ልጥፎች

መሪነት ስጦታ ነው። የገብያ ህግ አይገዛውም።

  መሪነት ስጦታ ነው። የገብያ ህግ አይገዛውም። ቅብዓ ከገብያ ህግ ውጪ ነውና። መቀባት #ዊዝደምን መታደል ነው።  ዊዝደም የሰማዩን የምድሩን የባህላዊ ህግጋትን ካለመዳፈር አህዱ ይላል። ጥንቁቅነት። የመሪነት አቅም ምንጩ #ጥሞናዊ ርግታ ነው።  ጥሞናዊ ርጋታ የአምላካችን የአላኃችን ፈቃድ የጥዬቃ ጊዜ ብቻ ሳይሆን እራስን #የመገሰጪያ ጊዜም ነው።  እራስን ለማረም ድፍረት እንጅ ፈሪነት አያዋጣም። መሪነት ሕይወትን የመረዳት #ፍጥነትን ፤ #ክስተቶችን በጥልቀት የማገናዘብ ብቃትን፤ የዘመኑን #ሉላዊ የፖለቲካ ባህሬን የማጤን ክህሎትን፤ ብቁ የማገናዘብ አቅም ከማድመጥ ተሰጥዖ ጋር ይጠይቃል።  መሪነት ታምራታዊነት አይደለም ለገኃዱ ዓለም ዕውነታ። መሪነት በግል እና በጋራ አቅም ሰልጥኖ መፍለቅን ይጠይቃል። መሪነት ቲም ሊደርነት ነውና።  ሥርጉትሻ2024/07/19

መሪነት ከማህበረሰብ ለመማር መፍቀድን ይጠይቃል እንጂ "ደንቆሮ" እያሉ ማህበረሰብን ማቃለል፤ ማጣጣል መሪነት አይደለም። ሳይለንት ማስ ዲስክርምኒሽንም ይቁም እላለሁኝ።

  ብዙ ጊዜ " #ደንቆሮ " የሚለውን ቃል የሚደፍሩ ሰብዕናወች ይገርሙኛል። እነሱ ተፈላስፈው ወይንም ተጠበው ዓለምን #ከውችንፍር ያዳኑበትን የእውቀት ጥግ ቢያሳዩን ምንኛ ባደነቅናቸው ነበር።  አንድ ስብስብ መምራት እያቀተ ሲፈርስ //ሲሰራ ለሚውል #የአቋም #አክሮባቲስትነት ላይ ተፈናጦ እግዚአብሄር፤ አላኃችን በአምሳሉ ለምስግና የፈጠረውን የፍጥረት አውራ የሰው ልጅን ሰርክ " "ደንቆሮ/ ደንቆሮወች" እያሉ ሲዳፈሩ #ቅጭጭ አይላቸውም። አይፀፀቱም ይቅርታም አይጠይቁም።   #መሪነት በዚህ ውስጥ ዕዳ ወይንስ ባላንጣ ለተፈጥሮም ለሰባዕዊነትም ብለን ጥያቄ እንድናነሳ እንገደዳለን።  እግረ መንገዴን እምለው #ዝምታችን #ይከበር ። ሳይለንት ማስ ዲስክርምኒሽንም ይቁም እላለሁኝ።  ሥርጉትሻ 2024/07/19   መሪነት ከማህበረሰብ ለመማር መፍቀድን ይጠይቃል እንጂ "ደንቆሮ" እያሉ ማህበረሰብን ማቃለል፤ ማጣጣል መሪነት አይደለም።  እንዲህ ያለ ሰብዕና አይደለም ለመሪነት #ለመመራትም ብቁ ነው ብዬ አላሰብም። እግዚአብሄር // አላህ በአምሳሉ የፈጠረው ፍጡር ለዛውም በወል እንዴት "ደንቆሮ" ይባላል።  በግለሰብም ደረጃ ቢሆን የህግ ጥሰት ነው። አንጎልማ ድንቢጥም አላት። የሰው ልጅ ህሊና ስላለውም ነው ከእንሰሳት የሚለዬው።  ታላቅ የፍጥረት ዓውራን "ደንቆሮ" ማለት #ምጥ እና #ዳጥ ። የሆነ ሆኖ መሪነት #ከማህበረሰቡ #ለመማር መፍቀድን ይጠይቃል።  #አክብሮ መነሳት። ይህ ማለት በማህበረሰቡ የህይወት #ውጣ #ውረድ ፈቅዶ #በንቃት መሳተፍ ይገባል። ሥርጉትሻ 2024/07/19

መሪነት የህይወትን ማህደርነት መመርመር አለበት ስል ...

