ልጥፎች

ከፌብሩዋሪ, 2026 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ኦ፧ ሻሸመኔ! እግዚአብሄር ይደነግጣል፤ ገደሉ ተደፈረ ። ለመሰናክላዊ አዲስ ገረጭራጫ ዘመን ይለፍ ተሰጠው። ኑ! አ...

ምስል

#Timing.

ምስል
  #Timing . መረጃው ዘገዬ፤ የአብይዝም መንገድ ……… ምን ልበለው???   ********     "Timing refers to the #strategic selection of the #exact #moment for an #action to #achieve the #best #result or the or the #regulation of when event occur."       https://www.youtube.com/watch?v=gWLfcwf1dS0   “የቀይ ባሕር ጉዳይ አይደለም ችግር የፈጠረው”   • ዛሬ የኤርትራ መንግሥት መልስ ስለሰጠ አያይዠዋለሁኝ። ለዳኝነትም ለታሪክም መንገዱ ይህ ስለሆነ። ሁለቱም የሚመሩት ህዝብ አለ። ህብራዊነት ውህድ ማንነትም አለ። ከስሜት የጸዳ ጠንቃቃ ተግባር መፈጸም ይገባል። ኃላፊነት የሁሉ ኃላፊነት ነውና። ****   እስከዛሬ ስለምን #አምቀው ፤ #ተጭነውም አቆዩት ይህንን ሃቅ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ጥያቄ ነው። በወቅቱ ተናግረውት ቢሆን ኖሮ፤ ብዙ መካረሮችን #ሊያረግብ ይችል ነበር። በተለይ መንግሥት እና ህዝብን #የሚያቃቅር ወሳኝ ጉዳይ ብዙ ነገር ስለሚያሳጣም። የሆነ ሆኖ #timing አጤ ጉግል እንዲህ ይተረጉመዋል።   "Timing refers to the #strategic selection of the #exact #moment for an #action to #achieve the #best #result or the or the #regulation of when event occur."    ጊዜን በጊዜው በሰጠው ጊዜ ማናገር ይገባል። ለቀኑ ቀን ሲሰጠው ለቀኑ ቀኑ እራሱ መፍትሄ ያመነጫል የሚል የእኔ ፍልስፍና አለኝ። ቀን ...

የወልቃይት ጉዳይን ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ መልስ ሰጥተውበታል

ምስል
   https://www.youtube.com/watch?v=Z4vI8mHgxkI   “ተፈናቃይን መያዣ ያደረገ ፖለቲካ”   የወልቃይት ጉዳይን ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ #ፍንትው ያለ መልስ ሰጥተውበታል። የመንግሥታቸውን #አቋም ገልጸዋል። "እኔ መብት የለኝም" ብለዋል። ወሳኙ እዛው የሚኖረው ህዝብ ነው ብለዋል። ይህን አቋማቸው አጽንተው ይቆዩ አይቆዩ የሚውቀው ፈጣሪ ነው። በሌላ በኩልም ከሌላው ጊዜ በተለየም #ጸጸትም አለበት በንግግራቸው ውስጥ የጤና፤ የትምህርት፤ የበጀት ጉዳይን አስመልክቶ መንግሥታቸው ሳያሟላ መቆየቱ #በደል መሆኑን ገልጸዋል።    እንደ አንድ የሚዲያ ሰብእና፤ እንደ አንድ የአገሩን ፖለቲካ በትጋት እንደሚከታተል ሰብዕና በአንድም በሌላም ቤተሰብ ሳገኝ ስጠይቅ የፈለገ ችግር ቢፈትናቸውም #ከነፃነታቸው በላይ ሊሆን እንደማይችል፤ ሙሉ ነፃነት ላይ እንዳሉ ገልጸውልኛል። ትናንት እንደፃፍኩትም አካባቢው #ፍጹም ሰላም መሆኑ ብቻ ሳይሆን በጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አመራር፤ በሠራዊቱ ላይም ጠንካራ እምነት እንዳላቸው ያረጋገጥኩት ሃቅ ነው።    እኔ የሚገርመኝ ዘመን አልፎት እየነጎደ የሚገኜው አኞው የህወሃት ከፍተኛ አመራር ወልቃይት፤ ጠገዴ፤ አዲረመጥ፤ ጠለምት፤ ማይጠምሪ፤ ሰቲት፤ ራያ እኮ #በእጁ እያሉ ነበር መብረቃዊ ያለውን #ጦርነት የጀመረው። "ዶሮን ሲደልሏት በመጫኛ ጣሏት" ሆኖ ነገሩ ዛሬ "የትግራይ ሉዓላዊነት" ካልተመለሰ በጅ አልልም ሲል አዳምጠዋለሁኝ። ቀድሞ ነገር ክልል ብሎ ሉዓላዊነት የለም።    ምን አልባት ገዢ ሳለ በዚህ ስሌት ሊሆን ይችላል የወቅቱ ፕሬዚዳንት አቶ አባይ ዘውዱ ጎንደርን የተዳፈሩት በትዕቢት። ክብረ ልዕልናቸው ያከተመውም በዚህ በተንጠ...

