በሴቶች እና በአብይ ዙሪያ ሥርጉተ በታህሳስ 26/2017 ምን ብላ ነበር?

        አብይ ኬኛ! ክፍል ሦስት - ለቅኖች ብቻ። 
          አብይ ለእኛም ለሴቶች አናባቢያችን 
                       Vowels ነው።
„ከሳምንቱ በመጀመሪያው ቀን ማልዶ በተነሳ ጊዜ፤ አስቀድሞ ሰባት አጋንንት ላወጣላት ለመግድላዊት ማርያም ታዬ። 
እርስዋ ሄዳ  ከእርሱ ጋር ሆነው ለነበሩት፤ ሲያዝኑና ሲያለቅሱ ሳሉ አወራችላቸው። እነርሱም ህያው እንደሆነ 
ለእርስዋም አንደታዬ ሲሰሙ አላመኑም። ከዚህ በኋዋላ ከእነርሱ ለሁለት ወደ ባላገር ሴሄዱ፤ በመንገድ በሌላ
 መላዐክ ተገለጠ። እንርሱም ሄደው ለሌሎች ሄደው አወሩ፤ እነዚያን ደግሞ አለመኗቸውም። ኋላም በማዕድ
 ሳሉ ለአስራአንዱ /ሐዋርያት/ ተገለጠ። ተነሥቶም ያዩትን ስላላመኗቸው፤ አለማመናቸውን የልባቸውን 
ጥንካሬ ነቀፈ። እንዲህም አላቸው፤ ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ። 
ያመነንም፤ የተጠመቀም፤ ይድናል። ያለመነ ግን ይፈረድበታል“  
(የማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ  ፲፮ ከቁጥር ፱ አስከ ፲፯። ዮሖንስ ወንጌል ምዕራፍ ፳ ከቁጥር ፩ ጀምሮ … ) 

የበለጠ ሚስጢሩን ለማዬት የዬሖንስ ወንጌል ምዕራፍ ፫ ከቁጥር ፩ ጀምሮ ያለውንም በጥልቀት መመልከት ይቻላል። በመንፈሳዊ ህያዊነት ቃለ ህይወቱ መረቡን በረቂቅነት በውስጣችን ይዘራል። ይሄም ነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሚስጢር። የክርስትናም። ዶር አብይ አህመድ አኮ የቅኔ ማዕዛ ናቸው። እሳቸው ስላነሱት ነው እኔም የጹሁፌ ባርኮት ያደረኩት።

ከሥርጉተ ሥላሴ
ታህሳስ 26/ 2017
ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ



  • ·         ር።  

ቃል እና ተግባር!
በሙሉ ተስፋ እጠብቃለሁኝ የድርጊት እመቤትነትን!
በመሆን!
እውነት እና ኪዳን በመሆን!

ውዴቼ ትንሽ ለመግብያ ይህን ልበል። ይህን ጹሑፍ በታህሳስ ወር በ2017 በባይናክተን /በክርስማስ ማግስት የጻፍኩት ነው። ይህም ብቻ ሳይሆን ይህን ያጠናከርኩበትም ሌላ ጹሑፍም ነበር። ሙግት ላይ ነበርን እኔ እና የኢሳቱ "የማማ "አዘጋጅ ጋዜጠኛ ማስረሻ አለሙ ጋር። ለእሱ መልስ የጻፍኩት በ6ክፍል ነበር። ግንቦት ላይ ብሎጉን ስጀመር ከሳተናው ያለውን በሙሉ እዚህ አርኬብ አድርጌዋለሁኝ። 

ይህም ብቻ ሳይሆን ሴቶች እና ዶር አብይ አህመድን በሚመለከት ከዚህም ለላፈ አካል ምስክርነቴን ሰጥቼ ነበር። ያን ጊዜ ደግሞ ለ እጩ ጠ/ሚር ሲወዳደሩ ወጀቡ ስለበዛ ሚዛን ላመስጠበቅ፤ ዛሬ እኒያ ታላቅ የሉላዊው ዓለም የመቻቻል እናት ይህን ብስራት ሲሰሙ በምልሰት እኔን ያስታውሳሉ ብዬ አስባለሁኝ። የድምጽ አልባዎቹ የኢትዮጵያ ሴቶች ሃዘን ተጋሪዋ ክብርት ውድ ለእኔ ጌጤ ናቸው የጀርመን ጠ/ሚር ወ/ሮ አንጂላ ሜርክል። 

ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ ለእኛ ትውልድ የመጀመሪያዋ ፕሬዚዳንት ሴት? ይገርማል። "ገና ምኑ ተነክቶ" ክብርት ፕሬዚዳንቷ ብለዋቸዋል የሴቶችን አቅም አብዘተው ለሚፈሩ የ50 ዓመት ፖለቲከኞች። አዎን! "ገና ምኑ ተነክቶ።" ጠቅላይ ሚኒስተር መሆን ቀጣዩ የተጋድሎ ፋናችን ነው። ይህን መጻፍ እንኳን አይፈቀደልንም ነበር። እዚህ በነጻ አገር እነሱም እኛም ተቀምጠን ጹሑፉን ያስነሱት ነበር። አሁን ተመሰገን ነው። ቀና እያልን ነው። 

ኢትዮጵያ አገራችን እናትነቷን እና ሴትነትን ተቃኝተውታል አዲሷ ፕሬዚዳንት። እኔ በዚህ ደግሜ በለጥፍኩት ጹሁፌ ላይ ሴት አገር ስለመሆኗ ጽፌያለሁ። እሳቸውም አበክረው ገልጸውታል። ልዩነቱ እሳቸው የአገር መሪ እኔ ደግሞ አልባሌ ተርታ ዜጋ መሆኔ ብቻ ነው። እናም እኔ ብረት መዝጊያ የሆነ ወንድም የለኝም። ወይንም ብረት መዝጊያ የሆነ የፖለቲካ ድርጅት አባልተኛ አይደለሁም። 

በተጨማሪ ዶር አብይ አህመድ ያን ጊዜ የ ኦሮምያ የጽ/ቤት ሃላፊ ሳሉ እዚህ ላይም ለሴቶች ብቃት ያላቸውን አትኩሮት ስለ ክብርት ወ/ሮ ጽዮን ተክሉ ጽፌ ነበር።
 https://sergute.blogspot.com/2018/05/05.html

ዛሬ የተለዬ ቀን ነው። ጭምቷ ሲዊዝ ደግሞ በረዶውን አልሻም ብላ ፏ ብላ ነበር። እሜቴዋ የጫጉላ ጊዜዋን የጨረሰች ይመሰል ደህና ናችሁን - እንዴት ይዟችኋዋል ስትል? እንደ ልዕልትነቷ አነገቷን ለአማል ሰገድ አድርጋ ብቅ ብላ ነበር። 

ዛሬ በጋ መስሎም ነበር ሰዐተ ረፋዱ ላይ። ብዙም በዚህ ቀን አመጣጧ ካለ መሰናዶ በመሆኑ ፍቅር ባይቸራትም። ግን ዘው ብላለች። ዛሬ የመሬት የነጭ አበባ ስጋጃ ነበር የሚጠበቀው። 
----------------------------------------------------------------------------
ታህሳስ 26/ 2017 እንዲህ ብዬ ነበር። 


  • መቅድም።


በተጨማሪም ሲዊዚዬ „እንኳንም ዘንቦብሽ“ እንዲሉ እንኳንስ እንዲህ ዓይነት ብሄራዊ ሃይማኖታዊ፤ ዓለምዓቀፋዊ የጽሞና በዕላት ቀርቶ ወትሮንም ሲዊዝዬ አሜሪካን አገር የምትኖረው ደግ እህቴ እዚህ መጥታ በነበረችበት ጊዜ እንዳለችው „የሀገር ገዳም“ ናት። ጸጥ ረጭ ብሏል ሁሉ ነገር። ነፍስ በምድር ላይ ብትንቀሳቀስ ወዮ የተባለ ይመስል ጫ ብሏል። የጣሪያዬ እርግቦች እንኳን ዛሬ ድምጻቸውን አላሰሙም፤ ስለምን ይሆን? ዛሬ እኔ እነሱን ብሆንስ? ጉጉጉጉ በኢሳቱ ጋዜጠኛ በማስረሻ አለሙ ላይ ብልስ? ብተካቸው እነ ርግብን። 
  • ·         ሪደር።

የኢሳቱ ጋዜጠኛ አቶ ማስረሻ አለሙ „ከመለሳውያን ወደ ለማውያን“ ሲል ያባጨለበትን ዝግጅት ሙግቱ እነሆ አሁንም ቀጠለ። እሳቸውን እንደዛ ተንጠራርቶ አቅሙ ጥብቆ ነው። ለመተችት። በፖለቲካ ሊሂቅነታቸው አይደለም፤ በዕውቀት ባለቤትነታቸውም ላይሆን ይችላል፤ ነገር ግን አቅም ያነሰዋል የምለው እያንዳንዱ ልጅ ሲወለድ መልእክት ይዞ ይወለዳል። አዎንታዊም አሉታዊም። 

የዶር. አብይ አህመድ ይዘው የተወለዱት መልዕክትን በወጉ እንደ አባት አደሩ የጥሞና ጊዜ ወስዶ አለፍተሸውም። ይልቁንም በማንፌስቶ ስካር ተዛለለበት። ክህነተ ቤተክርስትያናዊ ቅብዕ ነው። መሪነትም እንዲሁ። ጉዳዮችን በጥልቀት፤ በማስተዋል አትኩሮታዊ ልብን መለገስንም። መሪነት እኛ መሪ ስለደረግነው ሳይሆን እሱ እራሱ ለመሪነት የሚያበቃውን ቅብዕ ቅዱስ በውስጡ ሲያሰርጽለት ነው ከሰውኛው የመሪነት ምኞት፤ ወይንም አምልኮተ ሰውነት ወደ መንፈሳዊ የመሪነት ጸጋ ወይንም ረድኤት የምንሸጋገረው። 

እኔ እሳቸውን እማዬው ከተለመደው የቀለም፤ የተመክሮ፤ የዕውቀት ብሂል ጋር በተዛመደ አይደለም። ለለእኔ ፈጣሪዬ የሚነግርኝ ሌላ መልእክት አለው ብዬ አምናለሁ። ቋንቋውን ይሄ ዓይነት ቋንቋ ነው ብዬ መናገር አልችልም። 

ብቻ በማስተዋል ውስጥ እንድመሰጥባቸው አድርጎኛል። ልክ እንደ ብላቴ ጌታ ሎሬት ጸጋዬ ገ/ መድህን አሁን ደግሞ የቃለ ምልስ ሂደቱን ውስጡን ስጎበኝ ጥሞናዬን በአዱኛ በሚያበራክትልኝ ጠቢቡ ቴወድሮስ ካሳሁን። ለዚህም ፈጣሪዬን አመሰግነዋለሁ። የጎበጠውን ቀን ለማቃናት ሁልአቅፍ የአውንታዊነት የግንባታ ማህንዲስነታቸው ፍንተው ብሎ ይታዬኛል - ለእኔ። ምህንድስናቸው ተፈጥሯዊ መሆኑን ያቀናልኛል። ቅብዕው ደግሞ የመዳህኒት ዓለም እንደሆነ መንፈሱን ያጎርሰኛል።
  • ·         ልፍኝ።

 „አብይ የእኔ!“ የእኔ ስል በምወደው እጅግም ጥልቅ አክብሮት ባለኝ የሴትነት ፆታዬ  ከእኒህ የመጀመሪያው የሴትን አቅም አደባባይ ወጥተው በመናገር፤ ያልተደፈረውን የአውነት አመክንዮ በሚገረም የብቃት ትራስ በመግለጽ፤ በሚገርም የባለቤትነት ጉዝጓዝ ውበት ሰጥተው በማቅረብ፤ ጸጋን አጎናጽፈው ውስጡን በማምራት የመልካም ዜና መልእክተኛ በመሆን፤ ሴትነቴን ክብሩን አገርመው የእኔ በማለት፤ ትህትናን በገፍ አጉርሰው አለሁህ በማለት፤ ልቅናን በህብር አቅልመው ውስጣቸውን የገለጹበት ህብርነታቸውን አይቻለሁ። ስለሆነም አምሰክራለሁ። 

