ልጥፎች

ከ2026 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የብልጽግና የስንዴ #ነዷዊነት የጉዞ ቁመና በሥርጉትሻ ዕይታ።

ምስል
  የብልጽግና የስንዴ #ነዷዊነት የጉዞ ቁመና በሥርጉትሻ ዕይታ።   መጽሐፈ ሩት ምዕራፍ ፪ ቁጥር ፯ …    «እርስዋም። ከአጫጆቹ በኋላ በነዶው መካከል እንድቃርምና እንድለቅም፥ እባክህ፥ ፍቀድልኝ አለች፤ መጣችም፥ ከማለዳም ጀምራ እስከ አሁን ድረስ ቆይታለች፤ በቤትም ጥቂት ጊዜ እንኳ አላረፈችም አለው»        #ምዕራፍ ፲፰   ይህ የፖለቲካ ፓርቲ የአደረጃጀት፤ የመርህ አፈፃጸም ጉዳይ #የተማርኩትም ፤ #የሠራሁበትም ስለሆነ ትዝብቴን እንሆ … የዕለቱ አትኩሮቴ፣ #በምርጫ ምልክቱ እና #በማንፌስቶ ዙሪያ ይሆናል። #ምንጭ ፎቶውን ጨምሮ ፋና ቴሌቪዥን እና የብልጽግና ፖለቲካል ፓርቲ ፌስቡክ ፔጅ ላይ ነው የወሰድኩት። ከሥር ተያይዟል።   • #የምርጫ ምልክቱ እና ማንፌስቶውን ማንስ ያጸድቀዋል?    አጽዳቂው የአባላት ጠቅላላ ጉባኤ ብቻ ነው።    1) ድርጅት ምንድን ነው? በቀላል አገላለጽ ሁለት እና ከዚያ በላይ ሰወች፤ ተቋማትም ሊሆኑ ይችላሉ፤ በፆታቸው፤ በዕድሜያቸው፤ በሙያቸው፤ በሃይማኖታቸው፤ በኢኮኖሚ አቅማቸው፤ በራዕያቸው ዙሪያ በሚያስማማቸው፤ በሚያግባባቸው ዓላማ እና ግብ፤ ወይንም ፍላጎት የሚፈጥሩት አቅምን፤ ኃይልን እና ጉልበትን የሚያማክሉበት ሥልጡን የሆነ የተቋም፤ የሥርዓት ለመመሥረት የመሰባሰቢያ ስልት ነው። መንግሥት እራሱ ድርጅት ነው።    2) የፖለቲካ ድርጅትስ?   የፖለቲካ ድርጅት የዓላማ እና የግብ ጥምረት ሳይሆን፤ ውህደትን የሚያበስር ተቋም ነው።   3) አንድ የፖለቲካ ድርጅት አካላት አሉትን።   አለው። የመጨረሻው የሥልጣን አካል ብሄራዊ ጉባኤ ሲሆን፤ መሰረቱ አስኳል ከሥር...