      መሪነት የሕይወት #ማህደርነትን መመመርን ይጠይቃል። ሕይወት በዥንጉርጉር ቀለማት ህብረ ዝማሬ የቆመች ናት።  ስለዚህ አክብሮ ተነሰቶ ማድመጥን ይጠይቃል። ሕይወትን ግርግር ማድረግ የመሪነትጥራት አይደለም።  ሕይወትን ርጉ እና የማህበረሰቡን የቀደሙ ልማዶችን ፈጥኖ አለመዳፈርን ይጠይቃል። ስክነት። ሥርጉትሻ 2024/07/19   መሪነት የህይወትን ማህደርነት መመርመር አለበት ስል የዛሬውን ብቻ ሳይሆን፤ የማህበረሰቡን የቀደሙ ማንነትን መስታውት መሆኑን አምኖ በቅንነት መቀበል ይገባል።  የትላንቱን - ከዛሬ፤ የዛሬውን - ከነገ ጋር በማጣጣም እና በማገናዘብ የተሻለ የሕይወት ጎዳናን ማመላከት ይጠበቅበታል።  ዕውነት ውስጥ ሆኖ ዛሬን ተሻግሮ ነገን ለማኖር የአቅም #ጥሪትም ሊኖረው ይገባል።  በዚህ አመክንዮ ትናንት #ዛሬን ስለሰጠው ዛሬ ላይ ተቀምጦ ትናትን መውቀስ፦ መንቀስ እንዲያም ሲል የትናንትን አበርክቶ #መደፍጠጥ አይገባም።  ለዛሬ እርሾው ትናንትን አልቦሽ ዛሬ ዬለም። ፍላጎቱ ተንሳፋፊ እና #ትንታበትንታ ይሆናል። የታነቀ ህቅታ።  የብዙ ውድቀቶች መሠረቶችም እርሾ አልቦሽ ጉዞ ነው ለብላሽ ገብያተኝነት የሚያጋልጠው።  ሥርጉትሻ2024/07/19

#ተናኘ።

  መንፈስህ ይጠራኝ ዘንድ ተማፅኜ ከአንተ ጋር እዘልቅ ዘንድ ተጠሙኜ ባላዬሁሽ እንዳታልፈኝ ተንበርክኬ ለምኘ አባብዬ ስለአንተ ለመኖር ቃል ገብቼ እራሴኑ ሞግቼ እንሆ ረትቼ፤ ዝንፍ ላል አንተን ተማምኘ ጋሻ ጥላዬ ብዬ ጥማትህ ራሃብህ ----------------------- #ተናኘ ። ጥሪህ ይምረኝም ዘንድ ፀልዬ ርህርህናህ ስቦኝ ቢማርከኝ ምን ይደንቅ አንተዬ? ዕፁብ ድንቅ ልዩ አዋዬ መካሪዬ! ሰባዕዊነት - ደግዬ ተፈጥሯዊነት - መልካምዬ የጽናት ፅዋዬ የአደራ የእምዬ የአሻራ የተክልዬ። "የቤትህ ቅናት በላኝ።" ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 19/07/024 ሰዓት 13.10 ሰባዕዊነት ይመስጠን።

#አጤ #ስሜት ይጠይቅ?

  #አጤ #ስሜት ይጠይቅ? ዛሬ ርግቦቼ እዬበጠበጡኝ ነው። ለምን በቀጠሮ።  የሆነ ሆኖ መገረም ከውስጥ ወይንስ ከላይ?   #መገረም በአክሽን ወይንስ #በጭብጥ ?  መገረም በአክሽን መበራከት ወይንስ በጭብጥ #ጥራት ?  መገረም በውዳሴ ክምር ወይንስ #በህይወት ፍልስፍና #መርኃዊነት ?  መገረም በውጥን መበራከት ወይንስ #በማጠናቀቅ በረከት?  መገረም በመጠናቀቅ በረከት ወይንስ ለህዝ ባለው #የተደራሽነት #ጠቀሜታ አቅም?  መገረም በአንደበት ርቱዕነት ብቻ ወይንስ በንግግሩ ውስጥ ባለው የህይወት መስመር ጭብጥ #ዕውነታዊነት ?  መገረም በሰዋዊነት ማዕከላዊነት ወይንስ በወረታዊ እንቁጥቁጥ?  ሥርጉትሻ 2024/07/19