ቧልተኛው ጋዜጠኛ ማስረሻ አለሙ የኢሳቱ „የማማ“ አዘጋጅ ያብጠለጠለው የእውነት ማህለቅ ተቀናቃኝ አሉታዊ መንገድ እንዲህ ድቅቅ ይላል። እንዲህም ይልማል። እንዲህም ብን ትን ይላል … አዎን አብይ የጎንደር ጌጥ! ብቻ ሳይሆን የሴታዊትም ጌጥ ነው! እስቲ ምን ትሆን ጋዜጠኛ ማስረሻ አለሙ። 

„ወንድ እና ሴት በሚያስደንቅ ሁኔታ የተፈጥሮ ልዩነት አላቸው። ወንዶች በደንብ እንድትሰሙኝ እፈልጋለሁ። ሴቶች በሚያስደንቅ ሁኔታ ከወንዶች የተሻለ ብቃት አላቸው።“

ዶር. አብይ አህመድ ይህን የሴቶችን የብቃት ወቄት ሲገልጹ በራስ የመተማመን ሙሉዑነት ንጹህ መንፈስን ታጥቀው በእርግጠኝነት ነው። ውስጣቸው ፈቅዶ ስንኛትን በመንፈሳችን ሲተክል አንዳች ግርማ ሞገስ አለው። ሲገልጹት አንዳች ስሜትን ውርር የሚያደርግ ሐሤት በመላ አካላት ይሰፍናል። እንደዚህም ሆነ --- መጪው የአውሮፓውያኑ አዲስ ዓመት ስለሆነ 2019 የሴቶች አቅም ቢያንስ የሃሳብ ጽንስ ሊሆን ይችላል ብለን፤ አቧራ ላይ ወድቆ ሲንፈራፈር የነበረውን የተስፋን መንፈስ ቀና አድርገን አይዞህን እናጠጣው ዘንድ ፈቀደ - አዶናይ። ምን ሲሳነው። ለካስ የመንፈስ እስረኝነት ፍች ቀን ሲወጣ ሳያማክር ነው። ይገርማል።
  • ·         ተፈጥሯዊ ዋና ብዕረኛዋን እንዲህ ያመጧታል …. 

ዶር. አብይ አህምድ ሴት ልጅ በተፈጥሯዋም ጸሐፊ ናት ይላሉ እንዴት? „በየቀኑ አንዲት ጸሐፊ አለቃዋ ሲገናኝ የዋለውን ስልክ፤ የሰጠውን መፍትሄ፣ የቀረበውን አቤቱታ፤ በሦስት ደቂቃ ወስጥ መልስ የተሰጠ፤ ቀርቦለት መለስ አልተሰጠም፤ አንዳንድ ገጽ መርጣ ጠቃሚውን ብቻ አቤቱታ የቀረበለትን፤ በሦስት ደቂቃ ውስጥ ለማድረግ የፈቀዱ መሆኑን፤ አቶ እከሌ ሊያናግሩት መጥተው የለም ብሎ አስመለሰ፤ ስብሰባ ነኝ ብሎ መመለሱን፤ ብትጽፍ በዓመት ውስጥ 365 ገጽ ጸሐፊያዋ፤ ያቺ የምትልካት የማታውቀዋ፤  የዕዬለት ታሪክ ጻፈች። ከእሱ ውስጥ አይረባም ፤ እንዲያው ግማሹ garbage ነው ብትሉት፤ ግማሹን ብቻ ብንወስድ መቶ ምናምን ገጽ መጸሐፍ ወጣ፤ ያቺ ጸሐፊ በየዓመቱ አንዳንድ መጸሐፍ የሚያወጣ ብቃት አላት። ግን አትጠቀምበትም። አይወጣም። ከምናዬው ከምንታዘበው ነገር ወደ ትውልድ የሚሸጋጋር ቢኖር በጣም በርካታ አውቀት እናንተ ውስጥ አለ።“ 

ከዚህ ጥልቅ አትኩሮት ውስጥ የጸሐፍትን ነገን ማሰብ ይቻላል። ነገር ግን ፈቃዱ አለ ወይ? በዬት የሴራው ሰንሰለት ታልፎ? አገር ቤትም ሆነ ውጪ ሀገር ይለፉ ይገኛል ወይ? የእኔ እኮ የልጆች እና የአዋቂዎች 7 መጸሐፍት ታትሞ እቃ ቤት ውስጥ ነው ያለው። ጥቂት እርማቶች የቀሩትም 8ኛ መጸሐፌ እንሆ ኮንፒተሬን ያሞቃል። 

የተጀመረው 9ኛ እና 10ኛው መጸሐፌም አንዱ ልበወለድ አንዱ የወግ ገበታ ደግሞ ተጀምሮ እንደ ጎንደሩ አዘዞ መናህሪ ቆሞ ቀር ሆኗል። ኮንፒተር ላይም ጽፌ መጨረስ ፍላጎት አጠረኝ። በእጅ የተጻፈ ነው። ምክንያቱም ቤቴ ጠባብ ነው፤ ዕቃ ቤቴ በታተሙት ሞላ፤ ስለዚህ ሚሞሪ ካርድ ላይ ማስቀመጡ ቀለለኝ። የሁለቱን የተጀመረውንም በ2012 እ.አ.አ ነበር፤ ቆመ። እስከ አሁን በተለይ በልጆች ጉዳይ ቁጥር ሊወጣለት የማይችሉ ስንት መጸሐፍትን ባሳተምኩኝ ነበር። በዬት አልፍን? እንዴት ብለን? ማን እንደ አሳገደው? ብነግረዎት ደግሞ ይገርመዎታል፤ ያማል። 

እርግጥ እርስዎ አትኩሮቶወት ጥልቅ ስለሆነ የሌላ የፍልስፍና ማህደር ይሆነዎትም ነበር፤ እኛ ምን ዓይነቶች ነን? ከምንስ እንመደብ ብለው? ስንት የመፍትሄ መንገድ ብሂል ባሰቡ ነበር። አንድ አገር ቤት በራሱ የግል ወጪ መንገድ ላይ የወደቁትን ድውያንን የሚረዳ ቅዱስ ወጣት አለ። መላእክ ብለው ይሻለኛል። ኢትዮጵያ ውስጥ ሁሉንም ለህትምት የበቁትን የመጸሐፌን ስክሪፕት ብሰጠው ደስ ይለኝ ነበር። ገንዘብን እኔ አልወደውም፤ ገንዘብም ወዶኝ አያውቅም። ይህን የሁለታችን ያለመፋቀር ግንኙነት እጅግ አድርጌ አውደዋለሁ እንደ ልዩ በረከት አድርጌ ነው የማዬው። 

እንደ ድህነት ደስ የሚል የነፃነት ቀን የለም። እንደ ድህነትም ቅልል ያለ ጣፋጭ ኑሮ የለም። አንደ ድህነትም ማራኪ ውሃማ ቀለም የለም። እና ያ እናት ሆዱ አሳትሞ፤ ሽጦ መጠቀም ይችል ነበር። የኮፒ ራይቱ እንደ ተጠበቀ ሆኖ፤ ግን የቅኖች ጋላሪ የለንም። የቅኖች ማህበር የለንም። የቅኖች መሪ የለንም። በምን መስመር እንገናኝ። ፌስ ቡኩን እኔ አልወደውም። መንገድ ላይ ካለ ከፈን የተኛሁ ይመስለኛል፤ ሳስበው እራሱ።

መጸሐፍቶቹ ለወላጆች፤ ለልጆች፤ ለባለትዳሮች የሚጠቅሙ የምክር አገልግሎት ነበሩ። እርግጥ ቀደም ባለው ጊዜ የጋሼ ጸጋዬን የማስታወሻ ከወገብ በላይ የሆነ ሃውልት ዩንቨርስቲ ውስጥ አስፈቅዶ የማሰራት ትልም ነበረኝ፤ አጀማመሬ ለዛ ነበር ግን ቀኑም ርጉም፤ ዕጣውም ጠማዳ … አስፓልቱም ወልቻማ … 
  • ·         የልቤ መሠረት!

Ethiopia Dr abiy የሰዉ ልጆች ልዩ ብቃት ክፍል ሁለት

https://www.youtube.com/watch?v=AHyuaT4mqz4

Ethiopia Dr abiy የሰዉ ልጆች ልዩ ብቃት ክፍል አንድ
  • ·         ይድረስ ለዕሴታዊት የንጋት ጮራዎች።

የእኔ ሊቃናዊት „እንኳን ደስ አላችሁ!“ ራዕያችሁን ፈጣሪ አምላክ ባረከላችሁ፤ ጥረታችሁን በአቅም አቅጣጫ ነደፈላችሁ መዳህኒታለም አባታችን/ አላህ። እንሆ ጋሼን፤ ክንዴን፤ ጥላዬን፤ መከታዬን ታላቅ ወንድም ነገን ጨምሮ ክርስቶስ ፈቅዶ ሰጣችሁ። አብሯችሁ ነው ያለው። ሊቁ ለሴቶች ያለውን ጥልቅ ዕውቀት በውል በህሊናው መሬት ቋጥሯል። ዶር. አብይ አህመድ የእሴታዊነት ሰማዕት ናቸው። ለትውልዱ ለሴቶች አቅም ሥራ ላይ መዋል፤ የሃሳብ ፕሮጀክት በነፍሳቸው ውስጥ የፈቀዱ የመጀመሪያው የፖለቲካ ሊሂቅ ናቸው። ለእኩልነት ተልዕኮ የጀርባ አጥንት Backbone ናቸው። ለውስጣችን አቅም ይህን ያህል ዕውቅና የሰማይ ታምር ነው። 


ልዕልቶቼ አብራችሁት ቁሙ ከእለታችሁ ጋራ፤ ማግስታችሁን፤ ዘመናችሁን ፈጣሪያችን/ አላህ መርቆታል እና። ጠብቁት የዶክተር አብይ አህመድን ቅናዊ መንፈስ፤ ህጋችሁ፣ ድንጋጌያችሁ ነውና። ቅረቡት ትልቅ ጆሮ አለው ያደምጣኋዋል። ፍቅራችሁን ሳትስቱ ለቅንነቱ ስጡት፤ ውስጡ አድርጓችኋዋል እና። ይህ የዘመነ ለማ እንከን ካልገጠመውም በእውንም ኢትዮጵያ የፍቅራዊነት መዲና መባቻዋ ይጀመራል። መንፈሱ ዋዜማችን ነው ለቅኖች ብቻ!

  • ·         ቅኖች ሆይ!