#አይበገሬው ወጣት Yonas Mequanint በጥሪው ውስጥ። የትውልዱ ነገር ይገደኛል - እኔን። ይመለከተኛልም - እኔኑ።

ምስል
  #አይበገሬው ወጣት በጥሪው ውስጥ። የትውልዱ ነገር ይገደኛል - እኔን። ይመለከተኛልም - እኔኑ። "አድርገህልኛል እና አመሰግንሃለሁኝ።"   እንዴት ናችሁ የእኔወቹ???    ያልተጠበቀ፤ የማይጠበቅ፤ የማይታሰብ፤ ግን ፈጣሪ አስቦ የጀመረው የዕውነተኛ ታሪክ ፍሰት። ኪኖ ይመስላል። ነጮቹ ቢያገኙት ፊልም ይሠሩታል። በተመስጦ፤ በተደሞ፤ በአትኩሮት፤ #በፍጹም ትዕግስት የተከታተልኩት ዕውነተኛ ታሪክ። ጓድ አበበ በዳዳ የሚባል አለቃ ነበረኝ። ከእለታት በአንዱ ቀን ጋሼ አቤ ከጎንደር ወደ ደቡብ ኦሞ ክፍለ አገር ፩ኛ የኢሠፓ ጸሐፊነት ተዛወረ።    በሌላኛው ቀን ደግሞ ለማዕከላዊ ኮሜቴ ስብሰባ ጸሐፊወች ፬ኪሎ ተገናኙ። ወደ ፭ የሚሆኑ ፩ኛ ፀሐፊወች ያውቁኙ ነበር በአካል። በኮርሰኝነት ወይንም በሥራ። ሞገደኛ ነበርኩኝ። ደፋር ነበርኩኝ። ትጉህ ነበርኩኝ ዲስፕሊንድ ነበርኩ። ከቤት ወደ ሥራ፤ ከሥራ ወደቤት። በቃ። እና የመሪወቼ #አጀንዳ እኔ ሆንኩኝ። የጋራ ሊንክ።   ጋሼ አቤ እረፍት ወጥተው ቡና በጣም ይወዳሉ ሁሎችም፤ ቡና እየጠጣ ደብዳቤ እዛው ላይ ሆኖ ፃፈልኝ። ስዳር ጎንደር ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጅበኝ እና ሌሎችንም ጉዳዮች አክሎ ፃፈልኝ። ከፃፈልኝ ውስጥ ከብረት ቁርጥራጭ የተሠራ ጥንካሬሽ …… ይል ነበር። በልጅ ዮናስ ያዬሁት ጥንካሬ፤ ብርታት፤ #የውሳኔ አቅም፤ #ሁለገብነት ጋሼ አቤ ለእኔ የሰጠውን ከብረት ቁርጥራጭ የተሠራሽ ያለውን ለዮኒ ለመስጠት ወሰንኩኝ።    አወን ልጅ ዮናስ መኳንንት ከብረት #ቁርጥራጭ የተሠራ ማንነትን የገነባ #ጀግና ልጅ ነው። "ከተሠራንበት ርቀናል፤ ያልሞተ ሰው ሃሳብ ይቀይራል፤ ከጎርጎራ ውጪ ለ?የት አለ ምድር ለእኔ? የምንጀምረውን እንጂ የምንጨርስበ...

እስትንፋስ ያለውን

 ሁለንም የተፈጥሮ ስጦታ #እስትንፋስ ያለውን እና አመክኖዊው ጸጋወችን ማስደሰት ባይቻልም፤ ሁሉንም #ቁርጥራጭ ማስከፋት መልካም አይደለም። ለምሳሌ ማጽናናትን፤ ትህትናን ወዘተ …… የሆነ ሆኖ ቢያንስ #ከሰውነት እና #ከተፈጥሯዊነት ፤ ከዕውነት እና መርኽ ጋር መቆም ዋጋ የሚያስከፍል ቢሆንም የተሻለ ጎዳና ይመስለኛል። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። ሥርጉትሻ 14/02/2026

EBS መሥራቹን አጣ፨

ምስል
  የምንኖረው #ለጤዛዊ ጊዜ ለአፍታ ነው።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       ይቺ ዓለም እንዲህም፤ እንዲያም ናት። ስትሞቅ /// ስትቀዘቅዝ፤ ለብ ስትል፤ /// ፍላት ሲያሰኛም እንዲህም እንዲያ ሲያሰኛት ትቆይ እና መራራ ስንብትን ጎምዛዛ ጠምቃ እንዲህ #ዕንባ ታራጫለች። ለብሰን - ስንታይ፤ ቁመን - ስንታይ፤ ስንሞግት ///ስንሞገት፤ ስንስቅ // ሲከፋን ቋሚ ጊዜ የተሰጠን ይመስለናል። ግን የአፍታወች ነን።    ጸጥ እረጭ ካለው ቅዝቃዜ ውስጥ ከተማችን ስለመሆኑ፤ ትዳር ጎጇችን ስለመሆኑ በህይወት እያለን ትዝ የማይለን ብዙወቻችን ነን። ጥልቀት ያለው መራራ ስንብት የፍጥረታት ሁሉ ተመስጥሮ አብሮን የተፈጠረ ስለመሆኑ እንዘናጋለን። ለዚህም ነው ሞት ሁልጊዜ አዲስ የሚባለው።   የሚዲያ ሰብዕና በፈተና #የታጠረ ነው። የመጨረሻው የፈተና ተጋድሎ እንዲህም፤ በዚህም ሁኔታ ይጠናቀቃል። የሚዲያ ተግባር በብክነት የተሞላ ነው። የሚዲያ ሰብዕና የመጨረሻው እረፍት በዘለቄታ እንዲህ ይጠናቀቃል። እንዲህም ይደመደማል። ይደመደማልም። የሠራ ሰብዕና፤ የተጋ ሰብዕና፤ በአዲስ ጎዳና፤ እሸት ሃሳብን አዝምሮ፤ አብስሎ ያሰበለ ሊቀ - ትጉኃን #አሻራው የተሟላ ስለሚሆን፤ ሞተ ከሚባል፤ ከድካሙ #አረፈ የሚለው ትርጉም የሚሻል ይመስለኛል። ሁላችንም ከጽንሰታችን ጀምሮ ተጓዦች ነን። እንከታተላለን።    ትልቅ ሰው በስጋ ቢለይም ሁልጊዜ ተግባሩ፤ ትጋቱ በቋሚነት ይቀጥላል። በብዙ ሁኔታ በዘርፋ በርካታ ባለሙያወችን በማብቀል እናም ተተኪ በመፍጠር የትውልድ በሆነ #ቀና ዕሳቤ ለትውልድ የሚሆን፤ የሚበረክት ተግባርን ፈጽሞ፤ በታታሪነት ተግቶ፤ አስብሎ የአረፈ ሰብዕና በሚሊዮኖች ልበ - ህሊና ው...