ነፃነት

  አንድ ሰው ሰብዕናው ሲመዘን ምን ያህል ዕውነት በእሱ ላይ አድሮ ዕውነት ዕውን ሆኗል ከሚል መነሻነት ሊሆን ይገባል። ይህንን የሚደፍሩ #ነፃነታቸውን በውል ፕራክቲስ ያደረጉ ሰብዕናወች ናቸው። ነፃነት ጋር የተዋወቁ ሰብዕናወች ቅጽበታዊነት #ዝር አይልባቸውም።  ቅጽበታዊ አክሽን ለትወና መልካም ነው፦ የጥበቡም ቤተኛ ነው። መደበኛ ሕይወት ለሚመራ ሰብዕ ግን ቅጽበታዊነትን የሙጥኝ ካለ በቅጽበት ውስጥ ብዙ ነገር ይናዳል። አብሶ ለዬትኛውም ደረጃ #መሪ ከተሆነ። ብዙ ምስቅልቅ ይፈጠራል። ምኞቴ እና ህልሜ #ቅጽበታዊ ሰብዕናወች ተከታይ እንዳይኖራቸው ነው።  ጎዳናው አጥፊ ስለሆነ። #ባልነቃው #ሕሊና ታቅዶ በደራሽነት ስለሚከወን የአደጋ ጊዜ #አበረካች ስለሆነ። ቅጽበታዊነት #አክ ሊባል የሚገባ ባህሬ ነው። ነፃ አስተሳሰብ የሚያራምዱ የሚደነግጡበት፤ የሚቻኮሉበት፤ የሚጣደፋበት ምንም ነገር ስሌለ ሰክነው አስበው እረግተው ይራመዳሉ።  ሥርጉትሻ 2024/07/19

ሐይሌ ገብረስላሴ ከበቀለ ሞላ ሰረቀ || እነሱ ከሀይሌ ገብረስላሴ ሰረቁ || ምኑን?

ምስል

ፋኖን ወደ አንድ ዕዝ ማዕከል ማምጣት ይቻል ይሆን?

ምስል

ዕውነት #ጋራጅ #የለውም። #የአማራ #የማንነት #ተጋድሎ፦ 2) #የአማራን #የህልውና #ተጋድሎን ውስጥ ማድረግ ይገባል።

ምስል
  # ዕውነት #ጋራጅ #የለውም ።   #ጤና ይስጥልኝ።           እንዴት አደራችሁ ማህበረ ቅንነት? #በርትታችሁ አደራችሁ? ትናንት ጦር ግንባሩ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ነበር። ካቴና ላይ ያሉ ወገኖቻችንም ይታወሱ። የተፈቱም ይኖራሉ።   መሬት ላይ ትክክለኛ ዘጋቢ ስለለ ነው። ቢፈቱም መልሰው ያስሯቸዋል። ልቀቁ ነው። እዬለቀቁላቸው ነው። በውነቱ ለእስረኛ #ሙግት ቀርቷል። እንደ ነውርም እዬታዬ ነው።   ሲያነክተን ውሎ በሚያድር የምጠዬፈው " #የሰበር ዜና" ቁምነገር የማሳት አቅሙ ልክ የለውም። የሰበር ዜና ሚዲያው ወዘተረፈ እንደ ሥልጣኔም የታዬ ይመስለኛል። ነርብን፤ ካርቲሌጅን የሚሰባብር ።   ብዙ ወገኖቻችን እንዳጣን ይሰማኛል። ብዙወቹ የእኔ ቅኔው ጎጃም ነበሩ። እስካሁን አልመጡም። እንጃ ኢንተርኔቱ ካልተሟላ አላውቅም።    ቸር ያሰማን። ቸር እንሁን። ቅንም እንሁን። ቢያንስ ለተጎዱ ወገኖቻችን #ስስ አንጀት ይኑረን። ትናንት ሙሉ ቀን ፌቡ የዋልኩት ህዳር ከታጠነ ወዳጆቼን አገኛለሁ በሚል ነበር።   #የገዘፈውን … ጣምራ የተጋድሎ አመክንዮ አንኳር አጀንዳ ይሁን። ማህንዲሱም፤ ፓስተሩም ስለተበራከተ እንጂ ብዙ እጅግ ጥንፍ ተጋድሎ አማራን ይጠብቀዋል። ዛሬ ይህ ከሆነ የዛሬ 15/20 ዓመት ይታሰብ። እኔ ብቻም ነኝ የትግሉ ዘርፍ በዚህ መልኩ የማቀርበው።    1) #የአማራ #የማንነት #ተጋድሎ ፦ 2) #የአማራን #የህልውና #ተጋድሎን ውስጥ ማድረግ ይገባል። እያገረሸ የሚፈትነን የቀራንዮ ሥነ ስቅለት እያለብን በሰናፍጭ ጉዳይ አቅም አናባክን። ሊቃናቱ ይገናኛሉ። ማገዶነታችን በልክ ይሁን። ሁሉም ጥሞና ቢወስድ መልካም ይመስለኛል።    "የቤትህ ቅናት በላኝ። "   ሸበላ ቀን። ኑሩልኝ። አሜን። ሥርጉትሻ 2024

ታላቁ ተልዕኮው።

  መ ሪነት # አቅም # መፍጠር ነው ታላቁ ተልዕኮው። የ ፈጠረውን አቅምም በቅጡ ለ መምራት የራሱን የ ምምራት # አቅም ፦ # ክህሎት ማሰልጠንም ይገባዋል።   ይ ህን አዋዶ ህዝብ ጠቀም ማድረግም ሌላው የመሪነት የ ጥበብ ዘይቤ ነው። ሥርጉትሻ 2024/07/17