„ሴቶች ጥሩ ነገር አላቸው ጊዜ እሲኪሰጣቸው ድረስ ጠብቀው ይይዙት ዘንድ እለምናቸዋለሁ።“ ይህን ጹሑፍ ቅን የሆኑ ዘሃበሻ እና ሞረሽ ወገኔ ድህረ ገፆች ለጥፈውልኝ ነበር። ወራቱ ታህሳስ ነበር እንደ ዛሬው፤ ቀናቱም 20ዎቹ ውስጥ ነበር በ2013 ነበር። ዛሬ ደግሞ ዓመት ድገሙ ልል በዚህ ዙሪያ እነሆ ከች አልኩኝ። የእኔ ልዕልቶች ያ በ2013 የለመንኳችሁ ጊዜ ዛሬ ወደ እኛ እዬመጣ ነው። አንዳችም አትጠራጠሩ። ቀኑ ለሴቶች አቅም፤ ልቅና፤ ህልውና ተደማጭነት የሚሆን ነው። እርግጥ ነው ለማንፌስቶ አባልተኞች ይህ ላይመች ይችላል። 

እንኳንስ ይህ ባተሌዋ የነፃነት አርበኛ የፖለቲካ ድርጅት አባልተኛ ቀርቶ፤ ለአንዲት አንስት የማንፌስቶ ጋዜጠኛ፤ የማንፌስቶ አባል አቅሙን መሸመት ይሳናታል። ስለሆነም ሴት የማንፌስቶ አባሎችን ይህ የዶር አብይ አህመድ ሥህነ- ነባቢት ከቁብ የማይቆጠር ሊሆን እንደሚችል አውቃለሁ። የቀደመ ጣዖት አለ። ማንፌስቶ። የወንዶች የፖለቲካ ማህበርም እንዲሁ፤ ይህን መንፈስ እንደ አንጡራ ጠላቱ ነው የሚመለከተው። የማዳኛችን ቀን መንገዱ መጠረጉን አያስተውሉትም እና።

ለእኛ ባለቤት፤ ተንከባካቢ፤ ጠያቂም፤ ጠጋኝም ለሌለን ሴት ምንዱባን ግን አዲስ የብርሃን መለከት ነው። ይህን የምለውም ያለምክንያት አይደለም። ኢትዮጵያ የወንዶች የፖለቲካ ማህበርተኛ ሀገር መሆኗ ደፍሬ የምናገረው ስለሆነ ነው። ወንዶች ፈሪዎች ናቸው። እጅግ ወንዶች የሚፈሩት ደግሞ ተፎካካሪ ፓርቲዎችን ሳይሆን እኛን ነው። የሴቶችን የውስጥ፤ የህሊና ብቃት። የመንፈስ ጽናት፤ የልቦና ብልህነት። ፈሪነታቸው ደግሞ ብዕር ብቻ ሳይሆን የሴቶችን የለማ ተመክሮንም ጭምር ነው። ይህን ስለማይሹ የማታስፈራቸውን ለቁጥር ተዋፆ ብቻ ደከም ያለችውን ፈልገው ይጠጋሉ ወይንም ያጠምዳሉ። 

ስለምን? ተፎካካሪ ሆና የምትወጣው ማግስትን እንዴት እንደምታደራጀው ስለሚያውቁ። ትበልጣቸዋለቻ። እነ ሴቶች አደራጅነትን በተፈጥሯቸው ያገኙታል ብዬ አምናለሁ። እርግጥ ክህሎቱ በሥልጣና ከተኮለመ ደግሞ ብልጹግ ይሆናል። ለዚህም ነው ጀርመኖች አምስት ትጉሃን ወንዶች ወይንም አንድ ሴት „fünf fleißige Männer oder eine Frau የሚሉት አቅማችን አጥብቀው ወንዶች ስለሚፈሩት፤ በአጋጣሚ እንደ ክብርት ዳኛ ብርቱካን ሜዴቅሳ ተፈጥሮ ሳይሰስት የሰጣት የነጠረ ብቃት ያላት አንስት፤ እንዲህ ትሆናለች ብለው ሳያስቡት ብቅ ስትል ድንጋጤ ተናኘ። 

በቃ በአጭር ጊዜ ውስጥ የመሪነት አቅም አግኝታ ወጣች። የበቀለው አጸደ ተክልም በሴራ ፖለቲካ ሃራም አለ። ይህን የፈተሸ፤ ያጠና፤ ያነበበ፤ የተረጎመ ያመሳጠረ ንግግር ነው የዶክተር አብይ አህመድ ጉልበታም ፍልስፍና። ባለፈው በክፍል ሁለት Thinker ናቸው ብዬ ነበር ዛሬ Positive Thinker ብዬ ጉልበት ልስጠው። ልክ እንደ ቅኔው ዕንቡጥ እንደ ቴወድሮስ ካሳሁን፤ እንደ ብሩኩ ቀን ፕ/ ፍቅሬ ቶሎሳ፤ እንደ የሞራል ፖለቲከኛ እንደ አቦ በቀለ ገርባ። 

ይህ ጉዳይ አክብረን መነሳት የምንችለው፤ ብረት መዝጊያ የሆነ ዘመድ፤ ትዳር፤ ወንድም፤ ባለቤት የሌለን፤ የማንፌስቶ ማህበርተኛ ያልሆነው ለመሆንም የማንፈቅድ ተማላ ሴቶች ብቻ ነን። አንዳንድ ጊዜ እኔ ግን ስለምን ነው እንደዚህ ውስጥ ገብቼ የምቸገረው  ለአንድ ነገር እል ነበር። አሁን ዶር. አብይ አህመድ መልስ ሰጥተውኛል። 

ለምሳሌ እኔ የአርበኛ አንዳርጋቸው ጽጌ የቅድመ ደወል የሞት ስለላ፤ ከዛም የቀጠለው ተላልፎ መሰጠት፤ በተመሳሳይ ሁኔታ የኢትዮጵያዊው ማንዴላ የዶር. መራራ ጉዲና እስር፤ እና ተከታዩ  የቆሼን ጉዳይ ሰው ካዬበት ሁኔታ በተለዬ ነው የማዬው። ዝም ብዬ እንደ ማንኛውም ዜና አልተመለከትኩትም። እርግጥ አጋድሜም ቢሆን ጽፌበታለሁ። ምክንያቱም ሂደቱን አንዲሁ ላዩን አይቼ እራሴን ልሸፍጠው አልፈቀድኩም።

መኖርን ባልጠላውም ሞትንም አልፈራውም። በመኖሬ ውስጥ አጀንዳዬ ሆኖ የኖሩት አመክንዮዎች ባለቤት አግኝተው ማዬቴ እናፍቀው የነበረውን ሞቴን ትንሽ ዘግይ እባክህን እንድል አድርጎኛል። ምንአልባትም አንድ ቀን ይህ የፍርሃት ዓለም መልክ የሚያስይዘው፤ ሰብዕና በተሟላ ተፈጥሯዊነት የሚቀርጸው „ፍቅራዊነት LoveIsm“ እንደ አንድ የትምህርት ዘርፍ ብቻ ሳይሆን የትኛውም ተቋም የመግብያ መስፈረት የመሆን ዕድል ሊያገኝ ይችል ይሆን ብዬም አስባለሁ፤ ቅን ነገሮች ደወላቸውን ሳዳምጥ፤  

በእነኝህ ሥም የሚጠሩ ለምሳሌ „የመከባባር ዩንቨርስቲ፤ የመቻቻል ት/ቤት፤ የተስፋ ኮሌጅ፤ በራስ የመተማመን ተቋም፤ የታጋሽነት ተቋም፤ የታማኝነት ኮሌጅ“ ወዘተ የሚሉ ትርጉም ያላቸው የተግባር ሂደቶችን ዓለም ጀምራ፤ የፍቅራዊነት LoveIsm መምህራን፤ ፈላስፋዎች፤ ኤክስፕርቶች፤ ተንታኞች፤ ሲፖዚዬሞች፤ ኤግዚቢሽኖች ዓለም ዐቀፍ ቀኖች፤ ቲያትሮች፤ ፊልሞች፤ ማህበሮች፤ አስተዳዳሪዎች፤ ሚ/ሮች፤ ወርክሾፖች ይኖሩ ይሆናል። 

ፍቅራዊነት በተለምዶ ሳይሆን የሚማሩት፤ የሚመረቁበት ሰብዕና ተቀርፆ የሚወጣበት፤ ጊዜም እንዲህ ዋዜማውን ባይ እምኛለሁ … ፍቅራዊነት የመሠረት መሠረት እንዲሆን አልማለሁ። አሁን እግዚአብሄር ይመስገን ከሰነበቱ፤ የወያኔ ሃርነት ተግባር ከሰይጣናዊ ተግባሩ እጁን ሽባ ካደረገ ተስፋዬ ብዙ ነው በእኒህ ተባረኩ የቅንነት ማህደር። የውስጥ የብቃት መኪያው ግልጽነት መድፈር እራሱ ግልጽነት ነው።

በዶር. አብይ አህመድ መንፈስ ውስጥ „ሰው“ ብቻ ሳይሆን „ተፈጥሮ“ አጀንዳ ሆኖ አለ። ለዚህም ነው መሳጭ ሰብዕናን እንዲላበሱ የሚያደርገው። እርግጥ ያልሠራንበት ጉዳይ አለ። ስንችል። ግን ይህ የግራ ፖለቲካ ደንጋጣ ነው። ኮሽ ባለ ቁጥር ርብትብት ስለሆነ ሠራዊቱን ያሰልፍ እና አመድ ያስግጠዋል፤ እንጂ አቅሙም ሆነ ማሰቡም ጠፍቶ አልነበረም የቅንነት ጋላሪ መፍጠር - ቢያንስ ውጪ ሀገር። 

ይህ የተፈጥሮ ጸጋ ባለቤት ቢኖረው፤ ማህበርተኞች ቢኖሩት፤ እራሱን ችሎ ቢደራጅ ስንት ነገሮችን መልክ ማስያዝ በተቻለ ነበር። ለስንት ጎባጣ ዕሳቤዎች ወጌሻ በተገኘላቸው በነበረ። አብሶ ቂም በቀልን በጠራራ ጸሐይ አፍር አስግጠን ጉሮ ወሸባዬ እንል ነበር። ውጪ ሀገር ተወልደው ለሚያድጉ ልጆች።

የግራ ፖለቲካ ነፍሱ የተደወረችው በቂም በቀል ነው። አሁን ገጣሚ ፍጹሜ አስፋው የጀመረው አንድ የራዲዮ ፕሮግራም አለው። ጊዜ አጥቼ አላደምጥኩትም። ፓስተሩን ብቻ ነው ያዬሁት። ፖስተሩ ራሱ መልካም ነው፤ በሻማ ፎንት ስለሰራውም ራሱ የሚልከው መልዕክት አለው። ፖስተሩ እራሱ ብዙ ነገር ይናገራል፤ ብዙ ያሰተምራል። መንፈስ ቅዱስ ለቀረበው ሰው። የ2010 የቅዱስ ዮሖንስ ዋዜማ፤ የወያኔ ሃርነት ትግራይ ሰላም ነስቶ አዬሩን በጭንቀት እያናወጠ „የፍቅር፤ የከፍታ“ የፍቅር ቀን እያለ ሲያላግጥ፤ ጽንሰ ሃሳቡም ኩረጃ ነው። በዚህ ዙሪያ ከ2015 ጀምሮ ጽንሰ ሃሳቡ ተሠርቶበታል፤ አብሶ 2016 መጋቢት ጀምሮ ደግሞ የቮዲዮ ፓስተሮች ተሰርተውበታል። 

ይልቅ አዲስ አባባ ላይ ፍጹሜ አስፋው /ጋዜጠኛ ገጣሚ/  ቅኖችን ሲፈልግ፤ ሲሸልም ነበር የዋለው። የሚገርመው ቅኖች ያገኙትን ገንዘብ ለእርዳታ ይሰጥልኝ ያለች ወጣት ሁሉ አይቻለሁ። የቅኖች ብዛት መሃል አዲስ አባባ ላይ የሚገርም ነበር። 

የሌለን የሚያሰባስበን ድርጅት የመፍጠር አቅም ነው ያነሰው። ከዚህ በላይ ፖለቲከኞቹ ሁሉ ነገር በጥርጣሬ ነው የሚመለከቱት፤ ከዚህም ባለፈ ደግሞ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሆነው የሚወጡትን ይጠልፉ እና የፖለቲካ ድርጅት አባልተኛ ያደርጉና የማንፌስቶ ባሪያ አድርገው ከተልዕኮው ውጪ ያደርጉታል። የተለመደ ነው ይሄ። አቅም በሥራ አይደለም የሚታቀደው፤ በዘረፋ እና በብልጠት። ለዚህ ነው እኔ ከግራ ፖለቲካ ቅኝት መውጣት የመጀመሪያው የትግላችን ምዕራፍ ሊሆን ይገባል የምለው። በፍጹም አይድንም - በሽታው። የለንበትም የሚሉትም ልግጫ ነው። ይህ ከሆነ ውጪ አገር እንኳን ስለምን ይሆን አዲስ ዕሳቤ፤ ድርጅት ወጨፎ የሚባዘበት። 

