ልጥፎች

የታሰሩ ጋዜጠኞችን በሚመለከት ልዩ መንፈሳዊ አጽናኝ ስጦታ ከባቲካን ተደመጠ። CPJ አጋዥ እዮር ላከለት። የልብ የሆነ ቅድስና።

ምስል
  የታሰሩ ጋዜጠኞችን በሚመለከት ልዩ መንፈሳዊ አጽናኝ ስጦታ ከባቲካን ተደመጠ። CPJ አጋዥ እዮር ላከለት። የልብ የሆነ ቅድስና። https://www.bbc.com/amharic/articles/czr87edg0neo «አዲሱ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ጳጳስ በእስር ላይ ያሉ ጋዜጠኞች እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ»   13 ግንቦት 2025, 07:22 EAT   «አዲሱ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ሊዮ 14ኛ ቫቲካን ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ከጋዜጠኞች ጋር በተገናኙበት ወቅት በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች እንዲለቀቁ ጥሪ አቀረቡ።»   «ጳጳሱ "እውነትን ፈልገው ለመዘገብ" ሲሉ ለእስር ለተዳረጉ ጋዜጠኞች ያላቸውን ድጋፍ በመግለጽ፣ የሚደርስባቸው ስቃይ "የአገራትን እና የዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ህሊና የሚፈትን ነው" ብለዋል።»   «የፕሬስ ነጻነት መጠበቅ አለበት ያሉት ፖፕ ሊዮ 14ኛ፣ መገናኛ ብዙኃንም ይህ "ውድ የሆነው ስጦታ" የመናገር ነጻነት መጠበቅን ማረጋገጥ አለባቸውም።»   «ኮሚቲ ቱ ፕሮቴክት ጆርናሊስትስ እንደሚለው ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት 361 ጋዜጠኞች ታስረዋል። ባለፈው ሐሙስ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን መሪ ሆነው የተመረጡት ሊቀ ጳጳስ ጨምረውም ጋዜጠኞች በዓለም ላይ ያሉት ኢፍትሃዊነት እና ድህነት ትኩረት እንዲያገኙ ሚናቸውን እንዲእጡ ጥሪ እርበዋል።»   «መገናኛ ብዙኃን በሚከፋፍሉ ወገንተኛ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ከማተኮር ይልቅ እውነትን በመዘገብ "ለጽንፈኝነት እና ጥላቻ" መድረክ እንዳይሰጡ አሳስበዋል።»   "መልዕክታችንን የምናስተላለፍበት መንገድ በመሠረታዊነት ወሳኝ ነው፤ የቃላት እና የምሥሎች ጦርነትን ባለመቀበል፣ የጦርነት አቅጣጫን መቃወም አለብን።"   "ኃይል እና ጩ...

#ሁለት ጊዜ የተደመጠ #ዕድለኛ ቃለምልልስ።

ምስል
  #ሁለት ጊዜ የተደመጠ #ዕድለኛ ቃለምልልስ። https://www.youtube.com/watch?v=fl_dSegYcYg&t=392s   "በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከአቶ ጌታቸው ረዳ ጋር የተደረገ ቆይታ -ክፍል 1"   "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም፤ ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውለውም።"   እንዴት ናችሁ ቤተ ቅንነት። ደህና ናችሁን?   ህወሃት ተሰረዘ፤ ህወሃት #ቀጠነ ፤ ህወሃት #ወደለ ፤ ህወሃት ነፍሱ ከሥጋው ተለየችም በውነቱ የእኔ አጀንዳ አይደለም። #ተጠቃሚ የነበሩት ሰርክ ይወዝወዙለት። አይደለም የህወሃት መስለሉ - #መሰልሰሉ ፤ ጎልቶ ቢወጣ በለስ ቀንቶት አልደነቅበትም። ለምን?? የምፈልገውን ፍላጎቴን ጸጥ ባለ ዊዝደም ገብ ሂደት ሥልጣኑን ፈቅዶ እና ወዶ ከማዕከላዊ መንግሥት ገዢነነት ተሰናብቷል። እራሱም ድምጽ ሰጥቶ። ለዚህም ነው ሙሉ ፯ ዓመት ጸጥ ብዬ እምከታተለው። ከሚወቅሱትም ሆነ፦ ተስፋ አድርገው ምልሰቱን ከሚመኙትም፤ ከሚሞግቱለትም ወገን አልነበርኩም።    ህወሃትን በዘመነ #ጋሜዬ ገና ጩጬ ሳለሁ፤ በፖለቲካ ሆነ በዕድሜ የማውቀው ድርጅት ነው። ሻብያንም እንዲሁ። የሆነ ሆኖ ያን "የቆጡን አወርድ ብላ" እንደሚባለው #መታበዩ መራራ ስንብቱን አጎናጽፎታል። "አልጠግብ ባይ" ምን ሲል ያድራል እንደሚባለው። ዕድሜ #ለሃምሌ ፭ቱ የአማራ የማንነት እና የህልውና ተጋድሎ ክስተት ማብቃቱን ዓውጆልናል። በሌላ በኩል መቼወንም ዘመን ህወሃት አውራ የዞግ ፓርቲ ሆኖ #ራሱን ችሎ እንደማይመጣም እርግጠኛ ነኝ። ስለሆነም ቅንጣት አቅም አላዋጣም።    ህወሃት ከሌላ ተቋም እራስ ሊወረድ ግን ይገባል። #መክሰስም ፦ #መወንጀልም ካለበት ትዕቢተኛውን የወቅቱን የትግራይ ክልል መስተዳድር የ...

