ልጥፎች
#ህም። #እምም። #የፈንጅ እና #የቦንብ አደጋ የሙዚቃ ኮንሰርት አይደለም። #ማን #ይፈጽመው ማን??
- አገናኝ አግኝ
- ፌስቡክ
- X
- ኢሜይል
- ሌሎች መተግበሪያዎች
#ህም ። #እምም ። #የፈንጅ እና #የቦንብ አደጋ የሙዚቃ ኮንሰርት አይደለም። #ማን #ይፈጽመው ማን?? "የቤትህ ቅናት በላኝ።" ማህበረ ቅንነት እንዴት አድራችሁ፦ አርፍዳችሁ ዋላችሁ። ትንሽ ቆራጣ ነገር ልል ወደድኩኝ። #የፈንጂ ፤ #የቦንብ #ፍንዳታ ምኑ ያስፈነድቃል። ይህ ካስፈነደቀ የትኛውም ዓይነት የሰማይ በረራ፤ የምድር ጉዞ በሚደርስ ድንገተኛ አደጋ የፌስታ ኢቬንት ቤተኛ መሆን ማለት ነው። እንዴት ብሎ ነው በጦርነት ማህል፤ በግጭት መሃል፤ የእሳት አደጋ፤ የፈንጅ አደጋ ድንገተኛ አስደንጋጭ ክስተቶች የሰውን ልጅ #ሲቀጥፍ ፤ የነዋሪውንም የአለምንም መኖር ሲያውክ፤ መኖር ሲስተጓጎል የህዝብ የኗሪው #የተረጋጋ መንፈሳቸውን ሲዘርፍ "ወሸኔ፤ ማለፊያ" ዜና የሚሆነው። ምነው ሰውነታችን ከላያችን ላይ እንዲህ #እንዲፋቅ ፈቀድን? ማን ይሁን ማን ይፈጽመው// በዬትኛውም አግባብ ይፈጸም፦ ምንም መሳሪያ ያልታጠቁ ንጹሃን መንገድ ላይ መቅረትን የሚነግር መርዶ #ፖለቲካ ተብሎ ሊቀርብ ፈጽሞ አይገባም። እራሱ የፈንጂ የቦንብ አደጋ ሞት ብቻ አይደለም። ዘመቻው #አካል #ይጎድላል ፤ ጦሪ የነበረው ተጧሪ ይሆናል። ስቃዩ፤ የሞራል ድቀቱ፤ የተስፋ ማጣት ስቃዩ #ተመን ይወጣለታልን???? ልጆችስ ተብትነው ሲቀሩ፤ ሰርክ #በስጋት ሲናጡ ይህ እንደ ሸበላ ገጠመኝ ሊታይ ይሆን? አዝናለሁኝ። በየትኛውም ሁኔታ የምናጣቸው ወገኖች ሃዘን አይበቃንም? ከእስር ቤት በድብደባ፤ ከሥራ መልስ በባሩድ፤ ያልተነገረው በስውር #በምግብ #ብክለት ፤ ስንት ወገን አጣን? ባልተገባ የመረጃ ፍሰት፤ ባልተጠና እና አቅምን ባልመጠነ #ኦፕሬሽን ቀንበጦቻችን አላጣነም። ...
