ልጥፎች

የፖለቲካ እስረኞች ወገኖቼ #አዋን ይፈቱልኝ፤ በእስር ቤት እያሉ ወገኖቼ ጤናቸው ይጠበቅልኝ እንጂ አይደለም በአክብሮት እና በትህትና #ተንበርክኬ ብለምን የሚቀርብኝ ቅርጥፍጣፊ ክብር የለም።

ምስል
  የፖለቲካ እስረኞች ወገኖቼ #አዋን ይፈቱልኝ፤ በእስር ቤት እያሉ ወገኖቼ ጤናቸው ይጠበቅልኝ እንጂ አይደለም በአክብሮት እና በትህትና #ተንበርክኬ ብለምን የሚቀርብኝ ቅርጥፍጣፊ ክብር የለም።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።    #ምዕራፍ ፲፯      እኔ ሥርጉተ ሥላሴ ገና በጋሜ እና ታሬዬ ዘመን ጀምሮ ተከብሬ ነበር በፖለቲካ ተግባር ተኮትኩቼ ያደግኩት። እንደዛሬው ማህበራዊ ሚዲያ ቢኖር ከቶፕ ሁለገብ፤ ተከባሪወች እና ተወዳጆች መሃል የመሆን ዕድሉ የነበረኝ ሴት እሆን በነበረ።    ለእኔ የሙያ ብቃት፤ የሥራ ትጋት እና ቅልጥፍና ያግዛሉ በተባሉ መድረኮች ሁሉ እማርበት ዘንድ ሙሉ የዕድል በር የተከፈተልኝ ወጣት ነበርኩኝ። በእኔ ዘመን ዕንቁ ሴት ወጣቶች በርከት ያልን ነበርን። ከሁሉም ግን ለእኔ ይሰጥ የነበረው አትኩሮት እና፤ በእኔ ይጣል የነበረው ተስፋ ሰፊ ነበር።    ጎንደር ክፍለ አገር ብቻ ሳይሆን፤ ተወክዬ በሄድኩበት ቦታ ሁሉ ነበር። አርሲ ስመደብ ጢቾ በሠራሁ በሦስት ወሬ ነበር ለክፍለ አገር ኃላፊነት ሪኮመንድ የተደረግኩት። ተሰድጄም የሥራ ኢባሎሽኔ #A + ነው። #አገሬ #ሥራ ነውና። ያውም በበቃ ዲስፕሊን እና በትጋት። ሁሉንም የክብር አይነት አውቀዋለሁኝ። ለዚህም ነው ለውዳሴ፤ የማይደንቀኝ የማልንደፋደፈው ለጭብጨባ ሆነ ተከታይ ለማበራከት። በሌላ በኩል በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ብርቱ ናቸው ብዬ ለማምናቸው በገፍ የሰብዕና ግንባታ፤ ምስክርነት በቅንነት የመስጠት አቅሜም ምንጩ ይኽው ነው። በብዙ ሰው ድጋፍ ላይ ቁብ የለ ሰብዕና ስለአንድ ሰው ሰብዕና የመመስከር #አቅም የለውም። ለምን? ከእነሱ የተሻለ ሰብዕና እንዲወጣ ስለማይፈለግ። ...

