#ኮፒ ራይት የማይጠዬቅበት የተጋድሎ ዘርፍ የአማራ የማንነት እና የህልውና ተጋድሎ ብቻ ነው።

 

#ኮፒ ራይት የማይጠዬቅበት የተጋድሎ ዘርፍ የአማራ የማንነት እና የህልውና ተጋድሎ ብቻ ነው።
 

 
በሌላው ቤት ካለ ቤተኞቹ ማንም ዘውታ የለበትም። የአማራ ፖለቲካ ሁነኛ ባለቤት ስለለው ያገኜ ሲዳክርበት ውሎ ያድራል። #በሩ 24 ክፍት ነው። የአማራ #የትርታ ተጋድሎ በወጠነው ሁሉ ሁሉ አራጊ ፈጣሪ፣ አዛዥ ነዛዥ ነው።
ግንስ አንዳቸውም ከሞት መታደግ፣ ከመፈናቀል ማስቆም፣ ከመታረድ መታደግ አልተቻለም። የ40 ዓመቱ መከራ በአራት እጥፍ ተመንድጓል። ዘመናት መሠረት የያዙ ማናቸውም ትውፊት እና ትሩፋት አይሆኑ ሆኖ ከስሏል።
በዚህ ለመቀጠልም አልተፈቀደለም። የመስተዳድሩ ፕሬዚዳንት ዶር አብይ አህመድ በአዳዲስ ቀውሶች #የሚያርሱት አልበቃ ብሎ ሌላውም ተደርቦ ጥልቅ እያለ መከራውን በእጥፍ ድርብ ያነባብረዋል።
ትናንት ልዩ ኃይል ነበር ዛሬ #ፋኖዊነት። ነገ ደግሞ #ማናዊነት ይመጣ ይሆን? ሁሉም ነኝ ይላል።
ተግባር ላይ ያሉት ደግሞ ድምጣቸውን አጥፍተው ይተጋሉ። ሌላውወይ ሲወድቅ፣ ወይ ማህበራዊ መሰረቱ ሲሳሳ ሄዶ ይዶላል። እናም ዕዳ ከሜዳ ሆኖ ጠንቅ ሆኖ እንደ አርበኛ አስቻለው ደምሴ አደናው፣ እርሸናው፣ እስሩ እንግልቱ ቀጥሏል።
ከፋኖ እራስ መውረድ ያለበት ሁሉም ነው። ከሊቅ እስከ ደቂቅ። ፋኖ የዛሬው የፖለቲካ ድርጅት ሳይፈጠር የነበረ #የደም #ማህተም ነው። ሰው ሠራሽ አይደለም።
አላያችሁም ጎንደር ሀምሌ 5/ 2008 አብዮት ሲፈነዳ እነ ዋዋ አርበኛ ጎቤ ያን የመሰለ የተደላደለ ኑሯቸውን ትተው ሲደርሱለት። ያንጊዜ "ኢዜማ፣ ባልደራስ፣ አብን፣ "ብልፅግና፣" ህብር ወይንም ኢኃን" ነበሩን?
አሁን እነሆ ከፖለቲካ ድርጅት ጋር ወስደው ዘፍቀው ተው እያልኩ እዬተናገርኩኝ በግራ በቀኝ እዬታደነ ይገኛል። አዝናለሁኝ። እጅግ አድርጌም እምምምም ብዬ #አምጣለሁኝ
መቼ የአማራ ፖለቲካ እራሱን ችሎ #ኮፒራይቱ የማይደፈር ይሆን ዘንድ አላውቅም። ማነው በኦሮሞ ፖለቲካ፣ በትግራዋይ ፖለቲካ ከጫፋ ድርሽ የሚል። #ማንም
የአማራ ፖለቲካ ግን ያገኜ በፈለገው ሰዓት፣ በወደደው ወራት እንደ አሻው ይወራኝበታል። ያ ባልከፋ። የሚያሳዝነው ስበቡን ተከትሎ የሚመጣው ማትን መግታት አለመቻሉ ነው።
ለዛውም የአማራ ፖለቲካ #ወጥ #ማኒፌስቶ የለውም። ዓላማ እናግቡ አይታወቅም። ልቅ ነው። ሁነኛ የለውማ። ሲከፋኝ ብመለስ ተብሎ የተቀመጠ ማቆያ።
የዜግነት ነኝ የሚለውም ሌላው ማህበረሰብ አይደለም መነሻውም መድረሻውም ያው መከረኛው #አማራ ነው። ዜግነት በሌለበት አገር አማራ ብቻ ይህን እንዲሸከም ኢትዮጵያዊነትን ብቻ እንዲከበክብ ይገደዳል።
ባይባልም ቢባልምየተገራው የአማራ ህዝብ ልጆቹን የሚያሳድገው በሚስጢሩ ትርጓሜ ልክ ነው፣ ያውም ከበቃ ጨዋነት ጋር።
የሆነ ሆኖ አያልቅ ሥም እዬያዛችሁ እዬመጣችሁ አታባክኑት። ተውት! እባካችሁ ተውት። እባካችሁ ታቀቡ። መሬት እዬደበደባችሁ ማት አውርድለት ብላችሁ አትወኩት። እያሳደናችሁት፣ እያስጨረሳችሁት ነው።
ሰላሙን አውካችሁ ስጋት እና ውጥረት እምታነግሱበት እናንተው ፖለቲከኞች ናችሁ። 30 ዓመት ተሞክሮ በከሸፈ መከራ አሳሩን አታብሉት። ሁሉን ተቀምቶ፣ ሁሉንም ተነጥቆ ዛሬም አንተው ተማገድልን ከወንጀል በላይ ሃጢያት ነው።
ሞጣ የታመሰው የተቀጠቀጠው #በራስሰራሽ መከራ ነው። በኮፒራይት ሽሚያ ስትንደፋደፋ ህዝቡን አስጨረሳችሁት። ነገም ይቀጥላል። ሁሉም ተራውን እዬጠበቀ ነው።
የፋኖ መሪወች ብቻ ሳይሆን በአጋዥነት የሚጠረጠሩት ሁሉ ነገ ይጠበቅ። አንድ ተስፋ ቢኖር እሱንም ቀረመት ላይ ዋለ።
እግዚአብሄር ይስጥልኝ።
ሥርጉተ©ሥላሴ
Sergute©Selassie
17/03/2022
"አማራነት ይከበር!"
አማራነት ይለምልም!

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።