ልጥፎች

የbbc የአማርኛው ዘገባ። «ከ30 ዓመታት በላይ ሕይወቱን ለኪነጥበብ የሰጠው ኩራባቸው ደነቀ በወዳጆቹ እንዴት ይታወሳል?»

ምስል
      የbbc የአማርኛው ዘገባ። «ከ 30 ዓመታት በላይ ሕይወቱን ለኪነጥበብ የሰጠው ኩራባቸው ደነቀ በወዳጆቹ እንዴት ይታወሳል ?» https://www.bbc.com/amharic/articles/c62830d5kymo «ከ 1980 ዎቹ መጀመርያ ጀምሮ በተለያዩ ቴአትር ቤቶች በትወና እና በአዘጋጅነት ሰርቷል። በአዲስ አበባ በሚገኙት አራቱ ቴአትር ቤቶች በትወና፣ በዝግጅት፣ አንዲሁም በአመራርነት እውቀቱን አካፍሏል። የሙያ ባልደረቦቹ ኩራባቸው ከማለት ይልቅ “ ኩራ ” እያሉ መጥራትን ይመርጣሉ። ሁሉም በአንድ ቃል ለሙያው ካለው ፍቅር ባሻገር “ ጨዋታ ወዳድ፣ ወግ አዋቂ ” መሆኑንም ይመሰክራሉ። “ መካሪ፣ መንገድ መሪ ” ሲሉ የሚገልጹትም አሉ። ለሦስት አስርታት በላይ በኢትዮጵያ የኪነጥበብ አድማስ ደምቆ የኖረው ኩራባቸው ደነቀ የተወለደው በ 1957 ዓ . ም . በሐረር ነበር። ኩራባቸው የመጀመርያ ደረጃ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በጭሮ ከተማ ነው የተከታተለው። በ 1979 ዓ . ም . ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በቴአትር ጥበባት የትምህርት ክፍል የተመረቀው ኩራባቸው፤ በ 1980 ዓ . ም . ጋሞ ጎፋ ክፍለ ሀገር አርባ ምንጭ በጀማሪ የቴአትር ኤክስፐርትነት ተመድቦ ሥራ ጀመረ። በአርባ ምንጭ ቆይታው ለኪነጥበብ ዝንባሌ ያላቸውን ወጣቶች በተለያየ መልኩ ይደግፍ እና ያበረታታ እንደነበር የሚነገርለት ኩራባቸውን በተመለከተ ደራሲ ፍቅረማርቆስ ደስታ የራሱን ገጠመኝ በማንሳት ". . . እንደ መኪና ሮዴታ ከነበርኩበት ግራ መጋባት መንጭቆ

#ነፍስ ይማር።

ምስል
  #ነፍስ ይማር።      ሟቹ አርቲስት ጌታቸው እጅጉ ዬአዲስዬ የልደቴ ልጅ ነበር። ከ15 ዓመት በጥበብ ውስጥ ቆይቷል፤ ፊልም ቤት በትርጉም ሥራ አተኩሮ ይሠራ ነበር። ከ60 በላይ በፊልም ሥራ ተግቶ ሰርቷል። በሃይማኖቱም ጽኑ እንደሆነ ተገልፆዋል።   በአዲስ አድማስ በአምደኝነት ሠርቷል። ከ4000ሺህ በላይ መፃህፍት በቤቱ እንደሚገኝ የጊዜ ዘገባ ይገልጸዋል። 14 ሺ መፃህፍት ማንበቡ ተገልፆል። በበጎ ተግባርም ይሳተፍ እንደነበር ዘገባው ገልፆል። ዘገባው የጊዜ ሚዲያ ነው። ከሚዲያ ላይ እንደተረዳሁትም ግልጽ እና ቀጥተኛ ሰብዕና እንደነበረውም ተረድቻለሁኝ።   ለቤተሰቡ - ለሚወዱት - ለሚከተሉት ሁሉ እግዚአብሄር ጽናቱን ይስጣቸው። አሜን።   https://www.youtube.com/watch?v=hqFV66PIlco&t=601s ልብ ይሰብራል 60 ፊልም ሰርቶ የሚበላውበ አጥቶ በችግር ምክንያት ሞተ(‎@gizemedia1974)Ethiopia|Elisa Degenet|25 August 2024 26.8.2024

