ልጥፎች

ኢራንን #በእግረኛ ጦር ……… እና ተስፋው በስሱ።

ምስል
  ኢራንን #በእግረኛ ጦር ……… እና ተስፋው በስሱ።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       ስጋትን ለማስወግድ ቁልፋ በእግዚአብሄር በአላህ #መታመን ነው። 1) ኢራንን የሚሰጉ አገሮች አሉ። 2) አሜሪካንን የሚሰጉ አገሮች ይኖራሉ። 3) ራሺያን የሚሰጉ አገሮች አሉ። 4) እስራኤልን የሚሰጉ አገሮች አሉ። 5) እንደ ቃልኪዳን የጦር አቅም ኔቶንም የሚሰጉ አሉ። 6) ተስፋን የሰጠ፤ ተስፋችን የሚጠብቅ፤ ለተስፋችን ተፈፃሚነት እርግጠኛ የሚያደርግ አምላክን፤ አላህን ከውስጥ ማመን ቢቻል #ስጋቱ አቅም እንዳይኖረው አድርጎ የማክሸፍ ሥልጣነ ክህሎቱ #የእዮር ሊሆን ይገባል።   የሰው ልጅ በአምላኩ ካለው መታመን ይልቅ #ለፖለቲካ ፍላጎቱ #መታመን ስለሚያደላ እንሆ ትውልድ ሁልጊዜ #በጦርነት ጢስ እና #ጭንቅ ይታመሳል።    የሰው ልጅ #በመሸነፍ ውስጥ #ማሸነፍ መኖሩን ቢመረምር፤ በስክነት ስኬቱን ቢይ፤ ተሸንፎም ባለ ዕድል የመሆን አቅሙ ሊጎለብት ይችላል። በተለይ በጦርነት መሸነፍን ተቀብሎ የእግዚአብሄርን የአላህን ፍጡር መታደግ #የጽድቅ ጎዳናም ነው።    ይህም ብቻ አይደለም ይህ መርዛማ ኬሚካል ምድርን #ይበክላል ። ቀጣዩ ትውልድ በሙሉ የጤና ሁኔታ #ስለመፈጠሩም እርግጠኛ የሚደርግ ጭብጥ የለም። መሬትም #ተሰቃዬች ። አዝዕርትም #ፍዳቸውን አዩ። ተፈጥሮ ተሳቀቀ። እግዚአብሄርም አላህም #አለቀሰ ። #ኢራንን በእግረኛ ለመግጠም ባይሞከር ምርጫዬ ነው። ለምን?    #መስዋዕትነቱ የከፋ ስለሚሆን።    #እንዴት ? #የገዢ መሬት እና #የሙት መሬት ዕጣ።    1) የኢራን እግረኛ ዘገባወች እንደሚያመለክቱት...
ምስል
 