ጀርመኖች የዳኑት በዚህ የማያወላውል ቁርጠኛ የውስጥ ለውጥ ርምጃ በመውሰዳቸው ብቻ ነው። ኢትዮጵያ ሁለት ሰው ሆኖ መቆም አይፈቀድም፤ እዚህ ደግሞ አንድ ሰው ሆኖ መቆም አይቻልም። ብቻ መሥራት እንኳን አይፈቀድም። ኔት ተዘርግቶ አጨዳውን ውቂያውን ያስኬድና በወበራ። መልካሙ ነገር ሁሉ አመድ ሲሆንለት አመዱ ላይ ቆሞ  በአሸናፊነት ይደልቃል። ወይ አያድግ እሱ ዱካ ወይ ደግሞ ሌላው እንዲበቅል አይፈቅድ። ስለምን ግራው ግራን ግራ ስላደረገው።

ስለሆነም ነው እኒህ የሁሉ የበጎ ነገሮች አባት ሊሆኑ የሚችሉትን ቅን ዶር. አብይ አህመድን ባልተወለደ አንጀቱ በቤተመነግሥቱ ሚዲያ ባለው ሙሉ መብት ጋዜጠኛ ማስረሻ አለሙ ካለ አንዳች ርህራሄ ተስፋችን የሴራ ሊኳንዳ ቤት ከፍቶ አጋድሞ ያረደው። ይህን እያዬን፤ እዬሰማን „ዝም አንልም።“ በፍጹም። 

ቢያንስ በብዕር እና በብራና እንዲህ ውልቅልቁን ማውጣት ይገባል። አይመስልህም አቤቱ ጌታው ጋዜጠኛ ማስረሻ አለሙ። የተጋሩ ሰዎች አብሶ በባዶ 6 ቤተሰቦቻቸውን ያጡት መከረኞች እኛን መቀላቀል የሚፈሩትም ለዚህ ነው። ሌሎችም ከተሳትፎ ውጪ ሆነው ተመልካች የሆኑትም ለዚህ ነው። ከብረት ቁርጥራጭ መሰራትን ይጠይቃል ከልዑላን መንፈሶች ጋር ሙግት ለመግጠም። ዛሬ ካልታገልናቸው ነገ 4ኪሎ ዓፄ ሲሆኑማ ዳፍንት ነው ዕጣችን። እኛ ልናልፍ እንችላለን፤ ግን መንፈሱ ለትውልዱ ገዳይ ነው። ለሀገርም ጠንቅ።
  • ·         ሴታዊት።

http://www.satenaw.com/amharic/archives/38082 
እሴታዊነት በኢትዮጵያ ምንማለት ነው?

እግዚአብሄር አምላክ በአዳም ከባድ እንቅልፍ ጣለበት አንቀላፋም፣ ከጎኑም አንዲት አጥነትን ወስዶ ሥፍራውን በሥጋ ዘጋው። እግዚአብሄር አምላክም ከአዳም የወሰዳትን አጥንት ሴት አድርጎ ሠራት። ወደ አዳምም አመጣት። (ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ ፪ ከቁጥር ፳፩ እስከ ፳፫።)

ወጣት የሴታዊት ሥነ - መምህራን ያላቸውን አቅም ወቄት ማውጣት አይቻልለትም። ምን ልበላቸው? ነፍስ ነገሮች ናቸው። ፍቅር ናቸው። ዘመንም ናቸው። የልሳናቸው  ጣዕም እና ያላቸው ጉልበታም የአምክንዮ አቅም አንቱ ነው - ህላዊ። ሴታዊትነት ስንፈጠር የተሰጠን ነው። ፈቅደነው፤ መርጠነው ሳይሆን የፈጣሪያችን ስጦታ ነው። የአምላካችን ሽልማት ውላችን ነው። እንድንሆንበት የተፈቀደልን የመኖር ሜሮናችን ነው። ፈጣሪ አምላካችን እዬሱስ ክርስቶስ ሲፈጥረን „ሴት“ አድርጎ ፈጥሮናል። 

„ሴት“ መሆን ተፈጥሯዊነት፤ „ሴት“ መሆን መታደል፤ „ሴት“ መሆን ክብር፤ „ሴት“ መሆን ሰብዕና፤ „ሴት“ መሆን ማንነት፤ „ሴት“ መሆን ጥበብነት፤ „ሴት“ መሆን መሆንነት፤ „ሴት“ መሆን ቅንነት፤ „ሴት“ መሆን ቅኔነት፤ „ሴት“ መሆን ፍቅራዊነት፤ „ሴት“ መሆን አዛኝነት፤ „ሴት“ መሆን አጋርነት፤ „ሴት“ መሆን ተቆርቋሪነት፤ „ሴት“ መሆን ማህበራዊነት፤ „ሴት“ መሆን መኖርነት፤ ሴት መሆን እናትንት - እህትንት - አክስትነት - ጓደኝነት - ሚስትንት - አማካሪነት - ቤተሰባዊነት ወዘተ …. ነው።

ይህ ሁሉ እያላት ሴት በመሆኗ የምታደርገው ተስትፎ ግን ከቁጥር አይገባም። እዩት ፖስተሩን እሰረኞች ዝርዝር ውስጥ ሴት እሰረኞች የሉበትም። እዩት ውይይቱን ሴት ፖለቲከኞች የሉበትም፤ እዩት የፖለቲካ ሙግቶችን ሴት የፖለቲካ ተሟጋቾች የሉበትም፤ እዩት ቃለ ምልልሱን ሴት ተጠያቂዎች የሉበትም። እዩት ድርደሩን ሴት ሊሂቃኖች የሉበትም። 40 ዓመት አንዲትም የሴት መራሂተ መንግሥት አንድትበቅል፤ ብቅ እንድትል አይፈለገም። ለቁጥር ሲሆን ግን 100,000,000 ውስጥ አብረን እንቆጠራለን። ሴቶችን እራሳቸው ብቁ ሴቶችን ይፈሯቸዋል። ሲገለሉ ደስ ይላቸዋል። 

ሴቶችን ማድነቅ የሴቶች አቅምን ባህሪ የሚፈትን ጉዳይ ነው ለራሷ ለሴቷ። እንክን ትፈልጋለች። ወንዶችን ነው ስትፈልግ በባትሪ ውላ የምታድረው። ሴቶች ለዳታ - ለተዋፆ፤ ሴቶች ለገንዘብ ያዥነት፤ ሴቶች ድግስ ደጋሾች፤ ሴቶች ወንበር አዘጋጆች፤ ሴቶች የተፈጥሮን ሂደት ለመከወን የጋብቻዊ ግዴታቸውን ለመወጣት ብቻ … የሚሻሉት አፍንጫቸው ሰልከክ፤ ጥርሳቸው ሃሞጭ፤ ቁመታቸው ዘለግ ያሉት ትንሽ ካሜራ ይፈልጋቸዋል። በውስጧ ያለው የሴት የንጥረ ነገር ቅምም ሳይሆን ዞጓ፤ ወይንም ሸበላነቷ ነው የሚመረጠው። የእኔ ቢጤ ጎራዳ፤ ጠቆር፤ ደንበል ያለችውማ ዓይንም አያስተናግዳትም?
  •  ወጣ ገባ - ስንጥርጥር - ስብጥርጥር … ቅብጥርጥር፤

እኔ እንደሚሰማኝ የኢትዮጵያ የኋላቀርነት ምንጭ አልታወቀም። ኋላቀርነት ማለት ያልተመጣጠነ እድገት ማለት ነው። ስለሆነም ኋላቀርነታችን በኢኮኖሚ እድገት ብቻ አይደለም። ተፈጥሮን የምንተረጉምበት አቅም እራሱ ኋላቀር ነው። ተፈጥሮውን የሚመጥን አቅም ማመንጨት ተስኖናል። 

ሴቶችን በሚመለከት የዛሬ አጀንዳዬ ስለሆነ በቅንነት እና በነፃነት የሚያሳትፍ ተቋም ቀርቶ እጣ ነፍስ ሃስብ የለም። ዘመን ቀዝቃዘ ነው። ዶር. አብይ አህመድ ሴት አጀንዳቸው ሆነች። ለሀገራችን ለራሷ ይህ መድህኗ፤ መዳኛዋ ነው። ለዚህ ነው እኔ „ለማውያን ነኝ“ የምለው። „ለማ“ ብቻውን አይደለም „አብይ“ አለለት። „አብይና ለማ“ ብቻቸውን አይደሉም ቅኖች አለንላቸው። አሁን ይህን ንግግር ቁጭ ብለው ደጋግመው ሲያዳምጡት የእኔ እምቤቶች ቅን ሴቶችም ከጎናቸው ይሰለፋሉ። እኛ ሴቶች ማድረግ ያለብን እራሳችን ማክበር ነው። 

ለዚህ መሰል ጤናማ ዓውደ ምህረት ማህሌትም አንቴናን ቀና አድርጎ ማድመጥ ያስፈልጋል። ስለሆነም ለእኔ የሚቀርበኝ ከፖለቲካ ማንፌስቶ በላይ፤ በላይ እኔን ሴታዊቷን ሥርጉተን እንደ ተፈጥሮዬ የሚቀበለኝ ሃሳብ ያለው ሰው ብቻ ነው። እርሳቸውም ዶር. አብይ አህመድ። አብይ ኬኛ!

አሁን ይመስገን እኛ ባለፍንብት ወበቅ ወጣቶቹ ለማለፍ የሚፈቅዱ አይመስለኝም። አገር ቤት የሴታዊት ሞጋች አቅም እውን ነው የሚያሰኝ ብቃት እዬወጣ ነው። አሁን የ2009 የጳጉሚት ንቅናቄ ልቅናው ቅኔ ነበር። እኔ እንዲያውም የፖለቲካ ተፎካካሪ ሆኖ እንደ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ መውጣት አለበት ብዬ ነው እማምነው ነገረ - ሴት። እንደ ሙሁራኑ ንቅናቄ። ያ ካልሆነ ኢትዮጵያ በዚህ በተያዘው የወንድ ዓለም የልግጫ የፖለቲካ ግጥግጥ አትድንም። እኛም እንደ ኢትዮጵያዊ የምንታይ ከሆነ ማንታችን ይከበር! ሴትነታችን ይከበር! አቀማችን ይደመጥ። 

በ21ኛው ምዕተ ዓመት አትጨፍልቁን! አትርገጡን! አትደፍጡጥን! በዚህ አጋጣሚ ሳተናውን አመሰግናለሁ፤ ከልቡ ይወደናል። የሴታዊት ድንቅ፤ ከድንቅ በላይ መሪዎችን ከዋዜማ ራዲዮ ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልስ ለጥፎት ሳገኘው ውስጡን በሚገባ አዬሁበት። እናቱን ይወዳል። ትዳር አጋሩን ይወዳል። አክስቱን ይወዳል፤ እህቱን ይወዳል። ሴት ልጅ ካለውም ይወዳል ማለት ነው። ኢትዮጵያ ሀገራችንስ በሴት አይደል የምትጠራው እሷንም ይወዳል። 