የእቴጌ ጎንደር #ትናንት ይጠራ! ናልኝ አጤ ትናንት የእኔ ሸበላ በመሸቢያ! Bitte kommen Sie in da...

ምስል

ራህብን ማስደንገጥ፤ ራህብ ዞግ የለውም። ለራህብ ካቴና መለገስ አይገባም።

  ራህብን ማስደንገጥ፤ ራህብ ዞግ የለውም። ለራህብ ካቴና መለገስ አይገባም።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   የሃኪሞችን ጥያቄ ይሁን ማናቸውም ፍትኃዊ የህዝብ ጥያቄወችን የአብይዝም መንግሥት በጥንቃቄ፤ በእርጋታ እና በስክነት ሊይዘው የሚገባ ክስተት ነው። ሃኪሞች ጥያቄያቸው #ንጹሁ ነው። የተፎካካሪው ወይንም የተቃዋሚው ፖለቲካ የተግባር ራህብ ላይ ሲሆን የትኛውንም ጥያቄ ወደ ራሱ አስጠግቶ ወደሚፈልገው አቅጣጫ ሃሳቡን ማንሸራሸሩ የማይቀር ነው። ታስታውሱ እንድሆነ የድምፃችን ይሰማ እንቅስቃሴን እንደምን የተቃዋሚ ኃይሉ በዘመነ ህወሃት ሃንድል እንዳደረገው ይታወቃል። ከኦሮማራ ንቅናቄ በኋላ የድምፃችን ይሰማ ንቅናቄ ረብ አለ፤ ከአብይዝም አገዛዝ በኋላ ጸጥ ረጭም አለ።   የሆነ ሆኖ ጥያቄ ያላቸው ወገኖች በችግራቸው ገፊነት አደባባይ ሲወጡ የአቅም ሻሞ አያስፈልግም። በመሃል የሚጎዱት #የተጎዱት ይሆናሉ። የሚጎዱት እንዳይጎዱ ደግሞ ሁሉም ኃላፊነት እና ተጠያቂነትን አመጣጥኖ መከወን ይኖርበታል። አንድ ሃኪም #የሚሊዮኖች እስትንፋስ ነው። አንድ ሃኪም የሚሊዮኖች ቀጣይ ትውልድ #ሮልሞዴል ነው። አንድ ሃኪም የግሎባሉ ዓለም #ዜጋ ነው። አንድ ሃኪም #እናትም #ቤተሰብም አለው።   በሌላ በኩል አገር የሚመራ፤ አገር የሚያስተዳድር መንግስት ኮሽ ባለ ቁጥር ከመደንገጥ ጥያቄውን መርምሮ በአቅሙ ልክ መፍትሄ ሊሰጥ ይገባል። የኢትዮጵያ ቅን እና ትጉህ ሃኪሞች መኖራቸው ችግር ውስጥ ስለመግባቱ ማመልከታቸው #ቂም ሊያዝባቸው፤ ከደረጃ #ሊይስተጓጎሉ ፤ ከቀጣይ የትምህርት ዕድል እስኮላር ሊታገዱ አይገባም። ቀጣዩ ይህ ሊሆን እንደሚችል ስለማስብ ነው ይህን የምጽፈው። በዞጋቸው እዬተነጠሉ የበቀል እርምጃ ሊወሰድባቸው አይገባም።   ተ...

