ልጥፎች

ከጁን, 2024 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ክፋነት ስለምን ዓለምን ገዛት? ለምን? ክፋትን ጭካኔን የሚቋቋም ተቋም ለመገንባት ሃሳቡም ስሌላት።

ምስል
  ክፋነት ስለምን ዓለምን ገዛት? ለምን? ክፋትን ጭካኔን የሚቋቋም ተቋም ለመገንባት ሃሳቡም ስሌላት።   "ጥበብን አግኝ ማስተዋልን አግኝ አትርሳም፦ ልጄ ሆይ ከአፌ ቃል ፈቀቅ አትበል፦ አትተዋት ትደግፍህማለች" ምሳሌ ምዕራፍ ( ፬ ቁጥር ፭)   ክፋነት ዓለምን እያስተዳደረ ነው። ጭካኔም ዓለምን እዬናጣት ነው። ምክንያቱን ለዘጠኝ ዓመታት ያህል መረመርኩት። የመፍትሄ ሃሳቡን እንደመጣልኝ #ለተመድ እና #ለአውሮፓ ህብረት ላኩኝ። የተከበሩት ተቋማት አክብረው መልስ ሰጡኝ። ግን ምንም አክሽን የለም። 10 ፖስተር አሰርቼ መለጠፍ ፈለግሁኝ።    ግን ፕሮፌሽናሎች ቢሠሩት ብዬ አማከርኳቸው። ሽልንጉ እናቴ በምን አንጀቴ። ከዛ አንድ ቀን ዩቱብ ቻናል ከፈትኩኝ። እንዴት እንደሚሠራ አላውቅም። ባለሙያ እንዲያግዘኝ ጠዬኩኝ። ሲዊዝሻ ላይ ባለሙያ ውድ ሆነ። በቃ ዋናው የቃላት ፖስተር መሥራት ነው። እኔ ሳልፍ አንድ ቅን ሰው ዓለምን ሞግቶ ዕውን እንዲያደርገው ነበር ሃሳቡ። በቃ አዌርነስ መፍጠር። የፍቅር ተፈጥሮ ካሪክለም ተነድፎለት ልክ እንደ ማህበራዊ ሳይንስ እና የተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ትምርት ይሆን ዘንድ ነው ሙግቴ።    መነሻዬ አንድ ጀርመናዊ ወጣት #ታዋቂ ለመሆን ያሳፈራቸውን የጀርመን ዊንግ አውሮፕላን ተሳፋሪወች እሱ ፓይለት ነው ፈቅዶ ከተራራ ጋር ማጋጨት ነበር ህልሙ። አሳካ። ሙሉ 15 ቀን CNN (ሲኤንኤን) ላይ የሚገርም ሽፋን አገኜ። ልዕልት አንጌላ ሜርክል ጠቅላይ ሚር ነበሩ የጀርመን። ሰፊ ሃዘን ነበር። አውረፕላን ውስጥ የነበሩ ለልምድ ልውውጥ የሚጓዙ #ተማሪወች ነበሩ።    አስከሬናቸው ሲለቀም #አንሰፈሰፈኝ ። ዓይኔ ቅል ቅል እስኪያክል ድረስ አለቅሳለሁ። እንቅልፍ አጣሁኝ። ያን ጊዜ አውሮፓን በተለይ ፈረንሳይን የአክራሪነት ጦስ ይንጣ

የማንነትን ብዛት #መስፈር አይቻልም። ማንነት Homogeneous #አይደለም Heterogeneous ነው። በንግግር ጥበብ ፕረዘንቴሽንም ላይ ትልቅ ሮል ያላቸው ጉዳዮች ናቸው እነኝህ መንትዮሽ።

