ልጥፎች

ከሜይ, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ #የፈረንሳይ ጉዞ እና ዕይታዬ።

ምስል
  የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ #የፈረንሳይ ጉዞ እና ዕይታዬ።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"       #እፍታ ።    በጣም ረጅም ጊዜ ሆነኝ የጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድን ፎቶ ለጥፎ መሞገት ካቆምኩኝ። ምክንያቴ #አመክንዮዊ ነው። ዛሬም ግጥም የሆነ ቁምነገር ተገጣጥሞብኝ ነው እንጂ ፍላጎት የለኝም የሳቸውን ፎቶ ለጥፎ መሞገት። የሻሸመኔ ሰማዕትነት ሂደት ለጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ፍላጎት ሞተሩ ተተከለ። ጥረታቸውም ድሉን ሀሌታ አለ። የአሜሪካ ጉዞ እና ስደተኛው ሲኖዶስን …?// የህክምና ባለሙያወች ለምግብ እጥረት መጋለጥ አቤቱታ እና የነነዌ ሱባኤ በኢትዮጵያ እና የጠቅላዩ የፈረንሳይ ጉዞ የዛንጊዜውም ሆነ የዛሬው …??? ዘመኑን እኔ #አሳቻ እለዋለሁኝ። መሪውንም ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ አሊን አሳቻ መሪ እላቸዋለሁኝ። የዘመኑን የፖለቲካ ባህሬም አሳቻ ነው እላለሁኝ። ኢትዮጵያ መስቀለኛ መንገድ ላይ ሳትሆን አሳቻ ሁኔታ ላይ እንዳለች ነው የሚገባኝ። መስቀለኛማ ወይ ስሜን፤ ወይ ደቡብ፤ ወይ ምስራቅ ወይ ምዕራብ ትንሽ ዘለግ ሲልም ስሜን ምስራቅ፤ ደቡብ ምዕራብ እያለ ይቀጥላል።   አሳቸነት ግን አቅጣጫውን ለመወሰን ይቸግራል። አቅጣጫውን ለመተንበይም #ጋዳ ነው። በጠቅላይ ሚኒስተሩ አውሮፕላን ስደተኛው ሲኖዶስ ወደ አገር ሲገባ ማን ይህ ይሆናል ብሎ ተነበዬ? ማንም። ሐሤታችን ከእልልታ በላይ ነበር። ይዘው የወሰዷቸውን አትገቧትም ብለው "አገር ናት ያሏትን" ሃይማኖት ቢዛ ሰጪም፥ ነሺም ሲሆኑ ማየት የሚተነበይ አልነበረም። አሳቻነትን ቢገልጽልኝ ብዬ ነው ይህን ለንጽጽር ያቀረብኩት። ደጋፊወቻቸውም፤ አክባሪወቻቸውም ሆኑ አጋዥወቻቸው ያወቋቸው ይምስሏቸው እንጂ አያውቋቸውም።   ጠ...

የጤና ባለሙያወች #የራሳቸው #ጉዳይ ነው በህብረት ያስነሳቸው። ሌላ ገፊ ኃይል ያላቸው አይመስለኝም።

ምስል
  የጤና ባለሙያወች #የራሳቸው #ጉዳይ ነው በህብረት ያስነሳቸው። ሌላ ገፊ ኃይል ያላቸው አይመስለኝም።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"       በዘመነ አብይዝም የ፯ ዓመታት የአገዛዝ ሂደት ኢትዮጵያ ውስጥ ያልታዬ የፈተና፤ ያልተሞከረ የቀውስ፤ ያልተመለከትነው የሴራ ድንኳን የለም። 100 ቀናት ሳይሞላ ገና በልጅነት ዕድሜው ከሰኔ 16 ጀመሮ በመላ ኢትዮጵያ ያልታዬ የፈተና ቡፌ የለም። ደቡብ ምን ያህል ህዝብ ነው የተፈናቀለው። የገዴወ፤ የጋሞ ህዝብ ምን ዋጋ ከፈለ። ቡራዩ ለገዳዲ አዲስ አበባ ፦ ብቻ ፈተና ኢትዮጵያን ፈተናት።   ቀውሱ በመንግሥትም ታቅዶ፤ መንግሥት ውስጥ ባሉትም ተመስጥሮ እንዲሁም በፊት በምን አቅሙ እል የነበረው #ህወሃት መራሽ ሴራም በሚችለው ሁሉ በቀውስ አምራችነት ላይ ተሳትፎ እንደ ነበር ዛሬ ባለው የህውሃት የትርምስ ማሳቸው ለመገንዘብ ችያለሁኝ። ከዚህ ጋር ተያይዞም የህወሃት ሆነ የኢህዴግ #ተስፈኞችም ተመሳሳይ ትጋት እንደ ነበራቸው ቢዘገይም ምልክቶቹ ዛሬ ይፋ ናቸው። በምን መሥፈርት ህወሃት እንደሚናፍቅ ባይገባኝም።    የሆነ ሆኖ በህወሃት እና በብልጽግና #ልግዛህ እና #አልገዛም ጦርነት፤ በብልጽግና እና በአማራ ትጥቅ ፍቱ፤ አንፈታም የነፍጥ ተጋድሎ፤ በኦነግ የጫካው እና በብልጽግና፤ በኦነግ መንፈስ እና በአማራ ህዝብ የደረሰው ሰቆቃ ውስጥ የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያወች #ቤተ - ሳይለንት ማጆሪቲው ውስጥ ነበሩ። እርግጥ መጀመሪያ ላይ ከጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ጋር በነበራቸው የጋራ ቆይታ ጥያቄያቸውን ከሞላ ጎደል ማንሳታቸውን አስታውሳለሁ። ይህም #በራሳቸው #ጉዳይ ላይ ብቻ ነበር።   የኢትዮጵያ የህክምና ባለሙያወች በየትኛውም ሁኔታ፤ በማናቸውም ጊዜ የሙያ...

