ልጥፎች

ሻ/ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ፍለጋ የሚዛመዱ ልጥፎች በማሳየት ላይ

የፖለቲካ ሥልጣን ትርምስ በቃኝ ማለት ብልህነት ነው፤

ምስል
የመፍትሄ መቋሚያ። „የሥራው ሁሉና የነገር ግዳጅ መጀመሪያ ምክር ነው።“ መፅሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፴፯ ቁጥር ፲፮ ከሥርጉተ©ሥላሴ 23.08.2018 ከጭምቷ ሲወዘርላንድ የፖለቲካ ሥልጣን ትርምስ በቃኝ ማለት ብልህነት ነው፤፡ የፖለቲካ ስልጣን ትርምስ በቃኝ ማለት ብልህነት ነው።  ራስንም የማሸነፍ ልዩ አቅም ነው። ስለሆነም  አመሰግነዎታለሁኝ።  ·      መነሻ። https://www.zehabesha.com/amharic/archives/93721 ‘ ለኢትዮጵያ ሕልውና አስጊ የሆኑ ድርጅቶች በመደመር ስም ያለ ቅድመ ሁኔታ መግባታቸው ያሰጋል ’ – ሻለቃ ዳዊት ወ / ጊዮርጊስ ·          ወግ! ጤና ይስጥልኝ የኔዎቹ እንዴት ናችሁ? ትናንት ማምሻ ላይ ይህን ቃለ ምልልስ አዳመጥኩተኝ። እርግጥ ነው ብዙም ደህና ስላልነበርኩኝ ምን እንደሚሰማኝ አልጻፍኩኝም። አሁን ትንሽ ልለት ፈለግኩኝ።  የለውጥ ተጋድሎ ሲጀመር VOA የአማርኛው ክፈለ ጊዜ ከሁለት የፖለቲካ ሊሂቃን ጋር ያደረገው ውይይት ነበር። ሦስት ተከታታይ ውይይት ነበረው። ተወያዮቹ ፕ/ ዳንኤል አበራ እና አቶ ያሬድ ጥበቡ ነበሩ። በውይይቱ ላይ ያልተመቹኝ ነገሮች ስለነበሩ „መቋሚያ“ በሚል እርስ ሃሳቤን ገልጬ ነበር። ከገለጽኩባቸው ነጥቦች አንዱ አቶ ያሬድ ጥበቡ በኢትዮጵያ ግጭት አያሰጋኝም ስላሉ ነበር። እኔ ደግሞ ዕድለኛ ነዎት እንቅልፍ ተኝተው ማደር ችለዋል፤ እኔ ግን እጅግ ያሰጋኛል ብዬ ሞግቻቸው ነበር። ያልኩትም አልቀረም እስከ 2 ሚሊዮን ወገኖቻችችን መፈናቀላቸው ብቻ ሳይሆን ከመፈናቅል ጋር ተያያዥ የሆኑ እጅግ አሰቃቂ የወገን ሰቆቃ ደርሷል። እንግዲህ ያን ጊዜ ነው። አሁን ደግሞ ባለው „የመደመር ፖለቲካ“

ኩርፍርፍ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ  ኩርፍርፍ። „ ሳቅን   እብድ   ነህ፤   ደስታንም፤ ---  ምን   ታደርጋለህ ?  አልኩት። “   መጽሐፈ   መክብብ   ፪   ቁጥር   ፪ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 27.04.2019 ከእመ ዝምታ ሲዊዘርላንድ ·        እ ፍታ። እንዴት ናችሁ የአገሬ ልጆች? ደህና ናችሁ ወይ? ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለባዕለ ስቅለት፤ ለቅዳምሱር ለትንሳኤ ዋዜማም አደረሳችሁ አደረሰን። ትናንት ስቅለት ነበር በህይወቴ የምውዳቸው ባዕላት የቅዱስ ዮሖንስ ዋዜማ በጎንደርኛ ምሽት እና የስቀለት በዓልን ነው። ጎንደር የተለያዬ ትውፊት አላት ስቅለትን ልጆች ሰብሰብ ብለው ሆምሻምሾ እየዘመሩ በዬቤቱ ዱቄት፤ ዘይት፤ ድልህ ይለምናሉ። ከዛ ከሙሴዋ ቤት ይቦካል፤ የተቦካው ጸሐይ ላይ ይቀመጣል ተነሳ አልተናሳ በዬሰዓቱ እዬሄድን እናዬዋለን። የሚገርማችሁ እጃቸው ቶሎ የሚያቦካም የሚባልላቸው ባለመክሊት አንስትም አሉ። የእኔ የእናቴ እናት ለዚህ ተፈላጊ ነበረች። እሷ ነው የምታቦካልን ለደብረብርሃን ልጆች … ሊጡ በቅጡ ሳይቦካ በለቱ ነው የሚጋገረው። የአንድ ቀን ሊጥ እንጀራ፤ ዓይኑ ቦግ ቦግ ያለው ማር ማር በሚለው እንጀራ ወጥ ተስርቶ በጋራ ይበላል። ትናንት ኤቢ አድበርታይዝመንት ቅምሻውን ልኮልን አይቻለሁኝ፤ በስንት ዓመቴ ማለት ነው። ሴቶችን ግን አላዬሁም። ለምን ማለቴ አልቀረም? ሴቶች የማይሳተፉበት የመስቀል ሆያ ሆዬን ምሽት ብቻ ነው። ያም ለወግ አጥባቂው የጎንደር ማህበረሰብ ሴቶችን በምሽት መፍቀድ ታሳቢ በማድረግ ይመስለኛል። ሹግም ለወንዶች የተሰጠ ድርሻ ይመስለኛል።     የቤተ እግዚአብሄሩን ውሎ አክሎበት ቢሆን ደግሞ የበለጠ ያምር ነበር ኤቢ