ምስል
  የማንነትን ብዛት #መስፈር አይቻልም። ማንነት Homogeneous #አይደለም Heterogeneous ነው። በንግግር ጥበብ ፕረዘንቴሽንም ላይ ትልቅ ሮል ያላቸው ጉዳዮች ናቸው እነኝህ መንትዮሽ። "አሁንም ልጆቼ ሆይ ስሙኝ፦ ከአፌም ቃል አትራቁ።" (መጽሐፈ ምሳሌ ፭ ቁጥር ፯ )   ማንነት አንድ ሰብ ወይንም አንድ ማህበረሰብ፤ ወይንም አንድ ዞግ በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ ወጥነት መኖራቸው ብቻ እድርገን ልንመለከት አይገባም። የአንድ እናት እና አባት ልጆች #በፆታቸው ተመሳሳይ ሆነው፤ አንድ ቤት #አንድገው ፤ አንድ ሰፈር #ኖረው ፤ አንድ ትምህርት ቤት #ተምረው ፤ አንድ #ሥልጠና ወስደው፤ አንድ ቢሮ እዬሰሩ አንድ ሊሆኑ ፈጽሞ አይችሉም። ዕይታቸው ምርጫቸው ርዕያቸው ግባቸው ወጥ ሊሆን ቀርቶ ሊመሳሰልም ላይችል ይችላል። የራስ እና የእግር አሻራ ልብ የበሉ። የተወለድንበት ዕለት፤ ሰዓት ቀናት እና ወቅታትም የራሳቸው ተጽዕኖ አላቸው።    ከአባት ዘር ወደኋላ ሲቆጠር፤ ከእናት ዘር ወደኋላ ሲቆጠርም በአንዱ የሚከሰት በሌላው የሌለ ሊሆን ይችላል። ትንሽ ለማብራራት የአግር እጣቶቼ አንገተ ደፋታ ናቸው። የአጎቴ የልጅልጅ ይህን ይዞ ተወልዷል። ለእሱ ፍቅሬ ደግሞ የተለዬ ነው። እኔ ስናፍቃቸው ያን እንደሚዩ ነግረውኛል። እኔ ተማሪ እያለሁ 11ኛም/12ኛም ክፍል በደረጃ ነው የፈፀምኩት። ምርጫዬ ባይወሎጂ እና ኬሚስቲሪ ነበር። አንዱ ምርጫዬ ህግ ሌላው ባይወለጅስት ሌላው አስትሮነመር ነበር። አሁን ያልኳችሁ የአጎቴ የልጅ ልጅ ባይወለጅስት ነው። (ዶር) ሌላው ፖለቲካል ሳይንስ ነው። ሁለቱም ከእኔ የተወሰነ ዝንባሌን ወርሰዋል ማለት ነው።   በሌላ በኩል ደግሞ አንዱንም የማይመስል ገጠመኝ ይኖራል። አብረን አድገን በኋላም ያደጉ ያሳድግኳቸው እህት እና ወንድ

ዓለማችን ህግን የማህበረሰቡ ዕውቀት እንዲሆን ልትሰራበት ይገባል።።

ምስል
  ዓለማችን ህግን የማህበረሰቡ ዕውቀት እንዲሆን ልትሰራበት ይገባል።። "የሰው ልጅ መንገድን ያዘጋጃል እግዚአብሄር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።" (ምሳሴ ፲፮ ቁጥር ፱)   ህግ ሥርዓት ነው። ሥርዓቱን የሚያስጠብበት ድንጋጌወች አሉ። አፈፃፀሙን የሚከታተሉም ተቋማት አሉ። የህግ ትምህርት ቤቶች፤ ኮሌጆች ዩንቨርስቲወችም አሉ። በወል ኮርስም ላይ ህግን ሊያስወስድ የሚችል አጋጣሚ ሊኖር ይችላል። ህግ መማር አንዱ ምኞቴ ነበር። ጥቂት ፅንሰ ሃሳቡን በነፃ ከሚያስተምሩ ወገኖች ለጠብታ ያህል ቀማምሻለሁ። በቤትም መሬትን ተጠንቅቃችሁ እርገጡ ከሚል ቤተሰብ ስላደኩኝ ሃይማኖታዊው ቀኖና ዶግማ ታክሎ ራስን ገዝቶ ለመኖር አግዞኛል ብዬ አስባለሁኝ። ይህ ማለት ግን መብቴን አውቄ ግዴታዬን ለመወጣት የሚያስችለኝ የህግ መሰረት አለኝ ማለት አይደለም። ኢትዮጵያ ማደግ በራሱ ይሉኝታ እራሱ የሚሰጠው በረከትም ቢኖርም። ዓለማችን ካልሠራችው የቤት ሥራ አንዱ ህገ ነክ ጉዳዮች የፕሮፊሽናል ሰወች ማድረጓ ይመስለኛል። ህግ የጥቂት ሙያተኞች ብቻ በመሆኑ ዓለማችን "በወንጀለኞች" ትቀጣለች። #ዓለማችን ፦ 1) የዬአገሮች ህጎች እና ዓለም ዓቀፍ የሰባዕዊ መብት ድንጋጌወችን የትምህርት ሥርዓት ካሪክለም ነድፋ ከመዋለ ህፃናት ጀምሮ እንደ እንዲማሩት ለሁሉም ልጆች ብትፈቅድ፦፦፦፦ 2) ማህበረሰቡ የዬአገሩን እና የዓለም ዓቀፍ የሰባዕዊ መብት ድንጋጌወችን ከቀበሌ ጀምሮ እንዲማረው፤ እንዲወያይበት ብታደርግ፦ 3) ዓለማችን በዬአገሮች ህገ መንግሥት ህግጋት እና በሰባዕዊ መብት ዓለማቀፍ ድንጋጌወች ላይ አጀንዳዋ ሆኖ ብትመክር፦ 4) ወንጀል ከመፈፀሙ በፊት ወደ ወንጀል ሊወስዱ የሚችሉ ማህበራዊ ቀውሶችን ማስታገሻ ላይ ቀድማ ብትሠራ፦ 5) ዓለማችን እራሱን የቻለ ህገ ነክ ድንጋጌ