#ሁለት ቤተ - አብኖች #ኢህአፓን ወክለው የ2018ቱን ዓም ምርጫ እንደምወዳደሩ አስታወቁ።

  #ሁለት ቤተ - አብኖች #ኢህአፓን ወክለው የ2018ቱን ዓም ምርጫ እንደምወዳደሩ አስታወቁ።   የዘገባው ምንጭ #ሪፖርተር ነው።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። የፓርላማ አባሉ ዶር አበባው ደስአለው እና ዶር. ይህዓለም ታምሩ (የሚያምር ሥም።) ሁለቱም ቤተ - አብኖች የነበሩ ሲሆን አሁን ኢህአፓን ወክለው በ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ የምርጫ ሥርዓት ውስጥ #ሊወዳደሩ እንደወሰኑ ዘገባው ያመለክታል። በተጨማሪም ዶር. ይህዓለም ታምሩ የአዲስ አበባ የአብን ጽ/ቤት ኃላፊ እንደነበሩ መረጃው ይጠቁማል።   በውነቱ የእኔ ሁሉም ሚዲያ ጸጋዬ ራዲዮን ጨምሮ ዘገባ አይሠራበትም። ስለሆነም የምርጫ ዘገባም፤ በምርጫ ዙሪያም ያሉ ንቅናቄወችን በጥሞና መከታተሉ ይበጃል። ባለፈውም የፈጸምኩት በዝምታ ነው። አንዳንድ ኮሚክ ሁነት ሲገጥም ብቻ ነበር ሐተታ እጽፍ የነበረው። የተወዳደሩክት #ለማሸነፍ አልነበረም ልሸነፍ ነው የሚል ቧልት አዳመጥኩና ፃፍኩኝ። ሌላም "የብልጽግና አባል #አይደለሁም ግን ወክዬ እወዳደራለሁ" ያሉም ተወዳዳሪ እንዲሁ ገርሞኝ ጽፌ ነበር።    እንጂ በምርጫ ዙሪያ ብዙም መሳተፍ አልሻም። የሆነ ሆኖ በኢህአፓ ላይ ያለው የሚዲያ ጫና ገርሞኝ ስለነበር፤ አንጋፋ መሪወቹንም የኢህአፓ በአካል ስለማውቃቸው በህይወት እያሉ ወጣት ተተኪወቻቸው በፓርላማ የመወዳደር ዕድላቸውን እንዳያፈሱ ትናንት ዘለግ አድርጌ መፃፌ ይታወቃል።    በተጨማሪም "ለህዝቤ የፈየድኩት ነገር ስለለ መጪውን ምርጫ አልሳተፍም" ያሉትን ዶር ደስአለኝ ጫኔ ከምርጫ እራሳቸውን ማግለላቸውን አክብሬ ምክንያታቸው ስላላሳመነኝ ትናንት በዚህ ዙሪያ ስለፃፍኩኝ፤ የጓዶቻቸው ለመሳተፍ #መፍቀድ ተያያዥ ስለሆነ ነው ለመዘገብ የወደድኩት...