ልጥፎች

«በጠለምት በናዳ የተቀበሩ የሁለት ሰዎችን አስክሬን ለማውጣት ሲሞክሩ ከነበሩት የ7ቱ ሕይወት አለፈ" bbc

  https://www.bbc.com/amharic/articles/c0mnprenz00o «በጠለምት በናዳ የተቀበሩ የሁለት ሰዎችን አስክሬን ለማውጣት ሲሞክሩ ከነበሩት የ 7 ቱ ሕይወት አለፈ" 26 ነሐሴ 2024 "በአማራ ክልል፣ ሰሜን ጎንደር ዞን፣ ጠለምት ወረዳ አብና ቀበሌ በናዳ የተቀበሩ የሁለት ሰዎችን አስክሬን በመፈለግ ላይ ከነበሩት የ 7 ቱ ሕይወት ማለፉ ተገለጸ። የወረዳው አስተዳዳሪ ጋሻው እንግዳው ለቢቢሲ እንደገለጹት የሰባቱ ግለሰቦች ሕይወት ያለፈው ባለፈው ዐርብ ነሐሴ 17/2016 ዓ . ም . አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ባጋጠመ የመሬት መንሸራተት በመኖሪያ ቤታቸው ሳሉ በናዳ የተቀበሩ ሰዎችን በመፈለግ ላይ ሳሉ በድጋሚ በተከሰተ አደጋ ነው። በአደጋው እናትና ልጅን ጨምሮ የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የጠቀሱት አቶ ጋሻው፣ ክስተቱ ባጋጠመበት ወቅት የልጁ አስክሬን ወዲያው ሲገኝ የሁለቱ የቤተሰብ አባላት አስክሬን ግን ሳይገኝ እንዳደረ ተናግረዋል። በማግስቱ ቅዳሜ ነሐሴ 18/2016 ዓ . ም ጠዋትም የሁለቱን ሰዎች አስክሬን ለማውጣት የተሰባሰቡ ከ 18 በላይ የሚሆኑ ዘመድ አዝማድና የአካባቢው ነዋሪዎች ለፍለጋ በተሰማሩበት ወቅት ድጋሜ በተከሰተ ናዳ የሰባቱ ሰዎች ሕይወት አልፏል ብለዋል አስተዳዳሪው። በአደጋው ከሞቱት በተጨማሪም በስምንት ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል። በሁለቱም አደጋዎች ከሞቱት መካከል የአራት ሰዎች አስክሬን የተገኘ ሲሆን የቀሪዎቹ አለመገኘቱንና ፍለጋውም መቋረጡን

የbbc የአማርኛው ዘገባ። «ከ30 ዓመታት በላይ ሕይወቱን ለኪነጥበብ የሰጠው ኩራባቸው ደነቀ በወዳጆቹ እንዴት ይታወሳል?»

ምስል
      የbbc የአማርኛው ዘገባ። «ከ 30 ዓመታት በላይ ሕይወቱን ለኪነጥበብ የሰጠው ኩራባቸው ደነቀ በወዳጆቹ እንዴት ይታወሳል ?» https://www.bbc.com/amharic/articles/c62830d5kymo «ከ 1980 ዎቹ መጀመርያ ጀምሮ በተለያዩ ቴአትር ቤቶች በትወና እና በአዘጋጅነት ሰርቷል። በአዲስ አበባ በሚገኙት አራቱ ቴአትር ቤቶች በትወና፣ በዝግጅት፣ አንዲሁም በአመራርነት እውቀቱን አካፍሏል። የሙያ ባልደረቦቹ ኩራባቸው ከማለት ይልቅ “ ኩራ ” እያሉ መጥራትን ይመርጣሉ። ሁሉም በአንድ ቃል ለሙያው ካለው ፍቅር ባሻገር “ ጨዋታ ወዳድ፣ ወግ አዋቂ ” መሆኑንም ይመሰክራሉ። “ መካሪ፣ መንገድ መሪ ” ሲሉ የሚገልጹትም አሉ። ለሦስት አስርታት በላይ በኢትዮጵያ የኪነጥበብ አድማስ ደምቆ የኖረው ኩራባቸው ደነቀ የተወለደው በ 1957 ዓ . ም . በሐረር ነበር። ኩራባቸው የመጀመርያ ደረጃ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በጭሮ ከተማ ነው የተከታተለው። በ 1979 ዓ . ም . ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በቴአትር ጥበባት የትምህርት ክፍል የተመረቀው ኩራባቸው፤ በ 1980 ዓ . ም . ጋሞ ጎፋ ክፍለ ሀገር አርባ ምንጭ በጀማሪ የቴአትር ኤክስፐርትነት ተመድቦ ሥራ ጀመረ። በአርባ ምንጭ ቆይታው ለኪነጥበብ ዝንባሌ ያላቸውን ወጣቶች በተለያየ መልኩ ይደግፍ እና ያበረታታ እንደነበር የሚነገርለት ኩራባቸውን በተመለከተ ደራሲ ፍቅረማርቆስ ደስታ የራሱን ገጠመኝ በማንሳት ". . . እንደ መኪና ሮዴታ ከነበርኩበት ግራ መጋባት መንጭቆ