ልጥፎች

#ዝምታ ቢከበር ምንኛ በታደልን ነበር በኢትዮጵያ የፖለቲካ አቅም እና አቋም።

ምስል
      #ዝምታ ቢከበር ምንኛ በታደልን ነበር፦ በኢትዮጵያ የፖለቲካ አቅም እና አቋም።   "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውለውም።"   #ጠብታ ።    ለጭካኔ ሴራ ፖለቲከኛው ለአቦይ ስብኃት ነጋ የአልማዝ ጉንጉን አሰርቶ በግል ማክበር መብት ነው። የምስጋና ሴሪሞኔውን አደራጅቶ መምራትም የማይሸሹት ሞጋች ህሊና ከፈቀደ መፈጸም ይቻላል። በሌላ በኩል የህወሃት ዶግማ በመንፈሱ የታተመ ዜጋ ለአቤቱ ህወሃት የወርቅ ሃውልት በይፋ ማሰራትም ሙሉ መብት አለው። ጭካኔን እንደምናወግዘው ሁሉ ጭካኔ ናፈቀኝ ማለትም መብት ነው። በእኔ ላይ የጭካኔን አውራ አምጥቶ ለመጫን መሞከር ግን አይፈቀድም። ይህ ዱላም፤ ዝምተኛ የሆነ ስውር ጭቆና በጫናም ነው። ግፍም ነው። ስለሆነም ………   #መቃብር አይናፍቀኝም።   እኔ አዎን እኔ #ጉድጓድ አይናፍቀኝም። #ገደል አይናፍቀኝም። ቤተ - መቃብር አይናፍቀኝም። ሳጥናኤላዊ #ጭካኔ አይናፍቀኝም። #የጥላቻ ማምረቻ ቱቦ አይናፍቀኝም። የዞግ ፖለቲካ ፈላስፋ ሽው አይለኝም። የገዳይ የተሃድሶ ኦፕሬሽን #ካፒቴን አይናፍቀኝም። #የክፋ ሃሳብ አፍላቂ፥ አናጺ እና የጸረ ሰው ሹፌር ትዝ አይለኝም። የሴራ ቸረቸራ ቧንቧ ትዝ አይለኝም። የውድመት መሐንዲስ ትዝ አይለኝም። #ሬሳም አይናፍቀኝም። የጸረ ሰላም ኒዩክለስ አልፈልግም። የጭካኔ ቅሪት አካል የኑዛዜ የምክር አገልግሎትም አይናፍቀኝም። መቼውንም።   #በድል ይረሳል ወይንስ ይለመዳል?    ልመዱ ብቻ ሳይሆን በትንሳኤውም ሳቁለት¡ ማለፊያ¡ ወሸኔ¡ በሉት እየተባልን ነው። ይህን ርዕስ በዘመነ ህወሃት ደጋግሜ ጽፌበታለሁኝ። የደጉ ዘሃበሻ እና የደጉ ሳተናው ቋሚ አምደኛ በነ...

#ማወቅ አዳነ ነው ለማወቅ አወንታዊ

  #ማወቅ አዳነ ነው ለማወቅ አወንታዊ ዕውቅና መስጠት ከተፈቀደ። የእራስ እንደራሴነት እራስን ሳያውቁ ከሆነ እራስን ማውደም ይሆናል። የኢትዮጵያ ፖለቲካ አዚሙ ይህ ነው። የታሪክ ተመራማሪው የኔታ ኃብታሙ ተገኜ በርዮት ሚዲያ። እግዚአብሔር ይስጥልኝ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 20/06/2021 ማወቅ አወንታዊ ዕውቅና ከተሰጠው አዳነ ነው። ልስልስ ያለ የሰላም ጊዜ ይሁንላችሁ። አሜን።

በጥላቻ ውስጥ #መዳን የለም።

 በጥላቻ ውስጥ #መዳን የለም። በጥላቻ ውስጥ ከቅንጣት እስከ ገዘፈው ችግር ዘላቂ #መፍትሄ ማመንጨት ይሁን ወደ ህዝብ ጠቀም የተገኜውን የመፍትሄ አመክንዮ ወደ ድርጊት ማሸጋገር አይቻልም። በምሰማቸው ውይይቶች ሁሉ #ዘለፋ እና #ጥላቻ ፤ እንዲሁም #ማቃለል ፤ በተጨማሪም ማጣጣል የተካነበት ነው። ይህ #አትራፊ ጎዳና አይደለም። ሥርጉትሻ 2025/06/20

