#የህወሃት #ጃርታዊ የፖለቲካ ፍልስፍና ለኢትዮጵያ #መቃብር እንጂ #ትፍስህት አይደለም።
#የህወሃት #ጃርታዊ የፖለቲካ ፍልስፍና ለኢትዮጵያ #መቃብር እንጂ #ትፍስህት አይደለም። "የቤትህ ቅናት በላኝ።" እሚታዬ ጽግሽ ተናግሮ ካናጋሪ ያድነኝ የዕለት ጸሎቷ ነበር። እኔ በህወሃት ዙሪያ ቅንጣት አቅም ማዋጣት አልሻም። ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ቀበጥ ያሉ ዘመናይ ሃሳቦች ሲነሱ የተገባ መልስ መስጠት ያስፈልጋል። ህወሃት በኢትዮጵያዊነት ላይ ቂም #የቋጠረ ድርጅት ነው። ቂምን እዬዘረዘረ ነው ኢትዮጵያን ሲበቀላት ነው የኖረው። እናት አገር ኢትዮጵያ #መተንፈሻ እንድታጣ ያደረገው እልል እያለ በፌስታ ነበር። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ተፈላጊነት #እንዲከሳ ያደረገው አቅዶ ነው። ህወሃት ትግሉን መሠረትም ሲጥል ቂም እና በቀልን #ከጥላቻ ጋር አጋብቶ ነው የጀመረው። ለዚህም ነው በሥልጣን ዘመኑ እንኳን "የትግራይ ነፃ አውጪ ድርጅት" የሚለውን ሥያሜውን ያለወጠው። ህወሃት ጥንስሱም፤ ውልደቱም፤ እድገቱም፤ አስተምኽሮቱም፤ ፍልስፍናውም #በጸረ ኢትዮጵያዊነት የተጠቀለለ ነው። በእያንዳንዱ የሥልጣን ዘመን ሂደቱ ነገ ኢትዮጵያ #ሊያሰቃይ ይችላል የሚለውን ክፋ ሃሳብ ሲያፈላ፤ ሲተክል፤ ሲኮተኩት፤ ሲያሳድግ እና ጨካኝ ሃሳብን ሲያሰብል ነው የኖረው። የውጭ ኃይሎች የነደፋትን ካርታ ተግባር ላይ ያዋለው ህውሃት ነው። ኢትዮጵያን ባህር በር እና ወደብ ያሳጣ ህወሃት ነው። የኤርትራ ህዝብ እና የኢትዮጵያ ህዝብ ህብራዊነት #የጎረደው ህወሃት ነው። ህወሃት ጫካ በነበረበት ጊዜ ዒላማው ትምህርት ቤት፤ የህዝብ መገልገያ ክሊኒክ እና መንገድ ማውደም ነበር። ይህን እኔ በስማበለው ሳይሆን በዓይኔ በብሌኑ ያዬሁት ሃቅ ነውና #ቀለጤ ፕሮፖጋንዲስቶች አያስፈልጉኝም። ...