ልጥፎች

#ለምን? ቁራሽ እንጀራ ለጠዬቀ ካቴና??? ማህጸንን እንደ ዱባ ይቀረድዳል።

ምስል
  #ለምን ? ቁራሽ እንጀራ ለጠዬቀ ካቴና??? ማህጸንን እንደ ዱባ ይቀረድዳል።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"     እስከ አሁን የተደከመበት፤ ሙሉ አቅም የፈሰሰበት፤ ብዙ ወገኖቻችን ያጣንበት የኢትዮጵያ ፖለቲካ #እርካታን ይለፍ ሊሰጠው አልቻለም። ለምን? ከሊቅ እስከ ደቂቅ ኢትዮጵያዊው ዜጋ በአደብ፤ በጥሞና ከራስ ፍላጎት፤ ጥቅም እና ድሎት አለፍ አድርጎ ሊያስብበት የሚገባ በኽረ ጉዳይ ይመስለኛል።    በፖለቲካ ምክንያት ትናንት #ስደት ላይ የነበሩት ፖለቲከኞች ዛሬ አገር ውስጥ ገብተው #መኖርን እያኖሩ ነው። ትናንት አገር ውስጥ ሆነው መኖርን ያኖሩ የነበሩ ፖለቲከኞች ዛሬ መኖርን #ለስደት ሰጥተዋል። ይህ ተመክሮ ለዛሬም፤ ለነገም የትውልድ #በረከት ወይንስ #እርግማን ይሆን ብሎ ማንሰላሰል ይጠይቃል። ወደ ራስ አቅርቦም አጀንዳዬ ማለት ይገባል።   በዚህ ውስጥ የእያንዳንዱን ዜጋ መብት እና ግዴታ #ሳይጫኑ ወይንም #ሳይጨፈልቁ በቅንነት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሂደት ቁመና መገምገምም ይገባል። እያንዳንዱ ዜጋ እውነቴ የሚለው የራሱ ሃቅ አለውና። ስለሆነም የችግሮችን #ሴል በማድመጥ እረገድ በወልም በጋራም ሊታሰብበት ይገባል።    ምክንያቱም ነገ የስርዓት ለውጥ ቢመጣ እንኳን፤ ይህ ጠቃሚ ያልሆነው የተመክሮ ሰርክል ወይንም አዟሪት ይደገማልና። ከሆነ ቦታ ላይ መቆም አለበት። የመጨረሻው የሊቃውንቱ የዕውቀት ደረጃ #ዶክተርነት ነው። በውነቱ በብዙ ትጋት እና ልፋት የሚገኝ የዕውቀት አስኳል ነው ዶክተርነት። ዶክተርነት የሊቃውንት #ቁንጮነት ነው።   ይህ አካል #የዳቦ ጥያቄ አለኝ ሲል፤ የደህንነት ዋስትና ይኑረኝ ሲል፤ መኖሬ በዜግነቴ ደረጃ በልፋቴም ልክ ይሁን ሲል፤ በሊቃ...

LIVE: Austria's Eurovision Winner JJ Meets Chancellor Stocker | DWS News... ጥበብ የሆነ #የሊቃውንት #ጉባኤ በኦስትራሽ።

ምስል
ጥበብ የሆነ #የሊቃውንት #ጉባኤ በኦስትራሽ። የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስተር ከከፍተኛ የካቢኔ አባሎቻቸው ጋር አሸናፊውን አርቲስት ጄጄን (አርቲስት የኋንስን)እንዴት አክብረው አቀባበል እንዳደረጉለት። ዕውቅና በምን ልክ እንደሰጡት ተመልከቱ። አገር እና ህዝብ፤ ጥበብ እና መሪ፤ መሪ እና ትውልዱ #ዕውነት የሆኑበት ልዩ #ክስተት ። ልዩ መታደል። ልዩ የምድር ገነት።    ለዚህም ነው እኔ ኢሮ ቪዥን ሶንግ ኮንቴስት በዬአመቱ ORF 1 እምከታተለው። ልዩ ጣዕም ልዩ ቃና አለው። የአርቲስት ጄጄ እናቱ ከፊሊፒን አባቱ ከኦስትርያ ዱባይ ለስራ ሄደው ነው የተገናኙት። እና ይህ ሙሉ አቅም ያለው ወጣት ከውህድ ማንነት የተገኜ ነው። ኢንቴግሬሽን ክብር ሲሰጠው፤ ውህድ ማንነት እንዲህ የላቀ ክብር ሲሰጠው ዓለማችን ያምርባታል። #እንማርበት ።    ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 2025/05/19

«#UnitedByMusic” ይህ የእምዬ ሲዊዘርላንድ ለዓለም የላከችው የመንፈስ ስጦታ ነው። #Stolz!