ስለዚህ ተፈጥሮን ይወዳል ማለት ነው። ይህ ማለት እንደ ሳተናው ያሉ ተብዕቶች በረቂቁ ሲተረጎም „የሰብዕዊ መብት ተሟጋች ናቸው“ ማለት ነው። ለዚህም ነው አከራካሪ፤ ብቻ ሳይሆን ግልምጫ ፤ ፍጥጫ ጸበሉ የሆነውን የእኔን ብዕር ፈቅዶ የሚያስተናግደው። አሁን ሴቶችን በሚመለከት ብቻውን አይደለም ዶር. አብይ አህመድም ከጎኑ ናቸው፤ በመንፈስ የአህትዮሽ ሃዲድ አለ። ይህን ጸጋ አዬር ላይ ፕሮፖጋንዳን የሙጥኝ ያለ የንፋስ ቁራኛ የተጠናወተው ሳይሆን፤ መሬት ላይ ወረቅ ነው። የተጋፋች ሴት ያለችው እዛ አገር ቤት ነው። የተገለለች፤ ባይታዋር የሆነች፤ ዜግነት የማይሰማት ሴት ያለችው እዛ ነው መሬት ላይ። የሴቶች የ40 ዓመት ዕንባው ያለው እዛ ነው። 

ሴት ልጅ ከኑሯዋ ተፈናቅላ መንገድ ላይ ያለችው፤ ጫካ ላይ የምትወልደው እዛ ነው። ወደ 50,000,000 የሚገመቱ ኢትዮጵያዊት ሴቶች የሰቀቀን ኑሮ የሚገፉት እዛ ነው። ሰው የሚያስፈልገን እዛ ነው። እኔ ሴት እምላት ተፈጥሯዋን ያልገደለቸውን ሴት እንጂ የጫካ አረመኔዎችን አይደለም፤ ለአራዊትነትማ ወ/ሮ አዜብ መስፍን፤ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄርን ያሉት በተቆለፈ ሳጥን ውስጥ ያሉትን የጭራቅ ቤተሰቦችን አይደለም። እነሱማ ሲፈጠሩ ለጥፋት ነው። ሲያርዱ፤ ሲያስደፍሩ፤ ጥፍር ሲያስወልቁ፤ ሲገድሉ የኖሩ … ፈርዖናዊ … 
  • ·         ግግር።

ዶር አብይ አህምድ እንዲህ ይላሉ ዘመነ እማዊ እንዴት ወደ አባዊ እንደ ተሸጋገረ፤
„በመጀመሪያ ዘመን ሴቶች ስለነበሩ የዛን ጊዜ ተጠቃሚ ኮንፒተሩን አዋቂዎች እነሱ ስለነበሩ፤ ሁለተኛው ዙር … ወንዶች በሴቶች ላይ ያረጋገጡበት ጊዜ ነው። ሴት ቤት ትቀመጣለች፤ እሱ አርሶ ይመጣል፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ቀስ እያለ እዬገነባ መጣ“
„ማን? አቶ ወንድ“ ይቀጥላሉ የአዎንታዊነት ፈላስፋው „ ወንድ የሞኝነት ትምክህት ያበጠው፤ እንዴት እንደ አበጠ ለማሳዬት ወንድና ሴት በሚያስደንቅ ሁኔታ ልዩነት አላቸው። ወንዶች በደንብ እንድትሰሙኝ እፈልጋለሁ። ሴቶች በሚያስደንቅ ሁኔታ ከወንዶች የተሻለ ብቃት አላቸው። ለምሳሌ እማዬ ትደውልና እና አንዳንድ ጊዜ ልጄ ምን ሆነሃል ማታ በህልሜ አዬሁህ፤ አሞህ ነበርን? ትለኛለች። ሚስቶች ይመጡና ልጄ አልጠባም መሰለኝ፤ ጡቴን እንደዚህ አደረገኝ፤ እያለቀሰ ነው ካልደወልኩኝ ይላሉ፤ እዚህ ተቀምጠው ሥራ ቦታ ሆነው፤“ ምን ማለት ነው ይሄ?“ ሲሉ ዶር. አብይ እራሳቸው ይጠይቃሉ።

የርቀት ዕይታ ተፈጥሮ ችሎታ natural Remote Viewability አላቸው ማለት ነው። በርቀት ስሜት Sense ማድረግ ይችላሉ። አሁን በሳይንስ የርቀት ዕይታ Remote Viewability አማሪካኖች ከናሳ ዋና መሥሪያ ቤት/ ህንድ ውቅያኖስ From NASA Headquarters Indian Ocean ላይ ምንም ስልክ ሳይጠቀሙ፤ በዛ ችሎታ Ability ብቻ መገናኘት Communicate ችለዋል። „ምናባዊ የርቀት መቆጣጠሪያ“ „Virtual Remote Control“ ይባላል።“

„ለምድነው ሴቶች እንደዛ ብቃት ያላቸው?“ ሲሉ የሴቶችን የብቃት ችሎታ ረቂቅነት ዶር. አብይ አህመድ በቀጠል ሲያመሳጥሩት „ሁሉም ሰው ግራና ቀኝ አዕምሮ Left and Right Mind ያለው ቢሆንም፤ ሴቶች more Left Minded ናቸው። ሁሉም አይደሉም። አብዛኛውን ማለቴ ነው። ምን ማለት ነው ይሄ?  ትንታኔያዊ አቅም Analytical Capacity አላቸው። በዝርዝር Detail ነገር ማዬት ይችላሉ። አንዲት ሴት በራዲዮ የሰማችውን ዜና የተረዳቸውን ልክ ያህል ወንዱ ሊረዳ የሚችለው በቴሌቪዥን TV ያዬ እንደሆን ብቻ ነው። ይህም እውነት ነው። ወንዱ በምስል visualized ካላዬ በስተቀር አይገባውም። አሁን ጨዋታው ሁሉ በዝርዝር  Detail ያለው ውስጥ ነው …

ለዚህስ ምን ማገናዛቢያ ሞጋች አመክንዮ ልታቀርብ ትችላላህ ተረበኛው ጋዜጠኛ ማስረሻ አለሙ? እንዲህ ዓይነት የፖለቲካ ሊሂቅ ነፍስ ካወቅክበት ጊዜ ጀምሮ ማዬት አይደለም አስበኸው ታውቃለህን? በግብታዊነት ውስጥ ስለተሰለፍክ፤ ማሰብ እንኳን አልተሰጠኽም። ደፍሬ ነው የምንገርህ። ግን የኔዎቹ የሀገሬ ለወጆች ---  አሁን እንዴት ነው እነዚህ ዶር. ደብረጽዮን ገብረሚኬኤል እና ወ/ሮ ፈትለወርቅ በዬትኛው የፍልስፍና ቋንቋ ሊግባቡ ነው? ወይም አማርኛውን በ አማርኛ የሚተረጉም አስተርጓሚ ካልኖሩ በስተቀር። የአዛውኑቱ ክበብ ቢሆን አይችልም። 

ይህ ልቅና በጃጃ አዕምሮ አይደፈርም። አይደለም እነሱ እራሳቸው የተማሩት አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ይችሉታል … መግባባት ይችላሉ? ማድመጡ ራሱ እንዴት ከባድ እንደ ሆነ። አንዷን ስንኝ 5/6 ጊዜ እዬመላላስኩ ነበር ያዳመጥኩት። ከባድ ነው። ሳይንስ ለሳይንቲስቶች ነው። ፍልስፍናውም ለፈላስፋው ለእነ ዶር. ዳኛቸው አስፋ። እያንዳንዱ ቃል ራሱ የፍልስፍና ፍጥረት ነው። ሞጋች ነው።

አብዛኞቹ ሴቶች ሴቶች „more Left Minded“ ናቸው።  ሲሉ እንዳለ ሳይንሱን በጥሬው ላስቀምጥ።

የአዕምሮ ግራኝ ክፍል የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን የመቆጣጠር ሃላፊነት አለበት። በተጨማሪም እንደ ሳይንስ እና ሒሳብ የመሳሰሉ በሎጂክ የሚያከናውኑ ተግባራትን ያከናውናል። በሌላው በኩል ደግሞ የቀኝ ሂሚለሪው የሰውየውን የግራ ጎን ያቀናጃል። እና በፈጠራ እና በሥነ - ጥበባት የተደረጉ ስራዎችን ያከናውናል።“ „The left side of the brain is responsible for controlling theright side of the body. It also performs tasks that have to do with logic, such as in science and mathematics. On the other hand, the right hemisphere coordinates the left side of the body, and performs tasks that have do with creativity and the arts.“ የትርጉም ዝበት ካለብኝ ይቅርታ ዝቅ ብዬ እጠይቃለሁ አንባቢዎቼን። የበለጠ ግልጽ ለማድረግ ነው ሳይንሳዊ ንድፈ ሃሳቡን አብራርቼ ለመግለጽ የተገደድኩት።

አጠቃላይ መንፈሱን ሲታይ ዘዴን፤ ብልሃትን፤ ስልትን ተክተሎ አቅሙን ብንመረምረው የሴቶችን የችሎታ ጥልቅነት እና ተወራራሽነት ገጠር ያለችውንም፤ ኑሮ ተስብሮባት ጎዳና ላይ ያለችውንም እሰቧት ያቺ ምስኪን ቤት ውስጥ ቀጥረን የምናሰራት ሳይቅር በተፈጥሯዋ ጭብጥ በሆኑ፤ ዕውነት በሆኑ ጉዳዮች ላይ የመመራመረ፤ የመፈለግ፤ የአዲስ ግኝት ቅኝት፤ የማደራጀት፤ የመፍጠር፤ እርቆ የማሰብ ሙሉዑ አቅም አላት ማለት ነው። የማደራጀትን ሙያ ነጥለን ብናዬው ዓላማን፤ ራዕይን፤ ሃሳብን፤ ፍልስፍናን፤ ምናብን ሁሉ በስርዓት የማቀነባብር ተፈጥራዊ ችሎታ አላት ማለትነው።

የርቀት ስሜት የተያያዥነት መረባዊ ግንኙት በሚመለከትም፤ የሴቶች የአባዛኞቹ ጸጋ ብቻ ሳይሆን ሴቶች በጥልቀት ወይንም በዝዝር ክስተቶችን የመመርምር ልዩ ጸጋ አላቸው ይሉናል። ይህንን በሳይንሳዊ ፋክት ነው ነው አያይዘው ያቀረቡት። የአንድ ሴል ፍተሻ የበሽታውን ምንጭ ማግኛ መሆኑን፤ በሽታው ከተገኘ መደህኒቱን አግኝቶ መኖርን ይቀጥልበታል። በዚህ የሴቶች ጥልቅና ወደ ውስጥ ነገሮችን ዘልቆ የመመርምር አቅም ወንዶች እንኳን ሊበልጡ እኩል ልንመጥን፤ ግማሽ ላይ መቆም የሚያስችል አቅም የለንም ነው የሚሉት። ስታዳምጡት ታገኙታላችሁ … ከሴል ከተፈጥሮ ሳይንስ ጋር ነው አያይዘው ያመጡት …

ይቀጥላሉ ዶር አብይ አህመድ፤ የሴትን ሙሉ የተፈጥሮ አቅም ደፍጥጦ በንፋስ ሰረገላ አዬር ላይ የሚንጎባለለው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ዕጣ ውስብስብ ችግሩን በንጸጽር ያቀረቡበት ፈለግ ደግሞ „ ወደ  ብራዚል፤ ወደ አሜሪካ ስትሄድ በዬትኛውም የምርምር ማዕከል 1,000 ሴት 200 ወንድ ታገኛለህ“ „ለምን?“ ይሉና ይጠያቀሉ። መልሱንም „Pity ናቸው ያያሉ።“ ሁለቱንም ተፈጥሯዊ ጸጋዎች ያጠመሩ ናቸው የሚል ትርጓሜ ነው የሰጠኝ። ሀዘንና ርህርሄያቸው ቅብ አይደለም። ተፈጥሯዊ ነው የሚል መልእክት ነው ያስተላላፈልኝ። ለእኔ ያስተላለፈልኝ። ማዬትን ማድመጥ - ከውስጥ። ማዬትን መተርጎም - ከህሊና። ማዬትን ማንበብ - ከልብ።
  • ·         ትኩሮታዊነት። 

