...

Btte Gott.

ምስል
  ·          BiBtte Gott. O ! Gott, bitte beschütze das friedliche, humane, menschliche und natürliche Heilige Land Schweiz und seine Bevölkerung. Amen. Und möge Gott, unser Schöpfer, uns Frieden auf Erden schenken. Danke. Sergute © Selassie 02.01.2025 Schweiz, Wintertur. 

• #ብሄዊ የምህረት ዓዋጅ አስፈላጊነት እና፤ ለአፈፃጸሙ አክብሮትን ስለመመገብ።

ምስል
  • #ብሄዊ የምህረት ዓዋጅ አስፈላጊነት እና፤ ለአፈፃጸሙ አክብሮትን ስለመመገብ።        #ብሄዊ የምህረት ዓዋጅ አስፈላጊነት እና፤ ለአፈፃጸሙ አክብሮትን ስለመመገብ።    የምህረት ዓዋጁ ዱርቤቴ ላሉት ብቻ አይደለም፤ ተንሳፎ ላለው የብልጽግና አካላቱ ጭምር ነው። በሌላ በኩል በፋኖ ምክንያት የታሠሩ የአማራ ልጆች የምህረቱ ማዕከላዊ እንብርት ሊሆን ይገባል። የአማራ ሊቃናት ወላጆች፤ ልጆች፤ ጉልቻወች፤ እጮኛወች፤ ሙያወች፤ ተመክሮወች ተሰቃይተዋል። ይህ ስቃይ በብሄራዊ ሃቀኛ ምህረት እልባት ሊያገኝ ይገባል።   አፋር በርሃ ላይ ታሥረው ስለነበሩት የአማራ የጸጥታ አካላትን ሁሉ ምህረቱ ሊያካታቸው ይገባል። በአማራ ክልል በባህርዳር፤ በዞን እና በወረዳ ያሉ ሺህ የአማራ እስረኞች በምህረት ከካቴና ጋር እንዲፋቱ ሊደረግ ይገባል። ዊዝደም ማለት ለመሪነት ብልህነትን መመገብ ማለትም ነው። ብልህነት ብልጠት አይደለም። ጥበብ እንጂ። ክህሎት እንጂ።    የአማራ እና ወህ ልትል ይገባል። እኔም እረፍት እፈልጋለሁኝ። በጣም ውስብስብ፤ የተፍተለተለ ችግር ውስጥ ነው ክልሉ ያለው። እንደ አገር ኢትዮጵያም የአማራን ህዝብ ቅንነት፤ ገራገርነት ልታጣ አይገባትም። አክብሮ መነሳት፤ ጠንክሮ በማስተዋል መትጋት፤ በብልህነት መከራውን እያዬ ያለውን ህዝብ አለሁልህ ማለት ይገባል። በጥልቀት እንሰበው። በሰፊነትም እንመርምረው። የፋኖ ውስጥነትን በአትኩሮት በፖለቲካ ልቅና ማስተዳደር ይገባል። የህዝባችን ውስጡ፤ ቃናው ምን ምን እንደሚል በእርጋታ፤ በተከታታይ አንዳንዱንም እየደገምኩኝ አዳምጨዋለሁኝ።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   ምዕራፍ ፲፯። በዚህ ዘለግ ባለ የወግ...