#አደብ #ያጣ #ፍላጎት፤ #አደብ #ያጣ #ውድቀት #ያመጣል።

ምስል
  #አደብ #ያጣ #ፍላጎት ፤ #አደብ #ያጣ #ውድቀት #ያመጣል ። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። #ምዕራፍ ፲፯ #ለምን ? 1) ስኬት በአደብ ያጣ ፍላጎት ስለማይገኝ። 2) አደብ ያጣ ፍላጎት ቁንጥንጥ ነው። 3) አደብ ያጣ ፍላጎት ስርክራኪ ይበዛዋል። 4) አደብ ያጣ ፍላጎት ተናዳፊ ስለሆነ። 5) አደብ ያጣ ፍላጎት የውስጥ ሰላሙ የታወከ በመሆኑ። 6) የመነሻ ገፊ ፍላጎቱ የራሱ አቅም ሳይሆን የጥገኛ አቅም ተሰላቢ ስለሚሆን። 7) አደብ ያጣ ፍልጎት ጎርፍ ይበዛበታል።   ስምንት) አደብ ያጣ ፍላጎት በሦስት ወር የሰው ልጅ ጽንስ ልጅ ሆኖ እንደሚወለድ ነው የሚያስበው። ኢ ተፈጥሯዊ ነው። ሁሉም ነገር የራሱ ስበታዊ፤ ስክነታዊ ሂደት ይጠይቃል። በአገራችን ባህልም "የእነ ተሎ ተሎ ቤት ግድጌዳው ሰንበሌጥ።" 9) አደብ ያጣ ፍላጎት ውጥኑ ቀን ቢወጣለት እንኳን ዕድሉን ለማስቀጠል አደብ አይኖረውም። መነሻው ሶርሱ አደብ የለሽ ነውና። 10) አደብ ያጣ ፍላጎት አድራጊውም፤ ተደራጊውም ስክነት ከአጣ ሰብና ስለሚነሳ ያረገረገ ስለሚሆን። አንድ ፍላጎት #ያረገረገ ከሆነ ደግሞ የተነሳለትን ፍላጎት አጽንቶ ለማስቀጠል አቅም ያንሰዋል። የትኛውም የአቅም ዓይነት #በጀት ነው። የመንፈስ ይሁን የልምድ፤ የልምድ ይሁን የክህሎት፤ የክህሎት ይሁን የመሰጠት፤ የመሰጠት ይሁን የመንፈስ፤ የመንፈስ ይሁን የመዋዕለ ንዋይ አቅም በጀት ነው። የሂሳብ ሥራ ይጠይቃል። ለዚህ ዕውቅና መስጠት፤ አቅምን ማሰባሰብ፤ አቅምን ማደራጀት፤ አቅምን መርቶ ለስኬት ለማብቃት አደብ ወሳኝ ጉዳይ ነው። #ለምን ያረገርጋል አደብ የለሽ ፍላጎት? #ተርገብጋቢ ስለሚሆን። ገፊው ኃይል ያልተረጋጋ ስሜት ሊሆን ስለሚችል፤ ተርገብጋቢ ፍላጎትን ይዞ የግል ህይወትን፤ ማህ...

#ትህትና አንዱ #የስኬት #ጎዳና ነው።

ምስል
  #ትህትና አንዱ #የስኬት #ጎዳና ነው።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፯       ትህትና ለራስም የውስጥ ሰላም የሚሰጥ ልዩ የፈጣሪ አምላካችን፤ የአላሃችን ልዩ ስጦታ ነው። የፈለገ የከበደ፤ የገዘፈ ፈተና ቢገጥም ትሁታዊ አቀራረብ ሻካራውን ግንኙነት ልጎ አንፃራዊ ልስላሴ የመፍጠር አቅም ይኖራዋል። አንዳንድ ጊዜ ሳታስቡት እልህ የገቡ ሰብዕናወች ይገጥማሉ። እናንተ የተበሳጩበትን ሁነት ላታውቁ ትችላላችሁ።   ግን ግንኙነቱ ሳንክ እንደገጠመው ስትረዱ ምላሹን ግርጭርጭ መንፈስ ወደፊት ከማምጣት ይልቅ በትሁት መንፈስ ጉዳዩን ለማየት መፍቀድ ብዙ #የጎረቡ ጉዳዮች ፈውስ ሊሰጥ ይችላል። " ኃይል የእግዚአብሄር ነው።" ተስፋም ከእግዚአብሄር ዘንድ ነው። የተስፋ + የኃይል አቅም ትህትና ከታከለበት የስኬት ጎዳና ይጠረጋል።    ይህን በስማበለው ሳይሆን እኔ በዘመኔ ያዬሁት የዕውነት ገጠመኝ ነው። የእናቴ የእብዬ ትህትና ይከብደኝ ሁሉ ነበር። የእሺታዋ መጠነ ሰፊ አቅምም ይከብደኝ ነበር። እኔ ከእሷ መሐጸን መገኜቴ ብቻ ሳይሆን እንደ ጓደኛም አብሮ አደጎች ነበርን። ብዙ በጣም ብዙ ነገሮችን ከእናቴ ወርሻለሁኝ። አባቴ አቨይም የዝምታ ዘውድ ነበር። ስለሆነም ተበድየም ይቅርታ እምጠይቀው እኔው ነኝ። ካሳ ካለም እምክሰው እኔው እራሴ ነኝ። ከሁሉ የሚያስደስተኝ ስጦታ #መስጠት ፤ ደስታን በገፍ ማቅረብ ሲሆን ክንዋኔውም በትህትና ነው። ይህም በመሆኑ ውስጤ የጸና ሰላም አለው።   ቆፍጠን ማለትን በሚሹ የሥራ መስኮችም ቆፍጣና ነኝ። ሁልጊዜም በልኬ ነው መኖሬን መምራት እምሻው። እስር ቤትን አውቀዋለሁኝ። ስለዚህም እስር ቤት ያሉ ወገኖቼ ያሳስቡኛል። እስር ቤት እኮ #የ...