ምስል
 

"ከተማ #አፍርሰን እዬገነባን ነው።" (ዶር የትምጌታ አሥራት ከብልጽግና ፓርቲ።) አስደንጋጭ ክስተት ነው።

ምስል
  "ከተማ #አፍርሰን እዬገነባን ነው።" (ዶር የትምጌታ አሥራት ከብልጽግና ፓርቲ።) አስደንጋጭ ክስተት ነው።    ግን ለምን ከተሞች እንዲፈርሱ #ብልፄው ወሰነባቸው????   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       #የምዕራፍ ፲፰ የማጠናቀቂያ ዕድምታ።   https://www.youtube.com/watch?v=j9HL-v6Akjs «ለሚሊየኖች የቤት ጥያቄ ምላሻችሁ ምንድን ነው? ብልጭልጭ ፕሮጀክት ነው? - የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር በፋና መድረክ « #በቅድሚያ ።   ትናንት ላይፍ ላይ የምርጫ ተፎካካሪወች ክርክር ነበራቸው በፋና ቴሌቪዥን። ተጀምሮ እስኪጨረስ በጥሞና ተከታተልኩት። ትናንት የሰማሁት ግድፈት ይሆን ብዬ ደግሜም አዳመጥኩት። ኢዜማ ባደምጥኩት መድረክ ሁሉ ደረጃውን የጠበቀ ማብራሪያ ሰጥቷል። ብልጽግና አሳካሁ የሚላቸው ነገረ የከተማን #ምህንድስናን በሚመለከት በዩንቨርስቲ ደረጃ ጥናቱ በባለሙያ የተሠራ መሆኑን ሹክ ብለውናል የኢዜማው ርትዑ።   በተረፈ ውይይቱ ጥሩ ነበር። በተለይ መደምደሚያው ላይ በአራቱም ፓርቲወች ሴት ፖለቲከኞች የዕለቱን ውይይት ማሳረጊያ ሲያቀርቡ ትንሽ ኩራት ኩራት ብሎኛል። ሁለቱ ሥማቸው ትዕግሥት ነው።    የሆነ ሆኖ በህይወት እያለሁ የታገልኩበት፤ የሞገትኩበትን ፍሬ ነገር ስላዬሁ እግዚአብሄር አመስግኛለሁኝ። የኢትዮጵያ ዘላቂ መፍትሄ ሴት ጠቅላይ ሚኒስተር ኢትዮጵያ ሲኖራት ነው የሚል ከቀድሞ የቤተ - መጸሐፍት ባልደረባዬ ከወ/ሮ ባርባራ ጋር እንደ ተወያዬሁበትን አስታወስኩት።    ተመድን ጨምሮ ዓለም በሴቶች ብትመራ ገፆዋ ይናፍቀኛል። የሆነ ሆኖ በአራቱም የፖለቲካ ድርጅቶች ሴት የፖለቲካ ሊቃናት እንዲህ በእኩል ...

#ትዕግሥትን ፈታኙ ከመንግሥት ኮምንኬሽን የተሰጠ መግለጫ ትዝብቴ።

ምስል
  #ትዕግሥትን ፈታኙ ከመንግሥት ኮምንኬሽን የተሰጠ መግለጫ ትዝብቴ።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፰።                      #ጠብታ ።   ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ አሊ ወደ ሥልጣን ከመጡ ጀምሮ ሃሳቤን በምዕራፍ ከፋፍዬ ሳቀርብ ቆይቻለሁኝ። እሳቸው ድፍን ፰ ዓመታትን አሳለፋ፤ እኔ ደግሞ ፲፰ ምዕራፎችን አጠናቀቅኩኝ።   አንድ ሃሳብ ይቀረኛል። ዛሬ ምዕራፍ ፲፰ አጠናቅቃለሁኝ። መጪው ህማማት ነው። ማድመጥ። መጠሞን ያስፈልጋል። ከትንሳኤ በኋላ እንደ አማኑኤል ፈቃድ የጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አገዛዝ አብይዝም ፱ ዓመቱን አህዱ እንዳለው ሁሉ እኔም ፲፱ ምዕራፌን እጀምራለሁኝ።   ምዕራፍ ፲፰ የጨመተ፤ ያስተዋለ፤ ዘለግ ያሉ ዕይታወቼን ያጋራሁበት። በብሎጌም ከጠበቅኩት በላይ መነበብ የቻለ ጊዜ ነበረው። እርግጥ ነው በህይወት ውስጥ ያሉ ገጠመኞችን ትኩረት ለመስጠት አስቤ፤ ፖለቲካው ጊዜውን እየተሻማ በዛ ዘርፍ ብዙም አልሰራሁም።    ፖለቲካም የህይወት አካል ነውና በአገር ጉዳይ ያገባኛል ብሎ፤ ጉልበቱን፤ ሃሳቡን የሚያጋራ ሰብ የዜግነት ግዴታውን የፈቀደ፤ በመብቱም ያልቀለደ ነው ብዬ አስባለሁኝ።   ዝምታ ውበት ቢሆንም ከዘመኑ ሥጦታ ጋር ሳይገናኙ ዳር መቆም ህይወትን ሞናትነስ ያደርጋል እና ዘመናችን በሰጠን፤ እጅግ በተደራጄ፤ ቀልጣፋ እና ስልጡን ዘመን ሰጥ የሚዲያ ፎርማት ተጠቃሚ መሆን በእጅጉ አልፈላጊ ነው። እያንዳንዱ ሰውም ሰብዕናውን የሚገነባበት፤ የራሱን አሻራ የሚያስቀምጥ ነፃ እና ለታረመ አንደበት ብቁ የሆነ ዕድል ስለሆነ ተጠቃሚነቴ ይቀጥላል። ...