ልጥፎች

ይህ ቤተ - ሰለሞን #የድውያን #ማገገሚያ #ጣቢያ የለውም።

ምስል
  ይህ ቤተ - ሰለሞን #የድውያን #ማገገሚያ #ጣቢያ የለውም።   "ከንቱ የከንቱ ከንቱ ሁሉም ነገር ከንቱ።"     በውነቱ ለዛሬ የሚሆነኝን ፈፅሜ ነበር። ነገር ግን መዳኛ የሌላቸው ነፍሳት እዬመጡ ቤቱን ያውኩታል። እዚህ እኮ ጎንድ ተክለኃይማኖት #መጠመቂያም የለም ወፈፍ ለሚያደርጋቸው። የአማኑኤል #ማገገሚያ ጣቢያ የለም።    ቢያውቁት ቢረዱት የሃሳብ አቅም ያለው በትህትና፤ በአክብሮት በጥሞና የሚያነብበት፤ የሚያዳምጥበት፤ ሃሳቡን አቅርቦ የሚሞግትበት ነው። የውቂ ደብልቂ፤ የቅጽበተኞች መጋለቢያ አይደለም ቤቱ። ይህን ያሰኜው ሌላ ቦታ መፈለግ ነው ያለበት። ኢትዮጵያን #የተፀዬፈ ሰብዕና ይህ ቤት ልኩ አይደለም።    ከዘለለው ጋር የማልዘል፤ ከጎረፈው ጋር የማልጎርፍ መሆኔ ይታወቃል። #መልካምነት ፤ #ቸርነት ሲነሱ ያንገፈግፋቸዋል። ኢትዮጵያ ስትነሳ ደማቸው #ይንተከተካል ። ጎርፍ አምጥቶ ደለል የሠረባት ሁሉ እዬመጣ ልቤን ያወልቃል። እንዲያውም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማም እንደ ጠላት ያዩታል። #ይድከሙ - አይችሉም። #ይኳትኑ - #ነኩተው ይቀራሉ።   የአረብ ስፕሪንግ ተነሳ ኢንፖርት ኤክስፖርት ህግ ይግዛው፤ ፓኪሳትን ቤተ -:መንግሥት ንቅናቄው መጣ እኛም እንቀላቀለው የተነሱበትን የማያውቁ፦ ሰው በገነባው አቅም ተንጠላጥለው እንደ #ፌንጣ እዬዘለሉ ባጉም ባጉም። "ከበሮ በሰው እጅ" ሆኖ የፖለቲካ ድርጅቱም ተመሰረተ ጨዋታው ፈረሰ ቅሉ ተሰበረ አሟራው በረረ ሆኖ አዬን። ስንት አቅም የፈሰሰበት።    አቅልም አደብም ጠፍቶ በምኞት ሰረገላ የፋንታዚ ልዑል ተሁኖ መከራን ማበራከት። አዬ የአማራ ህዝብ ቻል የተባለው ገመና እኮ ወዘተረፈ ነው። ኩፍትርትር ያለች ብጣቂ ወረቀት ልሳንም አንደበትም ሁና ታላቁን የአማ

ጥሞና

  #ጥሞና እራስን #ለብቃት #ልቅና የሚያበቃ ነው። በኢትዮጵያ የ60 ዓመት የፖለቲካ ሂደት ግን ዕውቅና ያልተሰጠው ክስተት ነው። ሥርጉ28/06/024

#ቅጽበታዊነት #የውድመት #ኢንደስትሪ

 ቅጽበታዊ ሰብዕና የሌላቸው ሰወች ከቅጽበታውያን ፖለቲከኞች ጋር ሲሰሩ #ቅጽበታዊ ይሆናሉ። ድዌው ይሸጋገራል። ቅጽበታዊነት ለእኔ በሽታ ነው። የሥራ አዬሩም ቅጽበታዊ ይሆናል። ይህ ደግሞ #ለተረጋጋ የትውልድ ግንባታ #የህሊና #ኪንታሮት ነው። ለአደጋም ያጋልጣል። በሰብዕናቸው ቅጽበታዊ የሆኑ ፖለቲከኞች ፈቅደው ከፖለቲካው ዞር ቢሉ ይመከራል። በሁሉም ዘርፍ #ቅጽበታዊነት #የውድመት #ኢንደስትሪ ነውና። በግል ህይወትም መኖርን ያባክናል። #ማሰብን #ይበትናል ። #ፍልስፍናን ፦ #ሳይንስን ይጠናወታል። ቅጽበታዊነት የሥልጣኔ ገዳይ #ባይረስም ነው። ሥርጉትሻ28/06/024