እንዲህ እንደ ጨው ዘር መበተናችን እኮ ጥቃት ነው። እዛም መከራ ተሰዶም መከራ። ግን የተሻለ ዜና ነው። "በምያንማር የወንጀል ካምፖች ተይዘው የነበሩ 138 ኢትዮጵያውያን ተለቀቁ" BBC
- አገናኝ አግኝ
- ፌስቡክ
- X
- ኢሜይል
- ሌሎች መተግበሪያዎች
"በምያንማር የወንጀል ካምፖች ተይዘው የነበሩ 138 ኢትዮጵያውያን ተለቀቁ" https://www.bbc.com/amharic/articles/c805zvpjnlgo "ትናንት ከተለቀቁት የ19 ሀገራት ዜጎች መካከል ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት ኢትዮጵያውያን ናቸው" ከ 6 ሰአት በፊት "በምያንማር በሚገኙ የሳይበር ወንጀል ካምፖች በግዳጅ ሠራተኝነት ተይዘው የነበሩ 138 ኢትዮጵያውያን ተለቅቀው ወደ ታይላንድ መግባታቸውን በሀገሪቱ የሚገኝ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ምንጮች ለቢቢሲ አማርኛ ተናገሩ። የተለቀቁት ኢትዮጵያውያን ዜጎች ብዛት 138 እንደሆነ ለቢቢሲ ያረጋገጠው በሕንድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ፤ አስፈላጊው ሰነድ ተሟልቶላቸው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ እንደሚደረግ ገልጿል። በደቡብ ምሥራቅ እስያዋ ምያንማር ብዛት ያላቸው የሳይበር (የበይነ መረብ) ማጭበርበር የሚከናወንባቸው ካምፖች የሚገኙባት ሀገር ነች። በሀገሪቱ ውስጥ የሚገኙ ቢያንስ 154 ግቢዎች ውስጥ የሚፈጸሙት የማጭበርበር ወንጀሎች በአብዛኛው የሚከናወኑት "የሥራ ዕድል ታገኛላችሁ" በሚል ተታልለው በግዳጅ ለዚህ ድርጊት በተዳረጉ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ነው። ከእነዚህ ዜጎች መካከልም ታይላንድ ውስጥ ሥራ ታገኛታችሁ በሚል ተታልለው ወደ ምያንማር የተወሰዱ ኢትዮጵያውያን ይገኙበታል። የኢትዮጵያውያኑ ተጎጂዎች ወላጆች ኮሚቴ 300 ገደማ ኢትዮጵያውያንን ስም የመዘገበ ሲሆን፣ አጠቃላይ በተለያዩ ካምፖች ውስጥ የሚገኙ የሀገሪቱ ዜጎች ቁጥር "ሦስት ሺህ ይደርሳል" ተብሎ እንደሚገመት ከዚህ ቀደም ለቢቢሲ ተናግረው ነበር። ኢትዮጵያውያኑ መደብደብ እና በኤሌክትሪክ ሾክ መደረግን ጨምሮ የተለያዩ የማሰቃየት ቅጣቶች ይፈጸሙባቸዋል። የኢ...
"የሰው ልጅ ለአንድ ዓመት በማርስ ላይ መቆየት ምን ሊመስል ይችላል?" BBC
- አገናኝ አግኝ
- ፌስቡክ
- X
- ኢሜይል
- ሌሎች መተግበሪያዎች
https://www.bbc.com/amharic/articles/cp38kpn71n8o "የሰው ልጅ ለአንድ ዓመት በማርስ ላይ መቆየት ምን ሊመስል ይችላል?" ከ 3 ሰአት በፊት "ከጥቂት አስርት ዓመታት በፊት ወደ ቀይዋ ፕላሌት ማርስ የሚደረግ ጉዞን በልቦለድ ፊልሞች ብቻ የምንመለከተው ነገር ነበር። ዛሬ ላይ ቴክኖሎጂ ዘምኖ፤ የተመራማሪዎች እውቅት እና ፍላጎት ዳብሮ ወደ ማርስ የሚደረግ ጉዞ እውነት ሊሆን የሚችልበት ሁኔታ አለ። ለዚህም ቅድመ ዝግጅት በሚመመስል ሁኔታ የሰው ልጅ ወደ ማርስ ለመጓዝ ቢነሳ ረዥሙን ጉዞ እና ተስማሚ ባልሆነ ቦታ መኖርን ለማላመድ አራት ሰዎች በማርስ አምሳያ ወደተሠራ ቦታ ከዓመት በፊት ተልከው ነበር። ከአሜሪካ የሆኑት ኬሊ ሃስተን፣ ሮስ ባሮክዌል፣ ናታን ጆነሰ እና አንካ ሴላሪዬ የአንድ ዓመት የማርስ ቆይታቸው ምን ይመስል ነበር? የናሳ ሳይንቲስቶች