የፖለቲካል ፓርቲን የመረጠ ሰብዕ #የእኔ የሚለው የፖለቲካ ዕይታ ሊኖረው አይችልም።
የፖለቲካል ፓርቲን የመረጠ ሰብዕ #የእኔ የሚለው የፖለቲካ ዕይታ ሊኖረው አይችልም ። "የቤትህ ቅናት በላኝ።" #ምዕራፍ ፲፰። ፎቶው የፖለቲካ ድርጅት ቋሚ ሠራተኛ ሳለሁ የነበረ የሥራ መታወቂያ ካርዴ ላይ ያለ፤ እንደ ልጄ የማዬው፤ አብሮኝም የተሰደደ፤ እጅግ እምሳሳለት የፓርቲዬ የኢሰፓ ቅርሴ ነው። ፓርቲዬን ኢሠፓ እወደዋለሁኝ። በህይወቴ የመጀመሪያውም የመጨረሻውም ፓርቲዬ ኢሠፓ ነው። ከኢሠፓ ጋር እስከ መጨረሻው ታግያለሁኝ። እስከ ዛሬዋ ቀን ድረስ ለፓርቲዬ ደንብ፤ ፕሮግራም #በድንግል ነው ያለሁት። ከፓርቲዬ ኢሠፓ መራራ ስንብት በኋላ አይደለም የፖለቲካ ድርጅት፤ ማህበር እንኳን በአባልነት ተመዝግቤ፤ ተሳታፊ ሆኜ፤ መዋጮ አዋጥቼ አላውቅም። ወደፊትም ፈጽሞ አይታሰብም። ይበቃል። እንደ ዕድል ሆኖ እኔ አገር ለመምራት ሙሉ ልቅና፤ ሙሉዑ ልዕልና፤ ሙሉ ብቃት በነበራቸው ታላላቅ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሊቀ - ሊቃውንት ነበር የመለመሉኝ። #የሠሩኝ ልበል። እነ ጓድ ገብረመድህን በርጋ፤ እነ ጓድ ወንድወሰን ኃይሉ ወዘተ… የማይናወጽ ጽናት፤ #የማይበረግግ ሰብዕና፤ እጥፍ ዘርጋ የማይል ዕይታ፤ ገባ ወጣ የማይል የፖለቲካ አቋም ብቻ ሳይሆን አጥርቶ የመስራት ሚስጢር፤ የፖለቲካ ፓርቲ ጽንሰ ሃሳብ፤ ዲስፕሊን ተልዕኮ በተለያዩ የኮርስ፤ የሰሚናር፤ የጉባኤ ዕድሎች እንድሳተፍ በማድረግ ብቻም ሳይሆን ህይወቱ እኖረው ዘንድ በቅርብ እየተከታተሉ አዕምሮዬን አነጹት። የትኛውም የፖለቲካ ድርጅት ቢመጣ - ቢሄድ፤ ሚሊዮኖች የእኛ ቢሉት፤ ስልጣን ቢይዝ ቢለቅ ከቶውንም #አይናፍቀኝም እስከ ህይወቴ ፍፃሜ። በዛ በተደራጄ፤ ምራቁን...