"የሐኪሞቹ መሠረታዊ የሆነው የመብት ጥያቄ ምላሽ ይሻል!" (ነጭ ቁጣ - Witte Woede) የአቶ ያሬድ ኃይለማርያም ዕይታ

  "የሐኪሞቹ መሠረታዊ የሆነው የመብት ጥያቄ ምላሽ ይሻል!" (ነጭ ቁጣ - Witte Woede)   ትናንት ከሃሳብ ገበታ ጋር የነበራቸውን ቆይታ ዘግቤ ነበር። ድርጅታቸውም መግለጫ እንዳወጣ ሲገልጡ ሰምቻለሁኝ። አንድ ሃኪም ደም የሚሰጥ ላጣ በሽተኛ ደም መስጠቱን፤ ሌላ ሃኪም ከአባቱ የመጨረሻ መራራ ስንብት ይልቅ የበሽተኛው ቀዶ ጥገና በልጦበት በዛ ላይ እንዳተኮረ በዕውነት የተየሠረተ መረጃ ሲሰጡ ሰምቻለሁኝ። ዛሬ ከአቶ መላኩ በላይ ፔጅ ያገኜሁትን እንሆ። የጨመቱ፤ በንግግራቸውም ጥንቁቅ፤ ቋሚ የሆነ የሰባዊ መብት ትጋት ያላቸው በመሆኑ የማከብራቸው ናቸው።    ተቋማቸው ታግዶ ሁሉ ነበር። የዓለም የሠራተኞች ቀን በኢትዮጵያ ከታሠረ ሦስት ዓመታት እንዳሳለፈ ሲናገሩ ሰምቻለሁኝ። የሠራተኛም አደራጅ ስለነበርኩ ውስጤ ቁስል ነው ያለው። ሠራተኞች የህብረት ድምጽ ማሰሚያ ቀናቸው ሲታሠር እሰቡት። ወይ አብይዝም????? መጨረሻውን ያዬው ሰው። #ዕድሉን ሁሉ እጥፍጥፍ፥ #ኩፍትርትር እያደራረገ የት ሊደርስ ይሆን???? የአቶ ያሬድ ኃይለማርያም ዕይታ …………   "በሕክምና ሙያ ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎች በድፍን ጦቢያ ላይ ያጠላውን የፍርሃት ድባብ ገፈው 'ኽረ እየተራብን ነው፣ ብዙ አመታትን ተምረን አገር እያገለገልን እኛ ግን ተረስተናል፣ ደሞዛችን የኑሮን ውድነት እንድንቋቋም አቅም የሚፈጥር አይደለም፣ በቀን አንድ ጊዜ መብላት አቅቶናል' በሚል ለአመታት ውስጥ ለውስጥ ሲያጉረመርሙበት የቆየውን ብሶት ዛሬ አደባባይ ይዘው መውጣታቸው ይበል የሚያሰኝ ነው። መብትን ሰላማዊ በሆነ መንገድ መጠየቅ ስልጡንነት ነው።    መንግስት ትኩረት ከነፈጋቸው ዘርፎች መካከልና የመጨረሻው የትኩረት ተርታ ላይ የሚቀመጡት ትምህንትና ጤና ናቸ...