ምስል
  • « #UnitedByMusic ” ይህ የእምዬ ሲዊዘርላንድ ለዓለም የላከችው የመንፈስ ስጦታ ነው። #Stolz ! "ጥበብ ቤቷን ሠራች፤ ሰባት ምሰሶም አቆመች።"   79ኛው የዓውሮፓ የሙዚቃ ውድድር ትናንት በባዝል ከተማ በእምዬ ሲዊዘርላንድ #ኦስትሪያ ያሸነፈበት መሰናዶ በስኬት ተጠናቋል። በ2024 እምዬ ሲዊዘርላንድ አሸናፊ ስለነበረች የ2025 አዘጋጅ ቅድስቷ ነበረች። አንድ ሳምንት ቀድሞ መስተንግዶ የነበረ ሲሆን ተሳታፊወች በተመረጡ ከተሞች በነፍስ ወከፍ ግብዣ ነበራቸው። ህሊናቸው #ቤተሰባዊነትን ይዋህድ ዘንድ የነበረው ቅድመ መሰናዶ እጅግ ሳቢ ነበር ለእኔ።   ዘመናችን የዲጅታል ሆነ እና ሰውኛ ጸጋችን እዬተጫነው ስለሆነ የእኔ ማሽን ጄኔሬሽን አስመልክቶ ስጋቴ እጅግ የላቀ ነው። ለዚህም ነው ዓለማችን የፍቅር ተፈጥሮን በትምህርት ደረጃ #ካሪክለም ነድፋ ልትሰጥ ይገባል በማለት የዛሬ 15 ዓመት #ለተመድ እና #ለአውሮፓ ህብረት መሻቴን በክብር የላኩት። እነሱም የተከበሩ ስለሆኑ ለእኔ አንዲት ባተሌ ብላቴና አክብረው መልስ ሰጡኝ።   ይህን ያነሳሁት የነገ ጉዳይ ውስጤ ስለሆነ የኦስትርያ፤ የሲዊዝ የጀርመን እና የኢትዮጵያን የትውልድ ቀረፃ መሰናዶወችን ከውስጤ ሆኜ ነው እምከታተለው። ጭንቅላቴን የሚመራውም ይህ ትጉህ ሰውኛ የተስፋ ብርኃናማ መንፈስ ነው። ሰዋኛ! ሰውኛነት! ተፈጥሮ! ተፈጥሮኛነት! ቢፈቀድላቸው በዓለማችን ያለው የስጋት ዳመና ተወግዶ #ቤተሰባዊነት ይነግሥ ነበር።   የሆነ ሆኖ ዊዝደም ያበቀለው የአውሮፓ የየዓመቱ የሙዚቃ ድግሥ የዬዓመቱን ቴክኖሎጂ፤ የየዓመቱን የሳይንስ፤ የዓመቱን የሞድ፤ የየዓመቱን የሙዚቃ ምርት ዕድገት፤ የያዓመቱን የሚዲያ ክህሎት፤ የየዓመቱን የኮስሞቲክ ሥልጣኔ ብቻ ሳይሆን የየዓመቱን...

ከቢቢሲ BBC አሁን ያገኜሁት መረጃ ነው። ረሃብን ማሰር?

ምስል
  ከቢቢሲ አሁን ያገኜሁት መረጃ ነው። ረሃብን ማሰር?   • ከቢቢሲ አሁን ያገኜሁት መረጃ ነው።       https://www.bbc.com/amharic/articles/cn8zxd33d0xo «አንድ ሱዳናዊ ሐኪምን ጨምሮ ከ80 በላይ የጤና ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተነገረ» «ከሰሞነኛው የጤና ባለሙያዎች ከፊል የሥራ ማቆም አድማ ጋር በተያያዘ በመላው አገሪቱ ከ80 በላይ የጤና ባለሙያዎች መታሰራቸውን የንቅናቄው አስተባባሪዎች አመለከቱ።   የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በተለይም በትላልቅ ከተሞች በሚገኙ ሆስፒታሎች የሚያገለግሉ በርካታ የጤና ባለሙያዎችን እያሰሩ እና እያወከቡ መሆኑን አንድ የንቅናቄው አስተባባሪ ለቢቢሲ ተናግረዋል።   ከጎንደር ዩኒቨርስቲ በፀጥታ ኃይሎች ተይዘው ከተወሰዱት የሕክምና ባለሙያዎች መካከል አንድ ሱዳናዊ ሐኪም መኖሩን ባልደረቦቹ ለቢቢሲ ገልጸዋል።    "ሐኪሞች፣ ነርሶች፣ ላብራቶሪ ባለሙያዎችን" ጨምሮ በርካታ የጤና ባለሙያዎች ለወከባ፣ ለድብደባ እና ለእስራት እንደተዳረጉ ገልፀዋል። የንቅናቄው አስተባባሪዎች ባሰባሰቡት መረጃ መሠረት በቁጥጥር ስር ከዋሉት ባለሙያዎች መካከል ዘጠኙ ሴት የጤና ባለሙያዎች ናቸው። 'የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች ንቅናቄ' በሚል ስያሜ የደሞዝ እና ጥቅማ ጥቅም ጥያቄን ጨምሮ የጤና ሥርዓቱን ያስተካክላሉ ያሏቸው 12 ጥያቄዎችን ያነሱ ባለሙያዎች፤ ከግንቦት 5/2017 ዓ.ም. ጀምሮ የከፊል የሥራ ማቆም አድማ መምታታቸውን ገልፀዋል።   ከዚሁ አድማ ጋር በተያያዘ አዲስ አበባ የሚገኙትን ጥቁር አንበሳ እና ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታሎችን ጨምሮ በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች በርካታ የጤና ባለሙያዎች ከሆስፒታል እና ከቤታቸው በፀጥታ ኃይሎች እየተወ...