በሂዩስተን ቴክሳስ በሚገኝ የጠፈር ምርምር ማዕከል ውስጥ ወደፊት ተመራማሪዎች ወደ ማርስ ሲጓዙ ሊገጥማቸው የሚችለውን እንዲሁም ኑሯቸው ምን ሊመስል እንደሚችል ለማሳየት የማርስን አምሳያ ፈጥረዋል። በማርስ አምሳያ ወደ ተሠራው ስፍራ የተላኩት አራት ተመራማሪዎች ለአንድ ዓመት ያክል በስፍራው ቆይተዋል። በዚህ ወቅት ተመራማሪዎች የአራቱን ግለሰቦች አካላዊ እና አእምሯዊ ጤና በቅርበት በመከታተል የተለያዩ ግዳጆችን እንዲፈጽሙ ያዟቸው ነበር። አራቱ ግለሰቦች ለመጨረሻ ጊዜ ሰማይ ከተመለከቱ ዓመት አልፏቸዋል። ከሚወዷቸው ወዳጅ ዘመዶችቻው ተለይተው 12 ወራቶችን አሳልፈዋል። ። ለ370 ቀናት ከተቀረው ዓለም ተገልለው በማርስ ሊኖር በሚችል ሁኔታ ውስጥ ቆይተዋል። ይህ ቆይታቸው ናሳ ካካሄዳቸው የጠረፍ ጉዞ ቅድመ ዝግጅቶች ረዥሙ ነው። የዚህ ጥናት ዋነኛ ዓ...
BBC "በአሜሪካ የኢሚግሬሽን ባለሥልጣን ቁጥጥር ስር የነበረው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ሕይወቱ አለፈ" አሳዛኝ ዕጣ።
- አገናኝ አግኝ
- ፌስቡክ
- X
- ኢሜይል
- ሌሎች መተግበሪያዎች
በአሜሪካ የኢሚግሬሽን ባለሥልጣን ቁጥጥር ስር የነበረው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ሕይወቱ አለፈ https://www.bbc.com/amharic/articles/cly7q2ee228o "ስደተኛው ተይዞ የቆየበት የኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ ባለስልጣን (አይስ) ኢሎይ የማቆያ ማዕከል" 12 የካቲት 2025 "በአሜሪካ የኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ ባለሥልጣን (አይስ) ቁጥጥር ስር የነበረ ሠራዊት ገዛኸኝ ደጀኔ የተባለ ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ሕይወቱ ማለፉ ተገለጸ። የ45 ዓመቱ ስደተኛ ፊኒክስ ግዛት በሚገኝ የባነር ዩኒቨርስቲ የህክምና ማዕከል ተኝቶ ህክምና ሲደረግለት እንደቆየ እና ጥር 21/2017 ዓ.ም. ዶክተሮች መሞቱን ማረጋገጣቸውን ባለሥልጣኑ ከቀና በፊት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ስደተኛው በህክምና ላይ የነበረ ቢሆንም ለሞት የዳረገው ትክክለኛ መንስዔ ምን እንደሆነ አለመታወቁን አንድ የህክምና ባለሙያ ሪፖርት አድርገዋል ተብሏል። ሠራዊት ከታኅሣሥ 14/2017 ዓ.ም. ጀምሮ በአሪዞና በሚገኙት ባነር ካሳ ግራንዴ የህክምና ማዕከል በኋላ ደግሞ በባነር ዩኒቨርስቲ የህክምና ማዕከል ተኝቶ ሲታከም እንደነበር በምህጻሩ አይስ ከተሰኘው የአሜሪካ ኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ ባለሥልጣን የተገኘው መረጃ ያስረዳል። እንደ አይስ ከሆነ ሠራዊት ወደ አሜሪካ የገባው ባለፈው ዓመት ነሐሴ 13/ 2016 ዓ.ም. በሉክቪል አሪዞና አቅራቢያ በኩል ነው። ወዲያውኑ በአሜሪካ የድንበር ጠባቂዎች ተይዞ በአስቸኳይ ከአገር እንዲወጣ የሚያዝ ማስጠንቀቂያ ሰጥተውት ነበር። ሠራዊት አሜሪካ ከገባ ከሁለት ቀናት በኋላ በአሜሪካ የኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ ባለሥልጣን (አይስ) ኢሎይ የማቆያ ማዕከል እንዲዛወር ተደረገ። ግለሰቡ መስከረም ወር ላይ በኢሚግሬሽን ችሎት ዳኛ ፊት ቀርቦ የ...