#ነገን መሥራት ይቻላል

  ለትውልድ እያንዳንዱ ሰከንድ ዕሴት አለው። #ዕሴቱ እንዳይባክን ትውልድ #ጊዜውን ማደራጀት ይኖርበታል። ጊዜ ማደራጀት ከተቻለ ሕይወትን በዕቅድ መምራት ይቻላል። ሕይወትን በእቅድ መምራት ከተቻለ በዛሬ ውስጥ #ነገን መሥራት ይቻላል። በነገ #መሠራት ውስጥም ከነገ ወዲያ #መሠረቱ ይጣላል። ዬትውልድ ተከታታይነት ቁምነገር የሚገነባው በራስ ውስጥ በሚሰራ የተደራጀ ተግባር ነው። በራስ ውስጥ የተደራጀ ተግባር ከኖረ ራስን #ለማድመጥ በቂ ጊዜ ይኖራል። ያ በቂ ጊዜ ሩቅ ይታሰብበታል። ታስቦም ይተገበርበታል። ያ ተግባር ሲዋህድ የማህበረሰብ ይሆናል። ሁሉም እራሱን #ያጥና እያልኩ ነው። ትውልድ የቅልቅሎሽ ድራማ አይደለምና። ሥርጉትሻ28/06/024

#ማዬት እና #መመልከት

  #ማዬት እና #መመልከት እንደ አፈፃፀማቸው ስኬታቸው ይለያያል። ከውስጥ ማዬት እና ከላይ ማዬት አንድ አይደሉም። ማዬት ማስተዋልን ሲያጎናፀፍ #አትኩሮት ይወለዳል። አትኩሮት ጥሞናን ሲጠጣ ዬፍልስፍና ጎዳና ይጠርጋል። ጥናቱ ወደ ፍትኃዊነት ዝንባሌ ያመጣል። መመልከት ከማዬት ጋር በአንድ #ትርጉም ይካተታሉ። መመልከቱ ግልብም ጥልቅም ከሆነ ግብረ ምላሹ በመልከት ውስጥ እንኳን ይለያያል። መመልከትም ማዬትም የዓይን ብቻ አይደሉም። የህሊናም ናቸው። የህሊናም ብቻ አይደሉም #የ12 አካላት ናቸው። ሳዬው ልቤ ተሰነጠቀ፤ ነዘረኝ፤ መላ ሰውነቴን ወረረኝ የሚባለውም ለዚህ ነው። በምንሳተፍባቸው መስኮች ሁሉ መላ አካላት ዓይነ ህሊና አላቸው እያልኩ ነው። ለሰጠው። ይህ ሁሉ #ተስቶ ነው መግለብለቡም ፦ግንፍል ግንፍሉም፦ አፍሶ መልቀም፤ ለቅሞ ማፍሰስ የሆነው። ሥርጉትሻ2024/06/28

«በአማራ ክልል በዚህ ሳምንት ከ27 በላይ የሚሆኑ ‘ሰላማዊ ሰዎች’ “በመንግሥት ኃይሎች” መገደላቸው ተነገረ» bbc

ምስል
  ·        https://www.bbc.com/amharic/articles/cley9eeyxv0o ከ 6 ሰአት በፊት ·     «በአማራ ክልል በዚህ ሳምንት ከ 27 በላይ የሚሆኑ ‘ ሰላማዊ ሰዎች ’ “ በመንግሥት ኃይሎች ” መገደላቸው ተነገረ»     «በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ እና ሰሜን ጎጃም ዞኖች በቀናት ልዩነት “ የመንግሥት ኃይሎች ” ቤት ለቤትና መንገድ ላይ ‘ ሰላማዊ ሰዎችን ’ መግደላቸውን የዐይን እማኞችና ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል። ጥቃቶቹ ሰኞ ሰኔ 17 እና ረቡዕ ሰኔ 19 ፤ 2016 ዓ / ም መፈጸማቸው የተነገረ ሲሆን፤ በጥቃቶቹም ከ 27 በላይ ንጹሃን ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል። በሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ከደብረ ሲና ከተማ ወጣ ብላ በምትገኝ ሾላ ሜዳ በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ ሰኔ 19 በመንግሥት ኃይሎች ደርሷል በተባለ ጥቃት ቢያንስ 15 ሰዎች መገደላቸውን እና አራት የሚሆኑ ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል። በከተማዋ ‘ አጋም በር መገንጠያ ’ በተባለ ሰፈር ጥቃቱ 11 ፡ 30 አካባቢ እንደተፈጸመ ለቢቢሲ የተናገሩ አንድ ከጥቃቱ የተረፉ እማኝ፤ በጥቃቱ በአብዛኛው ማዳበሪያ ለመውሰድ ከተለያዩ ቀበሌዎች የመጡ አርሶ አደሮች እንደተገደሉ ገልጸዋል። ከዘጠኝ እስከ 12 የሚሆኑ ወታደሮች “ ቀጥታ መጥተው ሱቅ ላይ የተኩስ እሩምታ ጀመሩ ” ያሉት የዐይን እማኙ፤ እሳቸውን ጨምሮ ማዳበሪያ ለመጫን በመጠባበቅ ላይ የነበሩ አርሶ አደሮች የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸውን ተናግረዋል። “ የመንግሥት ኃይሎች ” ማሙሽ