ልጥፎች

#የማይነጥፈው #ልሙጡ ህልመ - ግብጽ።

ምስል
  #የማይነጥፈው #ልሙጡ ህልመ - ግብጽ።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       #ምዕራፍ ፲፮   ክብረቶቼ እንዴት አደራችሁልኝ? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ በጣም ደህና ነኝ። አቤቶ ግብጽ የራሱ የሆነ ጸጋ እና በረከት አለው። የአባይ ጉዞ ወደ ግብጽ ሲያቀና እራሱን የቻለ እዮራዊ ሚስጢር አለው። የግብጽ ሊሂቃን በዚህ እዮራዊ ሚስጢር ውስጥ ሆነው በቅንነት እና በዲስፕሊን የእግዘአብሄርን፤ የአላህን ስጦታ በማክበር ከክፋ ሃሳብ ጋር ሊፋቱ፤ ከቅናት ጋራ ሃራም ሊባባሉ በተገባ ነበር።   እንደ እኔ የግብጽ ሊቃውንት ጸጋቸውን የማንበብ፤ የመተርጎም እና የማመሳጠር አቅም ቢኖራቸው ኖሮ ዘመናቸውን ሙሉ በስውር ሴራ ኢትዮጵያን ለማጥቃት ከሚንቀሳቀሱ የየዘመኑ የክፋ ሃሳብ ባለሟሎች ጋር ባልተባበሩ ነበር። ለግብጾች ኢትዮጵያ #እስትንፋሳቸው ፤ የመኖራቸው ልሁቅ ሚስጢር ናት። ይህን ትንግርት በወጉ ዕውቅና ሰጥተው ልጆቻቸው፤ ትውልዶቻቸው ኢትዮጵያን የነፍስ አድን ህይወት መሆኗን በማስተማር፤ ስለ ኢትዮጵያ ሊጸልዩ፤ እሷን ሄዶ ለማየት ሊጓጉ በተገባ ነበር።    ግብጽ እንደ አገር የመቀጠሉ ሚስጢር የአጤ አባይ የግዮን ሚስጢር ነው። የግብጽን መኖርን - ያኖረ፤ ማወቅን - ያተባ፤ ለግብፃውያን ትውልድ #ብራ የፈጠረ፤ የአገር ተስፋን ያለመለመ አጤ አባይ ነው። አጤ አባይ ልጆቹ በጨለማ እየማቀቁ፤ በምግብ እጥረት እየተሰለሰሉ ውሃ ብቻ ሳይሆን፤ የኢትዮጵያን እዮራዊ ቅን መንፈስ ይዞ እየነጎደ ግብጽን ድሯል፤ ኩሏል፦ ለወግ ለማዕረግም አብቅቷል። አባይ ሲጓጓዝ የኢትዮጵያ ንጹህ #ቅዱስ መንፈስንም ይዞ ነው። ይህ ረቂቅ ጉዳይ ነው።   አጤ አባይ፤ ውሃ ብቻ እንጂ የኢትዮጵያን እዮራዊ ሁለመና ...