"የጭካኔ ግድያዎችን ለማስቆም ሰብዓዊነት ብቻ ይበቃል!" ሪፖርተር።
- አገናኝ አግኝ
- ፌስቡክ
- X
- ኢሜይል
- ሌሎች መተግበሪያዎች
"የጭካኔ ግድያዎችን ለማስቆም ሰብዓዊነት ብቻ ይበቃል!" February 9, 2025 https://www.ethiopianreporter.com/138164/ "ኢትዮጵያ ውስጥ በየትም ሥፍራ የሚፈጸሙ የጭካኔ ግድያዎችን፣ ማሰቃየቶችንና ነውረኛ ድርጊቶችን በጋራ ማውገዝና ማስቆም የሁሉም ዜጎች ኃላፊነት ሊሆን ይገባል፡፡ መንግሥት ሕግ የማክበርና የማስከበር ኃላፊነቱን በአግባቡ እየተወጣ በንፁኃን ላይ የጭካኔ ድርጊቶች እንዳይፈጸሙ፣ በተገዳዳሪነት የቆሙ ኃይሎችም የዘፈቀደ ዕርምጃዎችን እየወሰዱ ሰላማዊ ዜጎችን እንዳያጠቁ በአፅንኦት ማሳሰብ ተገቢ ነው፡፡ በመላ አገሪቱ አስተማማኝ ሰላም ሰፍኖ መረጋጋት እስኪፈጠር ድረስ፣ በተቻለ መጠን ንፁኃን የፖለቲካ ሒሳብ ማወራረጃ እንዳይሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ ይኖርበታል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ከሚለቀቁ ተንቀሳቃሽ ምሥሎችም ሆነ ከዓይን ምስክሮች መገንዘብ እንደሚቻለው፣ ጭካኔዎች ከመብዛታቸው የተነሳ እጅግ አስደንጋጭ ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡ በተፃራሪ ጎራ የተሠለፉ ኃይሎች ሕፃናት ከአዛውንት ሳይመርጡ የጭካኔ ግድያዎች ሲፈጽሙ፣ ችግሩን በአገርና በሕዝብ ላይ ሊደርስ ከሚችል አደጋ አኳያ ማገናዘብ ተገቢ ነው፡፡ ሰብዓዊነት የጎደላቸው የጭካኔ ድርጊቶች አገር እንደሚያፈርሱ መገንዘብ የግድ ይላል፡፡ በተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጸሙ ነውረኛና የጭካኔ ግድያዎችን ተባብሮ ማስቆም አለመቻል የሚያስከትለው መዘዝ ከባድ እንደሆነ መታወቅ አለበት፡፡ የዕለት እንጀራቸውን ለማግኘት ከሚማስኑ ባተሌዎች ጀምሮ፣ አገሪቱ በከፍተኛ ደረጃ አስተምራ ለወግ ማዕረግ ያበቃቻቸው ባለሙያዎች ድረስ በጭካኔ ሲገደሉ ማየት ያሳቅቃል፡፡ የአዋቂዎቹ አልበቃ ብሎ ለአቅመ አዳምና ሔ...
