ልጥፎች

#ፕሮቶኮሉ እንደ ኢትዮጵያዊ አልተመቸኝም።

  #ፕሮቶኮሉ እንደ ኢትዮጵያዊ አልተመቸኝም።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።   “PM Abiy Appointed AU Champion for AI and Digital Health.” https://www.ena.et/web/eng/w/eng_8705845 https://www.youtube.com/watch?v=S0YCAlonH8c «ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአፍሪካ የAI እና ዲጂታል ጤና መሪ ሆነው ተመረጡ | PM Abiy Ahmed AU Champion |”   #የሹመቱ ፕሮቶኮሉ በፍጹም አልተመቸኝም። ኢትዮጵያ መመረጧ መልካም ነገር ነው። በዘርፋም ጥረት እንደ አለ እከታተላለሁኝ። ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድም በዲጅታል ደህንነት ላይ የሠሩ፤ ሙያውም ያላቸው ናቸው። ከፍ ያለም ዝንባሌ እንደ ነበራችው ቀደም ባለው ጊዜ አስተውል ነበር። እዚህ ደረጃ ሳይደርሱ እከታተል ነበር።    በተለይ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስተር ሳሉ። አንድ ብሄራዊ ውይይት አዘጋጅተው ነበር። " #ከእርምጃ ወደ ሩጫ" የሚል ሞቶ የነበረው። ይህን ዕርስ ወስደው ስለ አባይ ግድብ ውይይት ሲደረግም ያዬሁ ይመስለኛል። ባለቤቱ እሳቸው ናቸው እና በትምህርተ - ጥቅስ ማስገባት ይገባል። ሥንኙን መጠቀም የሚሹ ግለሰቦች ይሁኑ ሚዲያወች። እንዲህእንዲህ ዓይነት ሞቶ ዶክተር አብይ ይወዳሉ። "ከጎዳና ወደ ፓርላማም ብለውን" ነበር። ሂደቱ እራሱን የቻለ ፈተና ገጥሞታል።   የሆነ ሆኖ በዛ " ከእርምጃ ወደ ሩጫ" በጉባኤውም፤ ከዛም በኋላ በአገኙት የሚዲያ አጋጣሚ ሁሉ በዲጅታሉ ዘርፍ ዓለም ጥሎን እንዳይሄድ የቀረንበትን አስተካክለን አብረን መጓዝ የሚያስችል እርምጃ መውሰድ ካልቻልን፤ መጪው ጊዜ አብሮ ለመራመድ ይቸግረናል...

#ማስተዋል። ዘለግ ያለ ዕይታ ስለ ባለቅኔው ቴዲ አፍሮ።

ምስል
  • #ማስተዋል ።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።   #አሜን ።   እንዴት አድረን? እንደምንስ አረፈድን? ማስተዋል ተሰጥቶናል በጌታችን መዳህኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በአላህ፤ ያን እንጠቀምበት ዘንድ ፈጣሪ ይርዳን። አሜን።    "እዮሪካ" አልበምን። በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉውን ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ ቀን መድቤ አዳምጨዋለሁኝ። ሥንኞችን እየመላለስኩ አንብቤያቸዋለሁኝ። ሥራው ሐዋርያ ነው። ለሁላችንም ራዲዮሎጂ ነው። የምሥራቹ ደግሞ የኢትዮጵያ የሥነ - ጹሁፍ አቅም ከፍ አድርጎታል። ቋንቋወች ዘምነዋል። የቅንብር ሥልጣኔ በጉልህ ታውጆበታል። የህዝብ ፍቅር እናቀና ተሳትፎ ዘመንን አናግሯል። እያንዳንዳችን መርምሯል። የዳኜ ብቁ አቅም ነው።   #ትውስታ በምልሰት። ተያያዥ ጉዳዮች ዘለግ ብለው ይነሳሉ።    እኔ ሙዚቃ አድማጭ አይደለሁም። በልጅነት ጊዜዬ በአጋጣሚ ራዲዮ አቨይ አባቴ ያደምጥ ስለነበር ከዛ ጊዜ ወስጄ ያዳመጥኳቸው ከ10 አይበልጡም። እኔ እምሳበው በሥነ - ግጥሙ ይዘት ነው። ዛሬም በሙሉ ዕድሜዬ ይኽው ነኝ። ቤተሰቦቼ አብሶ ክብርት እናቴ ትወዳለች። ከእኛ ቤት በመደበኛ ሙዚቃ ይደመጣል። ቤተሰቡም ሙሉ ነፃነት አለው። እናቴ የአርቲስት ይሁኔ በላይ አድናቂ ናት። እኔ ደግሞ የመጸሐፍት ቀበኛ ሆኜ ነው ያደግኩት።   የሆነ ሆኖ ሚዲያወቼ በተፈጥሮ ዜማ ነው የምሰራቸው። በጸጋዬ ራዲዮ ሦስት ዓመት ቢሞላው ነው፤ ሙዚቃወቻችንም ይደመጡ ብዬ የፈቀድኩት። ይህም ሆኖ ኖቱ፤ ቅኝቱ፤ ቅላፄው፤ የላይኛው፤ የታችኛው የሚባለውን ጥበብ አላውቀውም።   ፍሬ ሃሳቡ የገባኝ፤ ስክርቢቱን ማግኜት ከቻልኩ በራዲዮ ዝግጅቴ አጫውተዋለሁ። ባመዛኙ በመሳሪያ ...