ባለ #ትንቢቱ #እጬጌ! አባ #እዮብ ጥናት መቀነቱን ቅድስት ድንግል ማርያም ትስጠወት። አሜን።

  ባለ #ትንቢቱ #እጬጌ ! አባ #እዮብ ጥናት መቀነቱን ቅድስት ድንግል ማርያም ትስጠወት። አሜን። "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   አባት ሆይ! #የፋመው ተጋድሎ የሚጀምረው አሁን ነው። የማቱሳላን ዕድሜ አጋይስትዓለሙ ሥላሴ ይስጠወት። አሜን። ስንቱን #መከራ ተሸከሙ?    ስንቱንስ ፈተና በጥበብ #ታገሡ ? ሰው ምን አቅም አለው ይህንን #ምርቅ የፈተና ሂደት የማንበብ ሆነስ #የመተርጎም ?    ከባድ ነው መጪው የአገልግሎት ዘመን። ይመስለኛል። እንደ ሰው ሳስበው። ጥንካሬወ፣ ብርታትወ፣ ትዕግሥተወት #ብልህነተወትንስ ማን አቅም አለው ለመተርጎም??? አይደለም ለመተርጎም የተዋህዶ ልጆች ከሊቅ እስከ ደቂቅ #ገብቶናልን ??? አይመስለኝም። የፖለቲካ ሸቀጥ በልጦናል። የዞግ ደንበር ገዝቶናል። ያማ ባይሆን ለአኃቲ ሃይማኖት #ቅጥልጥልስ ፤ #ግንጥልጥልልስ ምን ያስፈልጋት ነበር። ዕምነቱ ካለ፤ ጸጋው ከታወቀበት። ቅብዓ ከእዮር እንጂ ከሰው አይደለም።   ለሃይማኖታችን ጥንካሬ የሚጠቅመው በማስተዋል #በንፁህ ልቦና በአኃቲ መንፈስ መጓዝ በነበረ። #ቅንነት ። ለእመ ቅኒት ለቅድስት ተዋህዶ ሃይሞኖት ጽናት ተምሳሌ የሆኑ እጬጌን የመቀበል እንኳን አቅሙ እየታዬ ነው። አይደለም በ፯ ዓመታት፤ ለ፯ ሰከንድ የቅዱስነታቸው ያህል በብልህነት ፈተና መሸከም ሆነ ትብትቡን የአሳር አሳር ተቋቁሞ መቀጠል ከባድ ነው።    አባ እዮብ ግን ችለውበታል። ከጎናቸው መቆም የሚገባቸው ፈተና አምራች ሆኖ ከማየት በላይ ምን የሚገርም የታሪክ ድርሳን ይኖር ይሆን? በተለይ የትግራይ ብጹዓን አበው። ዝም የምለው ያላቸውን አውቃለሁ። ግን ያላቸው ለትውልድ መጠኑን #መከለል ? ፈጣሪ ደንበርም ወሰንም ዞግም የለውም። ዕድሉን...

ኢትዮጵያ #በልዕልና ቀደምትነት የተሰራች አገር ናት። ኢትዮጵያ በፋንታዚ ክምር አዲስ #እምትሰራ አገር አይደለችም።

ምስል
  ኢትዮጵያ #በልዕልና ቀደምትነት የተሰራች አገር ናት። ኢትዮጵያ በፋንታዚ ክምር አዲስ #እምትሰራ አገር አይደለችም።   "የቤትህ ቅናት በልኝ።"       1) "ኢትዮጵያ #እንደገና እየተሠራች ያለች አገር ናት።" ኢንጂነር አይሻ መሃመድ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሚኒስተር። #ጸያፍ አገላለጽ። ኢኒጂነር አይሻ መሃመድን ሞግቻቸው አላውቅም። እንዲያውም ከመከላከያ ሚር ሲነሱ ዲሞሽን ነው ብየ ለሳቸው ወግኜ የአብይዝምን ውሳኔ ሞግቻለሁኝ። ምክንያቴ ኢንጂነር አይሻ የወቅቱ የመከላከያ ሚር በነበሩ ጊዜ በኢትዮጵያዊነት ላይ ያላቸው ውስጥነት በንግግራቸው ትልልፍ ስላልነበረበት ነው የተለየ አክብሮት የነበረኝም። ዩንቨርሷል ኢትዮጵያን ሲያነሱ ገፃቸው ፈክቶ እመለከት ስለነበር ከማክበር ውጪ ሙግት በእኔ ብዕር ነክቷቸው አያውቅም ነበር።    በሌላ በኩል ሠራዊት ነክ ጉዳዮችን እራሱን የቻለ ሙያ፤ ተመክሮ ስለሚጠይቅ ተዳፍሬው የማለውቅ ዘርፍ መከላከያ እና የኢኮኖሚ ጉዳዮችን ነው። የሆነ ሆኖ ከፋና ቴሌቪዥን ጋር የመከላከያ ሚኒስተሯ ኢንጂነር አይሻ ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳመጥኩኝ። ቢቢሲ የአማርኛው ዘርፍ በእሳቸው ዙሪያ ያወጣውን ተከታታይ ዘገባም አንብቤያለሁኝ።   ስለሆነም ለስሜቴ ቅርብ የሆነውን ሃሳብ ብቻ ላነሳ ፈቅጃለሁኝ። #በልቅና #በጥሞና ተስርታ ባደረች አገር ተፈጥሮ፤ አድጎ፤ ለቁም ነገር ተበቅቶ " ኢትዮጵያእንደ #ገና #እየተሠራች ያለች አገር" ብሎ መናገር የዘመናት የኢትዮጵያ ታሪክን #መዳፈርም ነው። በአንድ ወቅት ቤተ - ኢሳት በአክቲቢስት ታማኝ በየነ የተመራ ቡድን ሲዊዝ ስብሰባ በመጣ ጊዜ ይህን መሰል አገላለጽ አድምጬ ነበር።    ከቡድኑ ውስጥ ጋዜጠኛ መታሰቢያ ቀጸላ ዛሬ ...