ጦርነት እና "ትርፋ።" ፈላስፊት ኢትዮጵያ #የጸና #ሰላም ትሻለች።

ምስል
 የኢትዮጵያ ፖለቲካ #ከብስጭት ፤ #ከቁጣዊ መስመር መውጣት ይኖርበታል። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። እኔ በልጅነቴ ነበር ጠላፊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጠልፎኝ #ሰምጬ የቀረሁት። የፖለቲካ ህይወቴ ምን ያህል እንደ ጠቀመኝ የማውቀው ነገር በውነቱ የለኝም። ሳውቀው የኢትዮጵያ ፖለቲካ #ብስጩ ፤ #ገረጭራጫ ፤ እና #ቁጡ ነው።  ትናንትም፤ ዛሬም ይኽው ነው። አሁን ባለው ሙሉ ዕድሜየ ላይ ሆኜ ሳስበው ምክንያቱንም፤ ሳንሰላስለው የኢትዮጵያ ፖለቲካ የስንቁ መሠረት የየዘመኑ ወጣቶች መሆናችን ይመስለኛል። ወጣትነት የአቅም ክምችት፤ የተግባር ፍጥነት እና ትጋት ያለበት ቢሆንም በዕድሜው በራሱ #የመቸኮል ፤ ያሰቡት ሲዘገይ #የመበሳጨት ባህሪ የፖለቲካ ድባቡን ይውጠዋል።  እናም የኢትዮጵያ ፖለቲካ በዚህ መሰል በማይታይ ሁነት ግን ብዙ ባለብሩህ ዕሳቤ ያላቸውን ወጣቶችን የሚያጣበት ክስተት ይህ ይመስለኛል። በአመዛኙ በየዘመኑ ለጥቃት የሚጋለጡት ወጣቶች ናቸው።   አንዲት አገር ወጣቶቿን ባጣች ቁጥር ነገን ለማሰብ ይከብዳታል። ይህን ችግር ለመፍታት ተገቢው ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ባይ ነኝ።  እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።  ሥርጉትሻ 2025/09/01    ጦርነት እና "ትርፋ።"  "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" ጦርነት ለሚናፍቃችሁ፤ ጦርነትን ለምትመሩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ኢሊቶች ሆይ! በተሳተፋችሁባቸው የጦርነት አውዶች ሁሉ ህዝበ ጠቀም የሆነ ያተረፋችሁት ነገር አለን????? "ትርፍ" የሚለው ቃል እራሱ ለሰው አጫጁ ጦርነት የማይመጣጠን ነው። ቃሉ በንግድ አግባብ፤ በገብያ ህግ አፈፃጸም ነው ትክክለኛ ቦታው። በሰው አፈጣጠር፤ አስተዳደግ እና አመራር "ትርፍ"  ...

የሰው ልጅ የጀንበር የእጅ ሥራ #ዳንቴል አይደለም። ኢትዮጵያ #የወላጆች #የጥሞና ንቅናቄ ያስፈልጋታል።

  የሰው ልጅ የጀንበር የእጅ ሥራ #ዳንቴል አይደለም። ኢትዮጵያ #የወላጆች #የጥሞና ንቅናቄ ያስፈልጋታል።   "አቤቱ ንጹህ ልቦናን ፍጠርልኝ።" አሜን።     ምዕራፍ ፲፮   ዛሬም የኢትዮጵያ ፖለቲካ #ማገዶ ይሻል፤ ይመኛል፤ ይፈልጋል። ያ ……… ማገዶ የወይራ አይደለም። ያ ……… ማገዶ የአባሎ አይደለም። ያ ……… ማገዶ የዝግባ አይደለም። ያ ………ማገዶ የባህርዛፍ አይደለም። ያ …… ማገዶ የኩበት - የፍግ - የሸለሸል አይደለም። ያ … ማገዶ ዘጠኝ ወር በእናት #ሆድ ፤ ሦስት ዓመት በእናት ትክሻ በታላቅ እህት ጀርባ፤ በእሚታ፦ በአክስት እቅፍ፤ ሰባት ዓመታት በቤተሰብ፤ በቤተዘመድ፤ በእኛ ባህል እና በወጋችን #በጎረቤት ልዩ ጥበቃ እና እንክብካቤ ያደጋል። ከዚህም በኋላ መምህራን እና በቅርብም በሩቅም ያሉ ወገኖቻችን ይሳተፋበታል። ሙሉ አቅም ይፈሳል። ረቂቅ ነው። የሃይማኖት አቨውም ይደክማሉ።   ከዛ የመኖር፤ የመማር ሁነቶች በቤተሰብ #አንጡራ ላብ እና ወዝ ይከወናል። የቻለው ኮሌጅ፤ ዩንቨርስቲ ዕድሉ ከተገኜ ተስፋን ለማግኜት በተስፋ ይተጋል፤ በመሃል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጠላፊ ነው ይጠልፋል። ተስፋ ይጨነግፋል። ተድሮ፤ ተኩሎ ልጅ ወልዶ፤ ተምሮ ተመርቆ ከፍ ያለ ደረጃ የደረሰው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ኢሊት ለፖለቲካው ማገዶውን ያልዘራውን፤ ያላበቀለውን፤ ቅንጣት አቅም ያላዋጣበትን ይጠልፍ እና #አንጋቹ ያደርገዋል። እኔ ይህን ጊዜ አስትሮኖመር ነበር እምሆነው።    የሚገርመው ብዙው ትዳሩን አሸሽቶ፤ እራሱም ሸሽቶ ተደላድሎ ተቀምጦ፤ ልጁን ትምህርት እያስተማረ ነው "በሞኝ ክንድ ዘንዶ ይለካበታል" እንደሚባለው የኢትዮጵያ እናቶችን የተስፋ ፍሬ ነጥቆ በተንቀለቀለው ቋያ የሚያርመጠምጣቸው። አንድ ጊ...