#የአማራን ልጅ #ስለኢትዮጵያዊነት #ለማስተማር ማሰቡ እራሱ #የውርንጫ ድካም ነው። #መቅኗችን ኢትዮጵያችን ናት።

ምስል
  #የአማራን ልጅ #ስለኢትዮጵያዊነት #ለማስተማር ማሰቡ እራሱ #የውርንጫ ድካም ነው።   #መቅኗችን ኢትዮጵያችን ናት።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።    #ምዕራፍ ፲፯       ክብሮቼ እንዴት አላችሁልኝ? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። የአማራ ወላጅ #ዶክትሬኑ #ኢትዮጵያዊነት ነው። የትኛውም ቦታ አማራ ልጁን ሲያሳድግ ደቡብ ይሁን ሰሜን። ስሜን ይሁን ምዕራብ። ምዕራብ ይሁን ምስራቅ ስለፈላስፊት ኢትዮጵያ ቅንነት #መቅኗችን ፤ ካልሽየሙ አድርጎ፤ መልቲ ቫይታሚኑ፤ ፕሮቲኑ፤ ሚኒራሉ፤ ንጥረ ነገሩ አድርጎ ነው ልጁን በኢትዮጵያኒዝም የከበረ ልዑቅ በራስ የመተማመን ተፈጥሯዊ ሙሉ አቅም እና ክህሎት አንፆ የሚያሳድገው። የአማራ ህዝብ በመላ ኢትዮጵያ በተለይ በከተሞች በስፋት ይገኛል። መገኜቱ ብቻ አይደለም፤ አብሮነቱን በጋብቻው፤ በቁቡ፤ በእድሩ፤ በቤተ አምልኮ ባዕቱ፤ በሥራ እና በመኖሪያው ሁሉ በተባ ኢትዮጵያዊነት አለምልሞ ነው የሚኖረው። ተጋብቶ ተዋልዶ። ተዛምዶ ተጎራብቶ። ተዋህዶ ተስማምቶ።    አሁን ከሆነም ውጭ አገርም በብዛት የአማራ ልጅ ይኖራል። የትም ይሁን የትም የአማራ ቅን ወላጅ የቅንነቱ መሠረት የሆነችውን ዩንቨርስ እናቱን ኢትዮጵያን የውስጥነቱ መገለጫ አድርጎ አስጠንቶ ነው የሚያሳድገው። ለዚህ እኮ ነው "የአማራ ……… ብሎ" ተደራጅቶ ኢትዮጵያዊነቱ ነግስ፤ የተነሳበትን ተልዕኮ ሳስቶ የሚታየው። ኢትዮጵያዊነት ለአማራ ህዝብ #እንደሬሰው ነው። ካፒቴኑ ነው። #የኖህ መርከቡም ነው። ይህ እንደ ባቢሎን ግንብ የሚናድ አይደለም። የታነጸበት ንጥረ ነገሩ ነው።   እና ኢትዮጵያዊነትን ለአማራ ህዝብ ለማስተማር ማሰቡ በራሱ #የውርንጫ ድካም ነው...