ላምን #ስላልፈቀድኩ ብቻ ዘገዬሁ። ኢትዮጵያ ያጣችው #ዓውራ ጥበበኛ።

ምስል
  ላምን #ስላልፈቀድኩ ብቻ ዘገዬሁ። ኢትዮጵያ ያጣችው #ዓውራ ጥበበኛ።       በፍፁም ማመን አቃተኝ። አልፎ አልፎ እንደሚወጡ አሳሳች መረጃወች ነበር የቆጠርኩት። የዛሬ ሁለት ዓመት በእሱ ዙሪያ አንድ መጣጥፍ ጽፌ ነበር። ተውኔትም፤ ቲያትርም፤ ጥበብም ይባል ውስጡ #የውስጥ ነበር። #ዋርካ #የጥበብ #ሰው ።    አወን ዋርካ የጥበብ ሰው። ተውኔት መሆኑን እስክትረሱት ድረስ ገፀ ባህሪያትን ተላብሶ ሲጫወት #ያስደምማል ። #ይመስጣል ። #የተሰጠው #የጥበብ #ባለፀጋ ። ለዘርፋ ሽልማትም ነበር። እንዲህ እንደ ዋዛ መራራ ስንብት።    የሚናፈቅ፤ የሚወደድ፤ የማይጠገብ ብዙ የሚዲያ ሰው ያልነበረ፦ መታዬትን ብዙ የማይቫ ቁጥብ። ግን በጥሪው ልክ ሆኖ በሥጋ የተለዬን። #የማይደገም ፦ #የማይሰለስ #ልዩ ፍፁም ልዩ ተዋናይ።    እኔን ጨምሮ ለሚያከብሩት፤ ለሚሳሱለት ቤተሰቦቹ ሁሉ መጽናናትን ልመኝ። አርቲስት ኩራ ቸኮለ። በጣም ቸኮለ። ኢትዮጵያ በአንድ ሳምንት ሁለት ጥበበኞችን አጣች። ወጣት እና ጎልማሳ የጥበብ ልጆቿን። ያሳዝናል።    https://www.youtube.com/watch?v=FymiluMUvdQ የአርቲስቱ ሞት እና አሳዛኙ የምርመራ ውጤት | ሀገሬ ቴቪ     እግዚአብሄር ይስጥልኝ። ሥርጉትሻ 27/08/2024    

Amhara Movement: Advocacy & Diplomacy

ምስል

ህፃን ሔቨን የመፍትሄ ንቅናቄ #ውክል #ዓርማ ናት። መደፈር፤ ጥቃት፤ ፍትህ፤ ጥበቃ፤ Vergewaltigen, Ang...

ምስል

ህፃን ሔቨን የመፍትሄ ንቅናቄ #ውክል #ዓርማ ናት ልክ እንደ አና።

ምስል
  ህፃን ሔቨን የመፍትሄ ንቅናቄ #ውክል #ዓርማ ናት ልክ እንደ አና።   "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል ሰው ግን አያስተውለውም።"     እንዴት አደራችሁ ውድ ቤተሰቦቼ? ደህና ናችሁ ወይ?    የአንድ ሳምንት የህፃን ፌቨን ንቅናቄን ትርጉም ባለው ተቋማዊ የተግባር መስክ መቋጫ ቢያገኝ ምኞቴ ነው። ንቅናቄው #ግሎባል ነበር። የብዙ ወገኖችን የህሊና በር አንኳኩቷል። ካለ ምንም የደንበር ልዩነት አብዛህኛው ኢትዮጵዊው #በርህርህና ድምፁን አሰምቷል። በጎውን - አወንታዊውን - የተጋድሎ ምዕራፋን እኔ ሳስተውለው #ክስተት የመሆን አቅምም አግኝቷል ብዬ አስባለሁኝ።    በአሉታዊ የተነሱ ኃሳቦችን አልፎ አልፎ አዳምጫለሁኝ። አቅም፤ ጊዜ መንፈስ ሊጠፋ የሚገባው የሚገጥሙንን ፈተናወች ለመፍትሄ አቅርቦታቸውን በመጠቀም ብቻ ሊሆን ይገባል። ለአንዱ ግን መልስ ልሰጥ ወደድኩኝ።    ይህም ለምን አሁን ለሚለው ጥያቄ። #እግዚአብሄር ሥራውን የሚሠራበት ጊዜ ስላለው ነው። ፈጣሪ #የፈቀደው ሰዓት እና የወደደው ጊዜ ይህ ስለሆነ ነው። ዕድሉን መጠቀም ደግም የሩህሩኃን ተግባር ነው።   እርግጥ ነው የተለያዩ #አሉታዊ ሃሳቦች ተነስተዋል። በተለይ አንድነቱን፦ ህብረቱን የተመለከቱ ማዋጋቱን አጋግለውታል። ከማይነካካ አመክንዮ ጋር እያነካኩ ላባቸው ጠብ እስኪል ሲናገሩ ሰምቻለሁኝ። ይህ ለእኛ አይጠቅመንም።    እኛ #በሰዋዊ ስሌት ለትውልዱ ሊጠቅሙ በሚችሉ የርህርህና፤ የአይዟችሁ ሰብዕና፦ እና የአጽናኝ መንፈሶች ላይ ብቻ ልንተጋ ይገባል። በጎ ስለማያስቡ ግለሰቦች ዕውቅና ሰጥቶ ጊዜ ማቃጠል አያስፈልግም።    #ጉዳዩ የደነደነ ፈርዖናዊ ልብ ያለውን መንፈስን ገርቶ ለመልካምነት ካተነሳሳም መልካም ዕድል ነው። ማቆላመጥ፤ ማባበል ያለብን የችግሩን ጥልቀ