„አንተ ሙሉ ቀን ተቀምጠህ ያላዬኸውን እነሱ መጥተው ከዛ ጋ ያለው ምንድ ነው? ቀለሙ፤ አልጸዳም፤ ያ ጨርቅ፤ ይሄ ጨርቅ አልተነሳም ይላሉ፤ ስለሆነም የማዬት ችሎታ አቅማቸው Capacity የላቀ ነው“
 የማዬት ችሎታ /አቅም  /ጥበብ/ ልቅናቸው ከሁሉ የበለጠ ነው የሚሉት። ይግርማል የቀጠሉት ደግሞ የችግሩን ማዕከላዊ ሴሉን ነው። በኬሚስትሪ Nucleus።

„ ወንዶች በሴቶች ላይ የበላይነታቸውን ያረጋገጡ ጊዜ ግማሽ አካላቸውን አይደለም ቆርጠው የጣሉት። ትልቁን ዕወቀታቸውን ቀበሩት፤ ዕወቀታቸውን ቀብረው ሆነ ጨዋታው።“

የኢትዮጵያ ዕዳ ይሄ ነው። ዘመን ያልፈታው ነቀርሳም። አንደ ጊዜ አንድ ሞጋች ጹሑፍ ጽፌ ነበር። ማንፌስቶ ፈራኝ ባሉት ትእዛዝ ይመስላል እንደ ተለጠፈ እያነበብኩት ነበር የተነሳው። አስታውሳለሁ ፎቶውን በኢትዮጵያዊ ምስል የእስልምና ሃይማኖታዊ ዶግማን ያከበረች እህት ፎቶ ነበርው። ዓለም አቀፍ የሴቶችን ቀን ሲከበር ለማስታወስ አንዳንድ ነገሮችን እጽፍ ነበር። አሁን አቁሜያለሁ። የዛ ጹሑፍ ጭብጥ ጥቅም ላይ ስላልዋለው የተፈጥሮ ዕምቅ ሃብት በወንዶች የፖለቲካ ዓለም የሚል ነበረ ጭብጡ። 

ይህን ያክል አስፈሪ አልነበረም። በእውነት ላይ የተመሰረተ ቢያንስ በሃሳብ ውስጥ የሴትን አቅም ያከበረ ፖለቲካ እናራምድ ነው፤ እንጂ ስልጣን አጋሩ አልነበረም። ይህ ደግሞ ድርቅ የመታው ስለመሆኑ ከ40 ዓመት በላይ ታይቷል። እኔም ወንድሜም አዬር ላይ እዬነበብነው ተነሳ። እሱ በዛ ቅጽፈት ደወለልኝ። ባልተለመደ ሰዓት ስለነበር የሞትኩ መሰለው መሰል። ምነው? ስለው ጹሑፍሽን እያነበብኩት ኢረር አለኝ አለኝ። እኔም የነበርኩበትን ነገርኩት። አይገርምም መስማት እንኳን አይፈልጉም። አለማንበብም መብት ነው። 

እኔ አሁን ከ2015 ጀምሮ ብዙዎችን አላዳምጥም። በፍጹም ስማቸው እራሱ ትዝ ብሎኝ አያውቅም። ቀድሞ ነገር የሴቶችን አቅም በሃሳብ ደረጃ ሳያከብሩ፤ ዕውቅና ሳያሰጡ ሰብዕዊነት የለም፤ ዴሞክራሲም የለም። አሁን እኔ በሰብዕዊ ተሟጋችነት የሚታወቅ አንድ ኢትዮጵያዊ አለ እማውቀው። አቅም የሴቶችን እንደ ጦር የሚፈራ። 

እሱ እንኳን የስብዕዊነት ተሟጋችነት ምልክት ሊሆን ቀርቶ የወጣበትን ማህጸን የማያከብር ነው። ታዲያ ሥርጉተ ቅጽል ሹመቱን እንዴት ጨምራ ትጽፋለች? ይሞግታል። ሴት እኮ ተሰውሮ ያለው ነገር ሰውም አይደለችም ነው እኮ። አሁን አንግዲህ ምን ይዋጠው? ድውይ መንፈሱ ሁሉ፤ ለሴቶች ፈጣሪ በጥበቡ ዓለምአቀፍ ፈላስፋ ኢትዮጵያ ላይ ሲፈጠር። እባክዎት ዶር. አብይ አህመድ ይህን የእውነት ማህጸን በእንግሊዘኛ ቋንቋ በትንሹም ቢሆን ይጻፉት። እባክዎት ልለምነዎት? ኢትዮጵያ እንዲህ ያለ ያውም በሴቶች አቅም ተኮር የሆነ ክህሎት እንዳለን ይወቁ። ይህን ቅን መንፈስ አለም ቢጋራው ወደ እውነቱ ተፈጥሮ ለመምጣት ቅርብ እንሆን በነበረ።
  • ·         የቅነነት ቅኔ።

ዶር አብይ አህመድ --- አንድ የሴቶችን የህሊና አቅም፤ ክህሎት፤ ሰማያዊ ጸጋ፤ እጬጌነት ሲገልጹ ለታዳሚው ከበደ። እጅግ ከበደ። ቀለል አድርገው አመጡት። ታናሽ ወንድሜ የሂሳብ ሊቅ ነው። እና በሂሳብ ደግሞ እኔ እስተዚህም ነበርኩኝ። እንደ ኬሚስተሪ እና እንደ ባይወሎጂ አልዳፈረውም ሂሳብን። ሲያስረዳኝ ግር ሲለኝ፤ ቆይ ይለኝና በዚህ መንገድ ሲል፤ ሳነጥርበት ደግሞ ሌላ መንገድ ደግሞ ያመጣልኛል፤ ያም ሳይሆን ሲቀር እንዲሁ በጣም አቋራጭ ስልት ያሳዬኛል። አያልቅበትም ነበር።


መቼም ዶር. አብይ አህመድ የመምህርነት አቅም አላቸው ብዬ አስባለሁ። ንግግር ጥበብ ነው። ንግግር ተስጥዖ ነው። ክህሎቱ በሥልጠና ማዳበር ይቻላል። ያካቲት 66 ፖለቲካ ኢንስቲቲዩት ይሰጥ ነበር። 40 ሰዓት 20 ፔሪድ እኔም ተምሬዋለሁ። 

እና አንድ ጥሩ ተናጋሪ ንግግሩ መድመጡ ነው የተዋጣለት ተናጋሪ ሊያሰኘው የሚያስችለው። የእኛ የፖለቲካ ሊሂቃን ደግሞ ከዚህ ውጭ ናቸው። ተናጋሪ ናቸው፤ ግን አድማጭ ምን ይላል? የሰጠሁት መልስ አርክቶኛልን? እየተከተለኝ ነውን አድማጭ? ካልተከተልኝ ስልቴን ልቀይር ወይንስ ላቁመው አይሉም። የግድ በአዳራሽ ላይሆን ይችላል። አድማጩ መጨመሩን መቀነሱን አይለኩትም።  አድማጭ የትም ቦታ ነው ያለው። 

ያልተመቸውን ማስተካክል ሲገባ ጥሰውት ይሄዳሉ። ለአድማጫቸው ያሰቡትን አምጥተው ይደፉባችኋዋል። ልክ እንደ ድንገተኛ ዶፍ ዝናብ። ወይንም በላይ ዘንቦበት እንደሚመጣ ፈረሰኛ ጋላቢ ውሃ ሙላት። ምላሹ ጉዳያቸው አይደለም። ዶር. አብይ አህመድ ግን እንደዚህ አይደለሙ። ዓይናቸው ለሰከንድ ከአድማጭ ውጪ አይደለም ሙሉ አትኩሮታቸው በሃሳባቸው፤ በመልክታቸው ውስጥ ነው መሆኑን ያረጋግጣሉ፤ ግበረመለስ feedback ፊድ በዬሰከንዱ update ተሎ ተሎ ያደርጋሉ። ከዚህ ጋር ዓይናቸው ውስጥ ያለው ተፈጥሯዊነት ህይወት ነው። በዚህ በኩል ሳዬው የሥነ - ልቦና ባለሙያነት በተፈጥሮም ያላቸው ይመስለኛል። የንግር ጥበብና ሥነ - ልቦናዊ ሙያ የተያያዘ ነው። ማህለቁ ስሜት ነው። 

ብዙ ሰው መማር አለበት እሳቸውን እያዬ ብዬም አስባለሁ። እርግጥ ነው 20 ጊዜ ስታዳምጡት ጭብጡ ሳያንሳዊ ትንታኔ ስለሆነ እጅግ ይፈትናል - ይሞግታልም። ስለሆነም አድማጭ መልእክታቸው ከአድማጩ አቀባበል ጋር አልተመጣጠነም ብለው ሲያስቡ እንደ ጌታችን መዳህኒታችን እዬሱስ ክርስቶስ፤ ልክ እንደ አባታችን ቃለ ህይወትን ሲያስተምር በምሳሌ እንደ ነበረው እሳቸውም ያነን ነው የተከተሉት። የአባታቸው ስም እንደሚነግረኝ የእስልማና ተከታይ እንደሆኑ ነው። እርግጥ ቤይሩት፤ ግብጽ፤ በእኛ ወሎ ይሄ ላይሰራ ይችላል። የሆነ ሆኖ ክርስትናን እና እስልምናን  በእኩልነት በውስጣቸው እንዴት እንደ ጸደቀ ስታዩ ጸደይ ያሰኛል።

 „ክርስትና ማለት ትንሳኤ ነው። እዚህ ክርስትያኖች አላችሁ። ማነው ትንሳኤን ያወጀው? ክርስትና ምንድነው ሚስጢሩ? ክርስትና ማለት ትንሳኤ ነው አይደልምን? የክርስትና የመጨረሻ ultimate ሚስጢር ትንሳኤ ነው! አይደል? ማነው ትንሳኤን ለሐዋርያት ያወጀው? መግደላዊት ማርያም አይደለችንም?“  አይገርሙም እኒህ ንባብ?