ሳይንስ፤ ቴክኖሎጂ፤ ሥልጣኔ ናቸው። ሥልጣኔያቸው መሠረቱ ዕውነት እና ፋክት ነው። የሁለቱ ጋብቻ መኖርን ያቀላሉ።

ምስል
  ሳይንስ፤ ቴክኖሎጂ፤ ሥልጣኔ ናቸው። ሥልጣኔያቸው መሠረቱ ዕውነት እና ፋክት ነው። የሁለቱ ጋብቻ መኖርን ያቀላሉ።    "የቤትህ ቅናት በላኝ።"     የማከብራችሁ የአገሬ ልጆች እኔ እና እናንተ የምንገናኜው፤ ወደ ተሰደድንበት አገር የተጓጓዝነው ዘመኑ በፈቀደው የቴክኖሎጂ ሥጦታ ነው። አንድ አገር የሳይንስ እና የቴክኖሎጂ፤ የትምህርት ተቋማትን የሚመሩ ማዕከላዊ ተቋማት መፍጠር፤ #ማሰልጠን ፤ የትውልድ ኃላፊነትን መወጣት ነው።   ዘመኑ በሚፈቅደው ልክ አጀንዳውን የእኔ ብሎ አትኩሮት መስጠትም ከሌሎች የመኖር ጉዳዮች በስተኋላ ቆዬኝ እስኪ ሳይሆን #በአቻነት እንዲጓዝ በመርህ ደረጃ መቀበል እና ወደ ተግባር ለመቀዬር የሚችሉትን ያህል መጣር #የሚጣጣል ፤ #የሚቃለል ፤ የሚወገዝ ሊሆን አይገባም።    ቀደምት አገር ግን በብዙ ነገር ኢትዮጵያ ኋላቀር ናት። ቢያንስ ዘመኑ በሰጠው ሥልጣኔ ጋር ተጣጥሞ ለመቀጠል መጣር የተገባ እርምጃ ነው። "ትምህርት ከድል በኋላ" በእኔ ዘመን የነበረ መፈክር ነው። ያ አልጠቀመም። 50 ዓመት በጨለማ ተዋጡ ነበር። የተሰደደው ትውልድ ግን ተምሮ እንሆ የትምህርት ሚር ለመሆን የበቃው በመማሩ ነው።   የዛን ጊዜው " #አትማሩ !" ብዙ ተስፋን አቀጭጮ እና ብዙ ዕድሎችን ለሙጦ ያለፈ ጎጂ ጉዳይ ነው። ዛሬም መደገሙ ያሳዝነኛል። ዛሬ ብዙ ሰው የከተማው ጉሮሮውን አርጥቦ የሚያድረው ማህበራዊ ሚዲያ በፈጠረለት #ትሩፋት ነው። ሥልጣኔ ሊገፋ አይገባም። ሥልጣኔን መፍቀድ እንደ ነውር ሊታይ አይገባም።    ልቅና እና በልዕልና የሚገኜው #በዕውቀት ነው። በመማር ነው። መሰልጠን በድካም ሳይሰለቹ በመትጋት የሚገኝ ትሩፋት ነው። በአብይዝም የመንግሥት ሥርዓት አፈፃ...

«የጤና ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት እና ሦስት ዶክተሮች ታሰሩ» BBC እንደ ዘገበው።