#ይቅናሽ እናትዓለም።

  እቴጌ ጎንደር ጠቅላይ ሚኒስትርሽ ትናንት ለተፈጠረ፤ ሞገድ ላይም ለተመሠረተ « #ስምረት »   ለሚባል የህወሃት ፍንካች ድርጅት ህሊናሽን #ቀብድ ሊሰጡልሽ ነው። #ሱባኤሽን ጠበቅ አድርገሽ ያዢ። #ይቅናሽ እናትዓለም። አሜን።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፰።   ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ በነገረ - ወልቃይት - ጠገዴ - አዲአርቃይ - አዲረመጥ - ጠለምት፤ ራያም ታክሎ የአማራ ክልል ቤተኛ ቢሆኑ የሚያስገኜውን ኢኮኖሚያዊ፤ ፖለቲካዊ፤ ስትራቴጅካዊ ጥቅም ስለሚያውቁ፤ ለዚህ በኽረ ጉዳይ #በጋድም ዕይታ፤ ጋድም ውሳኔ ሊሰጡ ይችላሉ። ዛሬ ላይ ማን አቅም ያለው ሊቀ - ሊቃውንት አለና ይፍሩ? የቲም አንባቸው ሰማዕትነት በአንድም በሌላም ከብዙ ፖለቲካዊ ሁነቶች ጋር ውህድ ነው።    ከውጥኑ በዶር አብይ አህመድ በ100 ቀናቸው ወደ ትግራይ ሲያቀኑ ጥያቄው ቀርቦላቸው ይህ የዲያስፖራው እንጂ የጎንደር ጉዳይ አይደለም ካሉ በኋላ ጎንደር ላይ ሲገኙ ደግሞ " #የአፍ ወለምታ ነው" አሉ። ያን ጊዜ ምልዓት ይደግፋቸው ስለነበር በቅጽበት ወጀብ ተነስቶ ነበር። በኋላ ግን የአፍ ወለምታ በሚል ኳሏት እና ሁሉም ተረጋጋ። አንድ ተጋሩ እሳቸው ወደፊት ከመምጣታቸው በፊት በነበረው ፍልሚያ አንዲት ሐረግ የፃፈ የሞገተ ሁንልን ያለ አልነበረም። ግን እማራዬ እጁ ስለምን አመድ አፋሽ ሆነ????    ወደ ቀደመው ምልሰት ሲሆን፤ ጉዳዩን ያዝ ለቀቅ እያደረጉ የልባቸውን በልባቸው ይዘው #ቅጣቱን አና አሉት። እሽት አድርገውታል ባዕቱን። እንደ አስፈላጊነቱ የነጠረውን ሃቅ እንደ ልጆች ጢባጢቦሽ ጨዋታ ትልቁን አመክንዮ ወለም ዘለም ሲያደርጉት ሰነባበቱ። መስቃም ነበረበት...