ኃራም መኖር ላይበር።

ኃራም መኖር ላይበር።
ከሥርጉተ©ሥላሴ  (Sergute©Sselassie)
21.03.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።)
„የሕልሙን ፍቺ አንዲሰጡኝ የባቢሎንን ጠቢባን ሁሉ ወደ እኔ ይገቡ ዘንድ አዘዝሁ።“
                                   (ትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ ፬ ከቁጥር ፮ እስከ ፯)
በመሆን ውስጥ ሳይኖር
በሳይኖር ውስጥ ሲኖር፣
በሲኖር ውስጥ ሳይኖር
በውስጥ ሳይኖር ሲኖር፤
ሳይኖር መኖር በማኖር
መኖር ሳይኖር ሲኖር?
በነፍስ መኖር ሲ‘ር
ብትን አፈር ሲመር፣
መኖር ሳይኖር ሲተረተር
ሲበረበር … ሲፈረፈር … ሲመረመር … ሲሸረሸር …
መኖር ሲታሰር በጭስ ግብር፣
የመኖር ቅበር ቀንበር
ሲሰረስር ሳይፈጠር?
እኮ! ምን ፍጠር?
ሲሰባበር በድርድር፣
ባርባር ባርባር …
ራም መኖር ላይበር።
·        ኖሩ ለተሰረዘ ለኢትዮጵያ ህዝብ በሙሉ ይሁንልኝ (21.03.2018.)


አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።