„ሙስሊሞችም ልነገራችሁ። ነብይ ጅብሪልን ካነጋገሩ በኋዋላ መጥተው ክድጃን ሲነግሯት ያናገርህ እኮ ጅብሪል ነው ያለችው ማን ናት? ክድጃ እኮ ናት! የመጀመሪያዋ የእስልምና ተከታይ እኮ ናት ክድጃ! የነብዩን መልዕክተኝነትን ያረጋገጠቸው የመጀመሪያ ሴት ማን ናት? „ማን?“ ብለው እራሳቸውን ይጠይቁና ይመለሰሱታል በድጋሚ አስርግጠው ይምልሱታል። „ክዳጃ!“

ወይ መታደል …  „እስልምናና ክርስትና ይህን ካለመን፤ የለም ማለት ነው። ሃይማኖቱ አይገባነም። እኛ የሳይንስ ሰዎች ነን ካላችሁ ደግሞ በጣም ጥሩ ስለሆነ እሱን ውትድራና ውስጥ አንድ ሚስጢር ልንገራችሁ።“

እኔ እዬገረመኝ ነው እናንተስ የኔዎቹ ቅኖቹ ናፍቆቶቼ፤  ወታደርም ነበሩ ማለት ነው። የውትድርና ህይወት ደግሞ የራሱ ጥበብ ስላለው፤ የራሱ ሥነ - ምግባርም ስላለው ይህም የሌላ ተጨማሪ መክሊት ባለሙሉ መብት ያደርጋቸዋል። ቀለሙ ህብሬ ነው።

„ ውትድርና ውስጥ ሴቶች አያስፈልጉም። በቅነሳ ሴቶች እንዲወጡ ተደረገ፤ እኔ ያለሁበትን ዘመን ነው የምነግራችሁ፤ በቅነሳ ወጡ፤ በጣም ብዙ ጀግና ሴቶች። የወንድ ዓለም ስለሆነ። ወንዶች ቀረን። እና ሴቶችን አስወጣን። ከዛ ድሮ አንድ ጋንታ ውስጥ ሁለት ሴት ካለች በሚያስደንቅ ሁኔታ ጀግና ተዋጊ የነበረው ሃይል መበተን ጀመረ።

 ከልቤ ነው የምነግራችሁ። ትክክለኛውን! ሴት ታጀግናለች! ብልሃት ማወቅ ብቻ ሳይሆን የማጀገን አቅም አላት! አያችሁ ወንድ በባህሪው በተፈጥሮ በማንነቱ ሴት ፊት ከመፍራት ሞቱን ይመርጣል። ታውቃላችሁ ከውጪ ሲያባርሩት እዬሮጠ መጥቶ ከእሷ ዘንድ ሲደርስ ዘራፍ ነው የሚለው“ ታዳሚው በሳቅ ፈነዳ እኔም ከልቤ ስስቅ ቤቱ ነው የሚነቃነቀው … አናጋሁት። ባለፈው ሰሞናት „ከእኛ ጋር በፍቅር ሊሞት ነው የኢትዮጵያ ህዝብ“ ብለው ጠ/ ሚር ሃይለማርያም አስቀውኝ ነበር።

  • ·         የሴቶች የአስተዳደር ብጽዕት አና የዶር አብይ አህመድ ፍልስፍና።

„ሴት የቤት ውስጥ አዛዥ ናት። ፓወር አላት። አሁን እኛ  የውስጥ ፓወሩን ውጪ የማውጣት ችግር ነው ያለብን፤ ሴት የላከው የሚባለው ዝም ብሎ እንዳይመስላችሁ፤ ቢሮው ውስጥ ሰንገባ ለምን እንዲህ አደረክ ብላ ታስቀይራለች። ግን ያ አቅሟ ከእኛ አቅም ወጥቶ እንዲታይ አንፈልግም፤ ከእስር ለመፈታት ይህንን አጉልቶ ማውጣት አለብን።“

ዶክተር አብይ አህመድ እማዊነትን በክላሽን አባዊነት ሆነ ነው የሚሉት። „የወንድ ዓለም“ ጥቁር ዘመን፤ ብርድ የመታው ዘመን። በምች የሚቃጠል ዘመን። በመጋኛ የተሰቀዘ ቀመር። ቆሽቱ እርር ድብን ብሎ የተቃጠለ ዘመን።

ግን የኔዎቹ ቅኖቹ  … „ምን ልበላቸው ማን ልበላቸው?“ ህሊናዬ፤ መንፈሴ፤ ትልሜ፤ ራዕዬ፤ የልቤ መሠረት ከቶ ምን ልበላቸው ዶር. አብይ አህመድን። ታዲያ እኔ ሥርጉተ ሥላሴ ወንድሜ ቢሆኑልኝ ብዬ ብመኝ፤ የጽድቅ የእዬሩሳሌም ወይንስ አንደ እስልምና እምነት ተከታዮች የመካ መዲና ጉዞ አይደለምን ይህ የፍልስፋና አቅም? ወገኖቼ ሁሉን አልጻፍኩትም የተወሰኑትን ብቻ ነው የጻፍኩት። አንዴት አንደሚፈውስ። መዳህኒት እንዲህ ይላካል፤ እና የእኔ ጥበቦች፤ የሴታዊት አርበኞች፤ የእኛ ነገርም ጉዳያችሁ የሆነ ተብዕቶች ግን ቅኖች ይህን ሩህሩህ፤ አነሳሽ መንፈስ፤ ሃይል ሰጪ መንፈስ የተራራው ቅዱስ ስብከት ብንለው ያነሰዋልን? 

ብንከተለው፤ አቅም ብንሆነው፤ አይዞኽ ብንለው ያነሳል? ይበዘባታል? ጣይቱን - ተዋቡን - ዘውድዬን - ሰብለወንጌል እኮ ነው የናፈቀቱ - ዛሬ? ለእኔ አላሉም? ኢጎ የለባቸውም፤ የሥልጣን ጥማት ወረርሽኝ የለባቸውም? ተፎካካሪ አቅምን እንደ ጦር አልፈሩትም። የሴራ ድር አለደራባቸውም፤ ወይንም የአስተሳሰብ ድህነት አልጎበኛቸውም፤ የፍርሃት ፍላትም ድርሽ አላለባቸውም። ዕውነትን፤ ሃቅን፤ ፋክትን፤ ተፈጥሮን በድፍርት ሆኑበት። የእውነት አምክንዮ ታታሪ / አክቲቢስት። የተፈጥሯዊነትም ታታሪ፤ የፍቅራዊነትም ታታሪ /አክቲቢስት …. ሊቀ ትጉሃን … ምን ይባሉ? የአንስት ብዕር ራድ ለሚያስዘው ሁሉ ማርከሻ ናቸው።

ይህ የሴቶች ዋስትና ጠበቃነት ምልከታዊ አሸራ ብሄራዊ ብቻ አይደለም የኮፐን ሀገን ወጋገን ነው። አህጉራዊም/ ዓለም አቀፋዊም። ለስሙም ቢሆን ዓለም ዐቀፍ የሴቶችን ቀን የሴት እሰረኞች ጥፍር በሚነቀልባት ኢትዮጵያ፤ ልጇን ገድሎ ከሬሳዋ ላይ አስቀምጦ እናት የምትደበደብባት ሃገር፤ በሱዳን ወታደር ህፃናት በጅምላ የሚጨፈጨፉበት ኢትዮጵያ ቅን ሴቶች ካላችሁ፤ ከኖራችሁ የዘንድሮ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን የክብር እንግዳ አድርጋችሁ ብታሳያኝ አይደለም እኔን የነዛን የደጋጋቾን አንስት መግደላዊት ማርያም እና  የክድጃም ቅድሱ መንፈሳችውን ልከው አብረው ያከብሩታል በዓሉን። ትምረቃላችሁ።

እንግዲህ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ካልነጠቀን፤ ካልቀማን፤ ተስፋችን ከልዋጠው። „ለማውያን“ እንዲህ ናቸው … ኢትዮጵያን ውስጧን፤ ተፈጥሮን ማህሉን ሳይመረምሩ ነው ሊሂቃን ሀገር እንመራለን የሚሉን? እነ „ለማውያን“ ግን ስትወለድ ብሄርህን ልሁነው ብለህ አይደለም፤ ሰው መሆንህን ተቀበል እያሉ ነው። ሰው በመሆን ውስጥም የሰውን ሰውነት የሚያጎላውን የአካልህን መክሊት ቀብረህ አሸንፋለሁ አትበል፤ የቀበርከውን አቅምህን ትንሳኤውን እወጀው እያሉን ነው። በተፈጥሮ ብቃት ሸልመው እያሉ ነው። … የእኔ መመሰጥ፤ የእኔ ጥሞና፤ የእኔ ተደሞ የእኔ „አብረንታት“ በዚህ ውስጥ የበቀለ ነው። እርግጥ ትናንት አንድ ዜና ከአባይ ሚዲያ አዳምጬ ነበር። 

የወያኔ ሃርነት ትግራይ በጠነከረ ሁኔታ እንደሚከታታላቸው፤ ይህም ያልተመቻቸው ሌሎች ደግሞ ከጎናቸው ተስልፈዋል። እነኝህ ሃላፊነት የሚሰማቸው ወገኖች የነገ የትግራይ ልጆች፤ ማህጸን፤ የኢትዮጵያም የአብሮነት ጉዞ ያሳሰባቸው ናቸው። ለዚህ መብቃትም ትልቅ ነገር ነው። እኔ አክብሬዋለሁ። መልካም ነገሮችን መልካም ካልሆኑት ጋር የምንለይበት ማንዘርዘሪያ አለመኖር እጅግ ጎድቶናል። ማህበራዊ ህይወታችን አቃውሶታል። ተፈጥሯችነንም ሞግቶታል። ከእንግዲህ ግን የውስጥ ለውጥ ማምጣት አለበን። አሉታዊ እሳቤ ላይ ፈጣን መሆን በሽታ ነው። ስለዚህ በሳቸው ጎን ያሉትን ወገኖች ጠንክረው ህይወታቸውን እንዲታደጉ/ አንዲጠብቁልን በአጋጣሚው በትሁት መንፈስ ላሳስባቸው እሻለሁ። አቨዎም ጸሎታቸውን በትጋት ያድርጉ ዘንድ አምጸናቸዋለሁ።

የወያኔ ሃርነት ትግራይ ሴራ ምስጥና ሽንክ ነው። አሁን የሁለቱን የመንፈስ ጥምረት ለመሰንጠቅ አንዱን ላይ ሌላውን ታች በማድረግ፤ ወይ አንስቶ ሌላ ቦታ በመሸጎጥ በአቶ ለማ መገርሳና በዶር. አብይ መካከል መጠራጠር እንዲሰፍን ለማድርግ ሊሠራ ይችላል። ይህም የሁለቱ የፈተና ዳገት ነው። አንዱን አቅርቦ ሌላውን በማግለል ለመምታትም አድብቷል። የሚፈልገውን መረጃ ምንጣፉን ዘርግቶ አሰባስቧል። ለበቀለኛ ሥርዓት፤ ለሴረኛ ርዕዮት፤ ለግራ ፖለቲካ ያን ያህል ግልጽነት የተገባ ባይሆንም፤ ቢያንስ ለመተርተር የሚያደርገውን ጉዞ ድል መንሳት የሚቻለው በአንድ መንፈስ ዳገቱን ለመሻገር በመጽናት ነው። ጽናቱን ይስጥልኝ ፈጣሪያችን። አሜን! 

በአንድ ላይ የማይነካ በመሆን የማይደፈር ውስጥነት መገንባት ያስፈልጋል፤ ሃሳብን ከተከፈለ ግን „አንድ አንጨት አይነድም፤ አንድ ሰው አይፈርድም“ ይሆናል። ይህን የፈተና ዳገት መሻገር የሚሊዮኖችን ነፍስ ብቻ ሳይሆን የትውልድም ጉዳይ ነው። የዘመን ጉዳይ ነው። ነገ እንዳይደርቅ፤ ቢመጣም ጠውልጎ እንዳይሆን ጥንቃቄም ያስፈልጋል። ፈተና ላይ ከራስ በላይ ታማኝ የለም። የማሰወር ሴራ ሁሉ ይኖራል። 

ሁሉን የጥቃት ዓይነት ሊሞክሩ ይችላሉ፤ የምግብ ብክለትም። ምክንያቱም መንፈሱ ሳጥናኤላዊ ነው። አዬሩ ጥሩ አይደለም። ሥልጣን የሚባል ነገር እብድ ነው። ምን ያቅታል „በቃችሁን“ ማድመጥ አንድ የትውልድ ዘመን ሁሉን ተገዛ፤ ተነዳ .. እይበቃንም? … ነገ አይሆኑ ሁኖ ተነዳደለ … 

TPLF factions argue on the fate of Dr. Abiy's Fate | Abbay Media // http://abbaymedia.info/76013-2/ እነ „ለማውያንን“ ጋዜጠኛ ማስረሻ አለሙ በፕሮፖጋንዳ ዘመቻ እዬተፋለማቸው ሲሆን፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ ወያኔ ራሱ በቅኑ ኢትዮጵያዊ ፖለቲከኛ ምክንያት ከሁለት ተክፍሏል። 