የጤና ባለሞያዎች ጥያቄ ከሰብአዊ መብት አንፃር ሲዳሰስ

ምስል
"የኢትዮጵያ ሃኪሞች #ጀግኖች ናቸው።" (አቶ ያሬድ ኃይለማርያም የሰባዕዊ መብት ተሟጋች ማዕከል መሥራች) ሁለት የህግ ባለሙያወች የህክምና ባለሙያወችን ጥያቄ ከህግ አንፃር እንደምን ገመገሙት?   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   ኢትዮ ሰላም ዩቱብን ዝግጅት መጨረስ ያቃተኝን ይህን ጨዋ፤ የጨመተ፤ ሥልጡን፤ የህግ መሠረትን ያገናዘበ ሰውኛ እና ተፈጥሮኛውን የሃኪሞች ጥያቄ አስመልክቶ የተደረገውን ውይይት ደግሞ #ሁለት ጊዜ አዳምጨዋለሁኝ። የሚገርመው የአስተያዬት ሰጪወችም ተሳትፎ ዲስፕሊንድ የሆነ #የውስጥነት #ቀለም ያለው ነበር ማለት እችላለሁኝ።   ይህን ቃለ ምልልስ አደብ ገዝቶ ላዳመጠው የነጭ ለባሾች ቁጣ ታሪክንም በምልሰት የቃኜ፤ አሁን ያለውን የኢትዮጵያ ያሃኪሞች ጥያቄ ግሎባሊ ያለውን የተደማጭነት ልክ የገመገመ፤ የንቅናቄውን አነሳስ፤ አካሄድ እና አስተዳደሪዊ አቅሙንም ዕውቅና የሰጠ፤ ጥያቄውን #በቅንነት እና #በቀናነት የተመለከተ፤ በዝበት ለሚነገሩ አገላለፆችን ሙያዊ እርምት የሰጠ፤ ለአብይዝምም ጥንቁቅ የመፍትሄ ሃሳብ ያቀረበ ውይይት ነው።    አወያዩ ልጅ ሞገስ ተሾመም፤ ተወያዩ አቶ ያሬድ ኃይለማርያም የህግ ባለሙያወች ስለሆኑ ቋንቋቸው ወጥ እና መምህር ነበር ማለት እሻለሁኝ። አጀንዳ በሳሰበት የኢትዮጵያ ፖለቲካ ይህን መሰል የሙያ ነፃ ትምህርት ቤት ሲገኝ ቁጭ ብሎ መማር ብቻ ሳይሆን ዝበት የሚያሰኛቸው ዕይታወችንም ማረቅ፤ ማስተካከል ይቻላል።    ከሁሉ የውስጥን ችግር የእኔ ብሎ መቀበል፤ ዕውቅና መስጠት የማግሥትን የትውልዱን ተስፋ ያለመልማል። በምልሰት ህወሃት ሥልጣን በያዘበት ዘመን የመጀመሪያው ንቅናቄ የባንክ ሠራተኞች ነበር። ያንንም ለንጽጽር ያቀረቡበት አግባብ ተገቢ እና ወቅታዊ ነውም ...

#ራህብን ለመግለጽ ሌላ "#ራበኝ" ከማለት ሌላ ቋንቋ ይኖረው ይሆን?

ምስል
  #ራህብን ለመግለጽ ሌላ " #ራበኝ " ከማለት ሌላ ቋንቋ ይኖረው ይሆን?   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"       እንዴት አደራችሁ ማህበረ ቅንነት? ደህና ናችሁ ወይ? https://www.youtube.com/watch?v=bR2GqRI2ZaU «ስራ ማቆም ትግል ሳይሆን ደሀ ላይ መፍረድ ነው»    # የአብይዝም መንግሥትስ?   የኢትዮ ሰላም ሚዲያ ባለቤት ልጅ ቴወድሮስ አስፋው ከሚያነሳቸው በርካታ ጉዳዮች ላይ #ሦስት ጉዳዮች እኔንም ሞገቱኝ እና ሃሳቤን ላጋራ ወደድኩኝ። ለመነሻነት ይህ ይሁን እንጂ ተያያዥ ጉዳዮችም ሊነሱ ይችላሉ።    የሆነ ሆኖ በአመዛኙ ከሁለት ዓመት ወዲህ #ቅይጥይጥ ክስተቶች ከመበራከታቸው የተነሳ በብዙ ክስተቶች ላይ ጥንቃቄያዊ ጉዞ ላይ ነው የባጀሁት። የኃይል አሰላለፋም ተለዋዋጭ ባህሬ መኖሩም። ስለሆነም የአቅም መግቦቱ እና ስኬቱ ለማን? የሚለውን በጥልቀት ማየት ያስፈልግ ስለነበር ተግታን መርሄ አደረኩኝ። ያ ጥንቃቄ ለእራሴ የውስጥ መንፈስ ቅዱስ መዳህኒት ሆኖልኛል።    ሰማይ ዝቅ ምድር ከፍ ቢል ቅንጣት አቅም የህወሃትን ተስፋ እንደገና በሚያለምልም አዟሪት ውስጥ መግባት በቁም ሬሳ የመሆን ያህል ይሰማኛል። ከመሼ እየታየ ያለው ሂደት ይህን እንደሚያመሳጥርም እዬታዘብኩ ነው። አቤቱ ህወሃት ለሚናፍቃቸው ወገኖቼ አቅም ብጣቂ አላዋጣም። ፈጽሞ። አቤቱ የሴራ ካፒቴኑ ህወሃት እና #አኞ ፖለቲከኛው ናፍቆኝ አያውቅም። ወደፊትም አይናፍቀኝም። ግድፈት፤ ሂደት፤ ወቅትና ዘመን ሊያስተምረው የሚችል ድርጅት አይደለም እና።    በሌላ በኩል የበዛው ቅንነቴ ስለ ወገኔ የምሰጠው ምስክርነት ሆነ ማገዶነት ጊዜ ራዲዮሎጂ ነውና የግለሰብ ሰብዕና ግንባታ...