#ጥበብ #ከእስር #ትፈታ።

ምስል
  #ጥበብ #ከእስር #ትፈታ ። "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   #ጥበብ የተሰማትን ያልተናገረች ማን ይናገር? #ጥበብ ያላፅናናች ማን ያፅናናና? #ጥበብ መከፋትን ያልገለፀች ማን ይግለፅ? ጥበብ እኮ #የሚሊዮን #ድምፅ #ናት ። ለመሆኑ ጥበብ ባትኖር ዓለም ምን ትመስል ነበር? ---- #ልሙጥ ? --- #ጠፍጣፋ ? ------- #ፋንጋ ? ልዝ? ---- #ጥውልግ ? ---- #ዳፍንታም ? ጥበብ ጨለማን #የምታበራ ፦ #ለፈጣሪያዋ #ያደረች ፤ በፈጣሪዋም #የተመረቀች ምስጉን - የዕውነት #ሐዋርያ ፤ የዕውነት #መልዕክተኛ ናት። #ፃድቅም ። ጥበብ ስትታሰር የተስፋ ዓይንም ይሰወራል። አፅናኝ መሪ ላጣችው ኢትዮጵያ፤ አይዟችሁ ባይ ሙሴ ለራባት ኢትዮጵያ ጥበብ አንደበቷ ተከፍቶ አይዟችሁ ብትል፦ ብታጽናና የድርሻዋን ብትወጣ ዛሬን በተስፋ ማሳደር ነገን በተስፋ ማስቀበል ይቻላል። በሌላ በኩል ትውልዱ ጥበብን እንዲፈራ፦ ፀጋውን እንዲሸሽ ማድረግም #ዳፍንታም ዘመን ዘመኑን ያደርጋል። #እሰቡበት ። #አማናችነን ፍቱት። ዕውነትን አትፍሩ። መድፈር ቢያቅታችሁ ዕውነትን ደፋሪወችን #ዘር #እዬቆጠራችሁ አታሳዱ። እኔ #ቅናትም ይመስለኛል። አሜሪካ ሲገባ #ካሊሙን ለብሶ ነበር - ተፈጥሯዊ የሆነ ሳተና። እዛው መቅረት ሲችል አገሬን እናቴን ብሎ ተመለሰ። ከዛ አሜሪካ ያያትን ቤቱ በር ላይ ሠርቶ መፀሐፍ ሼር የማድረግ ልምዱን ወስዶ በሩ ላይ ያችኑ ሠራ። ይህ #ቅን እንዴት ይታሠር? በሌላ በኩል በእረኛ ተፈጥሯዊ ትዕይንት የተመሰጡ ዕውቅና ሰጥተውታል። ያን ማሰር የሰማይን ፀጋ መበቀልም ይሆናል። ኮንፊደንስ የነሳው ሥርዓት ለራሱ አይበጀውም። ኮንፊደንስ ስለአጣችሁ እንጂ ሁለት ፍሬ ሥንኝ እንዲህ አያስበረግጋችሁም ነበር። በድንገት የታጡ አርቲስቶች የ