ተመስገን የምለው ከወያኔ ሃርነት ትግራይ ውስጥም ይህን መንፈስ ጥጋቸው ያደረጉና የሚፋለሙላቸው ወታደሮች መኖር የነገ መባቻን፤ የነገ መሰንበቻን፤ የነገን ጉዟችን ልዩ መክሊት ነው። መዳኛችን የሚሆነው ይህ ብቻ ነው። ቅኖችን መጠበቅ ቢያንስ ለህጻናት ሲባል። ቢያንስ ለነፍሰጡር እናቶች ሲባል። ቢያንስ አካል ለጎደለባቸው - ለማይሰሙ - ለማይለሙ ድውይ ወገኖቻችን ሲባል። አንድ ነገር ቢፈጠር እነሱን ማን ይሰበሰባቸዋል? ሃላፊነት ይሰማን። ሰው ጥሎት ሲሞት ሰኔል እና አፈር ነው ርስቱ። ምን ተከተላቸው የቀድሞው ጠ/ሚር መለስ ዜናዊ … ምንም … ለኑዛዜ አልበቁም። የአባ ጳውሎስ ሞት ራሱ። ከንቱ ነን።
  • ·         ብላኝ።

ጋዜጠኛ ማስረሻ አለሙ ይብላኝ አንተን ለተሸከመው የኢሳት ኤድትርያል ቦርድ። ለነገሩ አይሰሙም እነሱ? የነገ የቤተ መንግሥቱ ሚዲያ በቃሉ አማራ አልፎ አልፎ  ይላል „ተጋድሎ“ ባይልም? የሚያምኑት ፓርቲያቸው ለውጪ ሃይል፤ ለአውሮፓ ኮሚሽን ሆነ ለአሜሪካ አሸማጋዮች አሁን እዬገዛ ያለው የትግራይና የአማራ ህዝብ ብቻ ነው ብለው አሳምነዋቸዋል? የነገ ጥቁር ቀን ደም አንዣብቦታል?  ይህን እንኳን ደፍሮ ወጥቶ ማስታረቅ አልቻሉም ሌሎች ሊሂቃናት። በሥጋ መለዬትንም አላሰቡት። 

የሚገርመው እዛ ውስጥ አማራዎች ይኖራሉ ብዬ አስባለሁ። ይህን ሃቅ ሊያዩት አልቻሉም - አይፈቅዱም። እንደ ቀድሞው ኢትዮጵያ አርበኞች ግንባር ዕጣውን በጊዜና በሁኔታ በራሳቸው ደርሶ እስኪያወራርዱት ድረስ። የቀድሞው ኢትዮጵያ የአርበኞች ግንባር አይደለም መሬት ላይ የኮሎንቮስ ኦህዩ ቤተሰቦቼ ስንት መስዋዕትነት እንደ ከፈሉብት እራሴ አውቃለሁኝ። እኩል ነበር ቅንጅት እና ግንባሩን ይረዱ የነበሩት። ዛሬ „እጸድቅ ብዬ ባዝላት ተንጥልጥላ ቀረች“ ነው የሆነው። ሙሉ ለሙሉ ዓላማው ሳይቀር ነው የተለወጠው። ጉባኤው መፈክሩ በትግረኛ ሲሆን አንኳን አንድም ደፋር ሞጋች ጋዜጠኛ አልተገኘም። ከቁጥርም አልገባም።

ለመሆኑ 2.5 ሚሊዮን የጠፋው ፌንጣ ነበርን? ኢሳት ሚዲያው ሁሉ ነገር በትግራይ መሳፍንት ተያዘ እያለ፤ በዚህ ዙሪያ በመረጃ የተደገፉ ትንተናዎችን ይሰጣል። አዳማጭን ላለማጣት፤ አብሶ የአማራን ሠራዊት የህሊና መሬት በእጅ ለማስገባት። 

ፖለቲካው ደግሞ የተገለበጠውን ነገር ይሰራል። ይህን ማን ይደፈረው? ጋዜጠኛው? የሰብዕዊ መብት ተሟጋቹ? የሲቢል ድርጅቱ? እኔ የሚገርመኝ ድምጻቸው የሚናፍቀኝ የዶር. ኮንቴ ሙሳ ዝምታ ነው። ጋዜጠኛውማ ማንፌስቶ እንጂ እውነትና ሰው አይደለም ማዕከሉ? ለመሆኑ አማራ እዬገዛ አማራ ዘሩ እንዲጠፋ በፖሊሲ ደረጃ ያውጃልን? እርግማን ነው። ይህ በውነቱ የልጅ ልጅ አያወጣም፤ ኧረ ግፍም - ጡርም ፍሩ?! በዚህ ዙሪያ አንደ ተቋም መስጥሬ እንደ አንድ አብነታዊ ተቋም የማዬው ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌናን ነው። ከኢሳት ተቋም ይልቅ አማዝነው በሱ ነው። ሰብዕናው ችሎት ነው ብዬ አምን ስለነበር።   

የሆነ ሆኖ እግዚአብሄር ይመስገን በፈለገው ሁኔታ አሁን  ሀገር ቤት ያለው የለወጥ ንፋስ ቢገለባባጥም፤ አክሮባት ቢሰራም ወደ እኔ የቀረበው መንፈስ፤ እኔን ሊያይ የፍቅር ስንቅ ቋጥሮ ወደ ባህርዳር፤ ወደ ጎንደር የገሰገሰውን መንፈስ የእኔ ማለቴ በጽናት ይቀጥላል። እኔን አማራዋን ሥርጉተ ሥላሴን እንደ ኢትዮጵያዊነቴ ያዬኝ፤ እኔን እንደ ተዋህዶ ልጅነቴ፤ እኔን እንደ ሴታዊትነቴ፤ እኔን እንደ ጸሐፊነቴ፤ እኔ እንደ ጎንደሬነቴ እኔን እንደ አማራነቴ የተቀበለ „ኢትዮጵያዊነት ሱስ ነው“ መንፈስ የእኔ ነው። ጌጤ ነው። ጉልላቴ እና በፍጹም ሁኔታ የማልደራደርበትም ነው። ዘውዴ ነው። 

ትናንትም ጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድ አንድ የብሥራት ዜና ዘግቧል። የአፍሪካ የመጀመሪያው የጥቁሮች ሽምቅ ውጊያ ልዑል የብኽሩ ጎሬ ታሪኩን በታሪክ አበልጽጎታል። የመቱ ሙሉ ህዝብ „አማራ የእኔ ነው“ ብሏል።  „በአማራ ህዝብ እንዳትመጡብኝ“ ሲል በተደሞ ቃለ ወንጌል ጽፏል። አዎን እኔ ሥርጉተ - ሥላሴ „ለማውያን“ ነኝ። 

አሁን በአቦ አባ ዱላ ገመዳ የአቅም መነቃነቅ፤ ተስፋ ቆራጭነት ያንዣብባል። እኔስ እላለሁ --- የተዘራው ሁሉ አይበቅልም። የበቀለው ሁሉ አይሰብልም። የበቀለው ሁሉ ፈጣሪ ካልፈቀደ ለጎታ አይበቃም፤ ቢበቃም ጤና አይሰጥም። ትልቅ ዘር ዘርተዋል።

 አማራ መሬትና ያ ደግ የአማራ ህዝብ ህዝብ የኦህዲድ አኮስጂን እንደ ነበር። ካህዲዎችን የጎንደር መሬት ሰው ያደረጋቸውን አስደንግጠዋል። ለእኔ ከዚህ በላይ ድል የለም። ቀሪው ንግሥና ቅብዕ ስለሆነ የፈለገ ቢይዘው ጉዳዬ አይደለም። ባለማንፌስቶ ይውደቅ ይነሳ። እንቅልፍ ይጣ … ይማስን፤ እኔ ያ የፋሲል፤ የሱስንዮስ፤ የልብነ-ድንግል፤ የሰብለ-ወንጌል፤ የበካፋ ደም ህትምት ጥሪኝ ብቻ ከአድዋ ድል በላይ ነው። በዚህ ዙሪያ ጊዜ ተርፏቸው ሙግት የሚያደርጉ ሙሁራን እግዚአብሄር ይፍታቸው እላለሁ። ያበቃ የተከወነ ነገር ነው። አብይ ኬኛ!  ይቀጥላል … 
   
ጎሬ ከተማ ዉስጥ ታላቅ የተቃዉሞ ሰልፍ ተደረገ | ከአማራዉ  ወገናችን  ጋር  ሊያጋጩን  የሚሹ  ጨቋኞችን  እንፋለማለን
  • ·         አቤቱ የቀን ሙላት ሆይ! እንደ መከወኛ።

በዚህ አቅጣጫው ባለዬለት አውሎ ቅኖችን በልቶ፤ ወይንም ቅኖችን ወደ እስር ገፍትሮ፤ ወይንም ቅኖችን አራቁቶ የሚጋልቡ የኢጎ ፈረሰኞች የሚያሰራጩትን የሰለባ ፕሮፖጋንዳ ገሸሽ አድርገህ፤ መቅኖም አሳጥተህ፤ ጤና አዳሞችን አምላካችን ይጠብቅልን ዘንድ አቤት ማለት አለብን - ቅኖች - ሩህሩሆች። በተጨማሪም ሁላችንንም እንደ ባህሪያችን፤ እንደ ቀለማችን፤ እንደ ውበታችን በሃሳቡ የሚያቅፍ መንፈስን እንዳውቀው ፈጣሪ መንገዱን ስለጠረገልን የተመሰገነ ይሁን። አሜን! ስለ ሴቶች ተፈጥሯችን የሚጨነቅ፤ የሚጠበብ ሊሂቅ ስለገኘንም አማላካችን አሁንም ተመስገን። ዶር አብይ አህመድ አመሰግነዎታለሁ። ድንግል ትጠብቀዎት። አሜን! 

ስለሆነም የትናንትናው ታላቅነታችን ዛሬን ከሰጠን፤ የዛሬ ኮሰን መታዬታችን እንደ ትናንቱ ታላቅናታችን ወደ ተፈጥሯችን እንመለስ ዘንድ የሚታትሩትን ሐዋርያትን አምላካችን ከሰጠን ልንከተል ይገባል። ጥላቻ አመድ ነው። የማያበቅል - የማይበቅል። ጥላቻ ግርድ ነው የማያጸድቅ - የማይጸድቅ። ጥላቻ ትቢያ ነው የማያተርፍ - የሚያከስል፤ ጥላቻ ድቡሽት ነው የማይገነባ - የሚያፈርስ፤ ጥላቻ ደወዬ ነው የማያድን - የሚገድል፤ ጥላቻ እርግማን ነው የሚቀበር - የማይፈውስ። ጥላቻ የክፉ ነገር ህንፃ ነው በላይ ላይ የሚደረምስ።

አንዱን አቅርበህ ሌላውን ስታርቅ፣ በውስጥህ ጥላቻ ግንብ ቤተኛ መሆንህን አታስተውለውንም? አንዱን አክብርህ ሌላውን ስታግድ በመንፈስ የጥላቻ አግናባት ማህበረተኛ መሆንህን ልብ አላለከውምን? አንዱን ፊት ነስተህ ሌላውን የመንፈስ ቅርብ ስታደርግ ጥላቻን በነፍስህ ወደህ መሪህ፤ ማደሪያህ ማድረጉን አስበህው ታውቃለህን? ስደት ላይ አንዱን የቤት ልጅ ሌላውን የጎረቤት ስታደርገው ከክፋትን ጋር ህሊናህ ከተማ መሥረቱን ልብ አላልከወንም? ፈትሸው - ተፈታሹ?  „ልብ ያለው ሸብ“ ለቅኖች ብቻ።

ሴቶች ጥበቦች ናቸው።

ሴቶች ቅኔዎች ናቸወ።
ሴቶች የነፍስ ጣዕም ልዩ ዜማዊ ቃናዎች ናቸው።

እግዚአብሄር ይስጥልኝ። መሸቢያ ጊዜ።

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።