#የኔታ! ትንሽ ስለ ቴዲ አፍሮ።

  #የኔታ !   #ምዕራፍ ፲፱።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።    #የኔታ !   የቅኔ ~ ቃና ዕውነትን ~ ሊያቀና በማስተዋል ልቅና፤ ያበራል ---------- በልዕልና የምዕት ማሾ - ገ- ናና።   #የኔታ !   መምህር ~ የዝምታ የፊደል ቋሚ -----------የገበታ የውስጥነት - ይሁንታ የተሰጠህ - ከጌታ!   #የኔታ !   የፓን አፍሪካ ሁነኛ ዓውዳችን የእኛ - ለእኛ ምንግዜም አለኽልን - ለእኛ የሆንክልን የመታገስ -------- እረኛ የእምዬ የሃቋ መከታ ዘበኛ።   #የኔታ ።   የሰውኛ ልዩ ፍቅረኛ ተፈጥሮኛ የሆንክ ህሊነኛ የማዕዶት ሥህነ --------ቀመርኛ፤ አለኽልን የተደሞ ዳኛ የዕድምታ ቀና ማኛ።   #የኔታ !   የመቻቻል ቋሚ - በረኛ ለአብሮነት ታዛዥ - እሽተኛ ለኪዳንም ጽኑ ---------ቃልኛ፤ የቅንነት አዝመራ ሰብለኛ የብራ ሆይ! ዜመኛ።   #የኔታ !    የእኔ ድንግል ትጠብቅህ! አሜን። ሳቅህን - ታዝልቅልህ! አሜን። ጥረትህን - ታስብልልህ። አሜን። ጥላ ከለላ - ትሁንልህ። አሜን። እናትነቷን ትመግብህ። አሜን።   አሜን - ወ - አሜን ትንግርት ነህና - ለዘመን የጥበብ ዓውራ - የንብ፤ የብራና ሰንደቅ - ነባቢት የብዕር አደራ -------ትሁት፤ ሆነ እኮ! ----ር ትህ ችሎት - ኽ።    ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን።   ኑሩልኝ። አሜን።   እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።   ሥርጉተ©ሥላሴ። Sergite©Selassie. 29/04/026 21:45 ሲዊዘርላንድ ቢንተርቱር ከተማ።

#ለብልፄው ብርሃነ ትንሳኤው ምኑ ይሆን? አቶ ዩሱፍ ያሲን እና፤ ወይዘሮ ማህሌት ሰለሞን ሁለት የቴዲ አፍሮ የቅርቦች መታሰራቸውን ሰማሁኝ።

  #ለብልፄው ብርሃነ ትንሳኤው ምኑ ይሆን?   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   ምዕራፍ ፴፩።   ብልፄው ትንሳኤን አስመልክቶ የፖለቲካ እስረኞችን ከህሊና እስረኝነት ለቆ ይቆዬኛል ስል ተጨማሪ እስረኞችን አስሮ ነው ያገኜሁት። ከጥሞና ስመለስ። አዝኛለሁኝ። ሰሞነ ህማማት አልፎ ትንሳኤ በዳግም ህማማት??   በትንሳኤ እንደምን የሰው ልጅ ይታሰራል?    ትንሳኤ እኮ የኃጢያት ግድግዳ ተንዶ ብርኃን የታወጀበት የሐሤት ሰሞን ነው።    #እናት እንደዚህ ተይዛ ትታሠራለችን?   እናትነትን እንዲህ መቀጣጫ ማድረግ ይገባልን? ዕድሜስ - አይከበርንም? ሙያ መከበሩ፤ ጥበቃ ማድረጉ ቢቀር እንደምን እንደ ቀራንዮ ዕለት እንዲህ ያለ የግፍ አያያዝ ይፈጸማል? ይህ አክሰሱ ላላቸው አዲሱ ትውልድ ይበጃል ወይ?   #ለመሆኑ ?   ለመሆኑ ኢትዮጵያ ምን ያህል ታዳጊ ወጣት አላት? በዚህ አፈፃጸም ታዳጊ ልጆች የሥነ - ልቦና ስቃይ አይደርስባቸውምን?   " #የብሬ ቀን።"   ትናንት "የብሬ ቀን" ነበር ማለት ይቻላል። ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ከትምህርት ሚኒስተር ጋር ሆነው ለልጆቻችን እየሠሩ እንደሆነ ማብራሪያ ሲሰጡ ነበር። ምን ዋጋ አለው። ያን የትምህርት ሚኒስተር ድንቅ ጥረት እንዲህም ተናደ እኮ። ለዛውም 5 ሚሊወን የአማራ ህፃናት ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን #ቆዬን ብለን ወረፋ አስይዘን ማለት ነው።   ሰሞኑን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ "ወቼው ጉድ" ከሚባል ፖድ ካስት ጋር ረጅም ግን የማይሰለች መምህር ቃለ ምልልስ አድርገዋል። እሳቸው ስለተጠየቁ ነው ያዳመጥኩት። ከሚበልጡት ሰው በታች ሥር ሆነው መሥራትን መፍቀዳቸው የምመሰጥበት ክስተት ነው...