እህህህህ"በአሜሪካ የኢሚግሬሽን ባለሥልጣን ቁጥጥር ስር የነበረው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ሕይወቱ አለፈ" BBC
- አገናኝ አግኝ
- ፌስቡክ
- X
- ኢሜይል
- ሌሎች መተግበሪያዎች
"በአሜሪካ የኢሚግሬሽን ባለሥልጣን ቁጥጥር ስር የነበረው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ሕይወቱ አለፈ" https://www.bbc.com/amharic/articles/cly7q2ee228o ስደተኛው ተይዞ የቆየበት የኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ ባለስልጣን (አይስ) ኢሎይ የማቆያ ማዕከል ከ 9 ሰአት በፊት በአሜሪካ የኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ ባለሥልጣን (አይስ) ቁጥጥር ስር የነበረ ሠራዊት ገዛኸኝ ደጀኔ የተባለ ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ሕይወቱ ማለፉ ተገለጸ። የ45 ዓመቱ ስደተኛ ፊኒክስ ግዛት በሚገኝ የባነር ዩኒቨርስቲ የህክምና ማዕከል ተኝቶ ህክምና ሲደረግለት እንደቆየ እና ጥር 21/2017 ዓ.ም. ዶክተሮች መሞቱን ማረጋገጣቸውን ባለሥልጣኑ ከቀና በፊት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ስደተኛው በህክምና ላይ የነበረ ቢሆንም ለሞት የዳረገው ትክክለኛ መንስዔ ምን እንደሆነ አለመታወቁን አንድ የህክምና ባለሙያ ሪፖርት አድርገዋል ተብሏል። ሠራዊት ከታኅሣሥ 14/2017 ዓ.ም. ጀምሮ በአሪዞና በሚገኙት ባነር ካሳ ግራንዴ የህክምና ማዕከል በኋላ ደግሞ በባነር ዩኒቨርስቲ የህክምና ማዕከል ተኝቶ ሲታከም እንደነበር በምህጻሩ አይስ ከተሰኘው የአሜሪካ ኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ ባለሥልጣን የተገኘው መረጃ ያስረዳል። እንደ አይስ ከሆነ ሠራዊት ወደ አሜሪካ የገባው ባለፈው ዓመት ነሐሴ 13/ 2016 ዓ.ም. በሉክቪል አሪዞና አቅራቢያ በኩል ነው። ወዲያውኑ በአሜሪካ የድንበር ጠባቂዎች ተይዞ በአስቸኳይ ከአገር እንዲወጣ የሚያዝ ማስጠንቀቂያ ሰጥተውት ነበር። ሠራዊት አሜሪካ ከገባ ከሁለት ቀናት በኋላ በአሜሪካ የኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ ባለሥልጣን (አይስ) ኢሎይ የማቆያ ማዕከል እንዲዛወር ተደረገ። ግለሰቡ መስከረም ወር ላይ በኢሚግሬሽን ችሎት ...
Äthiopien heute. (Ethiopia Today)
- አገናኝ አግኝ
- ፌስቡክ
- X
- ኢሜይል
- ሌሎች መተግበሪያዎች
Äthiopien heute. (Ethiopia Today) • In meinem Land, Äthiopien, werden gebildete Amhara-Kinder getötet. • Millionen Amhara-Kindern wird Angst vor dem Lernen eingeflösst. • Mit anderen Worten: An der Amhara-Generation wird ein Völkermord an Wissen verübt. • Jeder Mensch mit einem Sinn für Menschlichkeit sollte uns helfen, dies zu stoppen. • Als ein Arzt brutal ermordet wurde; Auch die Gesundheit von Millionen Menschen wird gefährdet. Die Gesundheit wird in Äthiopien vernachlässigt. • In Äthiopien wird das Wissen vernichtet. • Volle sechs Jahre, Amhara-Studenten werden gefoltert und Amhara-Gelehrte werden verhaftet. Amhara-Gelehrte verstecken sich. • In Äthiopien wird die Weisheit getötet. Ich habe die Informationen beigefügt. Deshalb sollte jeder Mensch mit einem Sinn für Menschlichkeit uns helfen, diese Ungerechtigkeit zu stoppen. Meine Frage ist höflich und respektvoll. Die Mutter der Amhara-Kin...