ምስል
  «የጤና ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት እና ሦስት ዶክተሮች ታሰሩ» BBC እንደ ዘገበው። በአብይዝም ይቅርታ ተጠይቆ ቢፈቱ ይሻለል። እርምጃው ብልህነት ያረጠበት ነው።   • https://www.bbc.com/amharic/articles/ckgqdkx3q32o «የጤና ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት እና ሦስት ዶክተሮች ታሰሩ»   ዶ/ር በርናባስ ሳሙኤል፣ ዮናታን ዳኛው፣ ዶ/ር ሀብታሙ ጌታቸው እና ዶ/ር መላኩ አልማው «የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት አቶ ዮናታን ዳኛው እንዲሁም ሦስት የአርባ ምንጭ ጠቅላላ ሆስፒታል ዶክተሮች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ።   በአዲስ አበባ ከተማ እንዲሁም በአማራ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች በቀናት ልዩነት የታሰሩ የጤና ባለሙያዎች ቁጥር አምስት ደርሷል። በአዲስ አበባ ከተማ ሌሎች አምስት የጤና ባለሙያዎች ደግሞ ከሁለት ቀን እስር በኋላ ተለቅቀዋል።   የጤና ባለሙያዎች ከሰሞኑ እያደረጉት ላለው እንቅስቃሴ ድጋፉን የገለጸው የጤና ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ዮናታን የታሰሩት ትናንት እሁድ ግንቦት 3/2017 ዓ.ም. እንደሆነ የማኅበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ መለስ ባታ ለቢቢሲ ተናግረዋል። በ2015 ዓ.ም. የተመሠረተውን ማኅበር የሚመሩት አቶ ዮናታን፤ በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን በሚገኘው ቢቸና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የጤና ባለሙያ መሆናቸውን አቶ መለሰ ገልጸዋል።   ምክትል ፕሬዝዳንቱ እንደሚናገሩት አቶ ዮናታን እሁድ ከሰዓት የተያዙት ከመኖሪያ ቤታቸው ነው። "ከመያዙ በፊት ከትናንት ወዲያ [ቅዳሜ] የሚሠራበት ሆስፒታል አካባቢ እና በሚኖርበት ሰፈር [በሚገኝ የፖሊስ ጣቢያ] ለምርመራ እንደሚፈለግ ደውለው እንዳስታወቁት ነግሮኝ ነበር" የሚሉት አቶ መለስ፤...

ለፖለቲካ እስረኞች ማን ይሆን ጠበቃው? ስለምንስ ከአጀንዳ ውጪ ሆኑ???? #አልገባኝም።

  ለፖለቲካ እስረኞች ማን ይሆን ጠበቃው? ስለምንስ ከአጀንዳ ውጪ ሆኑ???? #አልገባኝም ።   "የቤትህቅናት በላኝ።"   በሁሉም ዘርፍ ያለውን ሁነት ስከታተለው የፖለቲካ እስረኞች ጉዳይ #ባለቤት #አጥቶ ነው እምመለከተው። ሁሉንም አቅጣጫ ዳስሱት። በዬእስር ቤቱ ያሉ የፖለቲካ እስረኞች አጀንዳ የሚሆኑት በስሱ #የፍርድ #ቤት ቀጠሮ ሲኖራቸው ብቻ ነው። ይህ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ትግል #ያልተለመደ ተመክሮ ነው።    ምክንያቱም የፖለቲካ እስረኞች ጉዳይ በዬትኛውም የትግል መስመር ያሉ ተቋማት፤ ንቅናቄወች፤ የፖለቲካ ድርጅቶች ሁሉ #በኽረ #አጀንዳ ሆኖ ነበር እማውቀው። ከእስር ይለቀቁ ዘንድ ህብረ ድምጹ #አህቲ ነበር። አሁን ግን ያ ህብረ ድምጽ የለም። ለምን ይሆን? ጥናት ስላላደረኩበት ያ ነው፤ ይሄ ነው ልል አልችልም። የሆነ ሆኖ ቢያንስ #የእስረኛ ቤተሰቦች እንግልት ላይ ስለመሆናቸው እንኳን ጉዳይ ሊሆን አለመቻሉ ይጨንቃል። ልጆች ያላቸው የፖለቲካ እስረኞችም አሉ። እነኝህ የእስረኛ ልጆች በትምህርት ገበታቸው ላይ ሊያሳድር የሚችለው የሥነ ልቦና ጫናም ከፍተኛ ነው።   በሌላ በኩል ሁሉም እናት አለው እና ይህቺ #እናት በልጇ ሃዘን እንደ ተጎሳቆለች የሰይጣን ጆሮ ይደፈን እና አንድ ነገር ብትሆን #እርግማን ይሆናል። ጭራሽ በአብይ ዘመን የእስረኛ ፍቺ ድፍንፍን ያለ ጉድ ነው የሆነው። ምንም ፍንጪ የለም። ቢያንስ ለቤተሰቦቻቸው ተስፋ ይሆን ዘንድ የፖለቲካ እስረኞች ጉዳይ በግልም ሆነ በጋራ በሰባዊነቱ አጀንዳ ሊሆን ይገባል ባይ ነኝ። እርግጥ ነው #የቅን እና #ቀና ዜጎች #ስጋት በስሱም ቢሆን ትንሽ ይገባኛል። ልፋታቸው ሆነ ድካማቸው አድማጭ ማጣቱ፤ ከእስር የሚፈቱ ወገኖች ለህዝብ ድካም ዕውቅና ለ...