በምእራብ ሽዋ አንዲት የ7 ዓመት ቀንበጥ #ተደፍራ በጭካኔ #መገደሏን ዜና አዳምጫለሁኝ።

 

 
 
ሌላም አሳዛኝ ዜና በኦሮምያም አለ። በምእራብ ሽዋ አንዲት የ7 ዓመት ቀንበጥ #ተደፍራ በጭካኔ #መገደሏን ዜና አዳምጫለሁኝ። ህፃን ሱንባ ብርሃኑ ይመስለኛል ስሟ። ትምህርት ቤት እንደ ሄደች ነው እንደወጣች የቀረችው። 
 
ይህ አረመኔያዊነት መቼ እንደሚቆም ይናፍቀኛል። #የጭካኔ #ፋክክር። የጠቅላይ ሚር አብይ የብልጽግናቸው ወፈ ሰማይ 15ሚሊዮን አባላት ከፊሉ አካል ነው የማንን ጎፈሬ ሲያበጥር ውሎ እንደሚያድር እግዚአብሄር ይወቀው። የዜጋው ህሊና ይህን ያህል ሸፍቶ ጭካኔ ሲነግስ የተሰባሰበው የአባላቱ ተግባር {} ምንም መሆንን የሚያመለክት ነው።
 
የሆነ ሆኖ #ወላጆች ሆይ! እባካችሁን ልጆቻችሁን ጠብቁ። ዘመኑ ልብ አስጥሎ የሚያስቀምጥ አይደለም። ለህፃኗ እንደ ህፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ሰማዕትነት ነው። ለቤተሰብ ግን የዕድሜ ልክ ሃዘን ነው። መጽናናትን እመኛለሁኝ። አይዟችሁ። ፎቶዋን ስላላገኜሁት ነው ያልተለጠፈው። አሁን ያገኜሁት ይመስለኛል። 
 
#በአጠቃላይ ግን የቀጣዩ የኢትዮጵያ ተስፋ #አደጋ ላይ መሆኑን አመላካች ክስተት ነው።
 
ሥርጉትሻ2025/02/02

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

የእኔ እማ ልዕልቴ እንዴት ነሽ?