የኢትዮጵያ ሃኪሞች ጥያቄ የኢትዮጵያ እንደ #ቀይ #የደም #ሴል ጥያቄ ሊታይ ይገባል። #የፖሊሲ አዲስ ጥሪም አለበት።

ምስል
  የኢትዮጵያ ሃኪሞች ጥያቄ የኢትዮጵያ እንደ #ቀይ #የደም #ሴል ጥያቄ ሊታይ ይገባል። #የፖሊሲ አዲስ ጥሪም አለበት። ህክምና ሁልጊዜ #በአስቸኳይ ጊዜ ውስጥ ነው።    " ሥራውን ሁሉ የሚያስገኝ እርሱ ጥበብን አስተምሮኛልና የተገለጸውንና የተሠወረውን ሁሉ አወቅሁ።" (መጽሐፈ ጥበብ ምዕራፍ፯ ቁጥር ፳፩)     ብልህነት ቢኖር፤ ለህዝብ ርህርህና ያለው መንፈስ ኢትዮጵያ ውስጥ ቢኖር፤ ህዝቤ የእኔ #ውስጤ ነው የሚል ፖለቲካ እና ፖለቲከኛ ቢኖር በውነቱ የሃኪሞች ጥያቄ የኢትዮጵያ የቀይ ሴል ጥያቄ ስለሆነ #መሪ አጀንዳ አድርጎ መውሰድ ይገባ ነበር። ህክምና ህንፃ ግንባታ አዬደለም። የሰው ልጅ የትርታ ፋክት እንጂ። የትኛውም የፖለቲካ አቋም፤ ወይንም የፖለቲካ ተቋም እስትንፋሱ የሰው ልጅ ጤንነት ነውና። ይህን በኽረ ጉዳይ #የካድሬ ማሳ ማድረግ አስፈላጊ አይመስለኝም።   ብዙወቹ የብልጽግና ዘመን ሰጥ ካድሬወች፤ በርካታ የግል የሚዲያ ሰራተኞች፤ አክቲቢስቶች እኮ ከአብይዝም ጋር የመጡ ናቸው። አብይዝምን መደገፍ መብት ቢሆንም ተመክሮ፤ ስክነት ሳይሆን እንደ ግል የተሻለ ዕድል ምቾት ላይ ያተኮሩ፤ ወይንም የተጽዕኖ ፈጣሪነት ረሃብተኞች ሊሆኑ ይችላሉ። ይህም ሆኖ አብይዝምን ስለደገፋ ብቻ ጥልቅ እና ውስብስቡን የኢትዮጵያ ፖለቲካ እንዲተነትኑ የሚሰጣቸው ዕድል ይገርመኛል።    ፖለቲካ የዳማ፤ የካርታ ጨዋታ አይመስለኝም። ግጥግጦሽም አይመስለኝም። የፖለቲካ ሳይንስነቱ ሆነ ፍልስፍናነቱ እራሱ ያንሰዋል ባይ ነኝ። የመኖር 13ኛው #ፕላኔት ፖለቲካው ስለሆነ። ሌላው ቀርቶ በፖለቲካ ተምሮ የመጨረሻ የዕውቀት ዳር ደርሶ፤ መምህርም ሆኖ ካልሰራበት ይልቅ፤ ሳይማር ግን በመደበኛ በሥርዓቱ፤ በደንቡ፤ በዲስፕሊኑ ...