ይታረዳል ጎንደር።

ይታረዳል ጎንደር።

ከሥርጉተ - ሥላሴ 13.11.2017 (ሲዊዘርላንድ - ዙሪክ)
ዓይኑን የሚዘጋ ጠማማ አሳብን ያስባል፤ ከንፈሩን የሚነክስ ክፋትን ይፈጽማል።
                                                             (ምሳሌ ምዕራፍ ፲፮  ቁጥር “)


መታበይ ሲቀለብ - የፈርዖን ጣቪያው
የቸነፈር ቁርጠት -  የውሉ መኛው፤
ተከዜም ደንበሩ ተገሷል ሁነኛው፤
ንውፀት ሆነ ርስትሽ መከፋት ግድግዳው።
የተጋሩ እናት ደልደል በይ እና …
ተኚ እንደ ልማድሽ ልጆች አሉሽና …
ወልደሽ አሳድጊ ዓለም እፈሺና
ቀለብ ማቀበሉን ለጎንደር ሸኚና
ሐሤትን ቀድሽው - ድጠሽው ስብዕና።
እናትዓለም ጎንደር ወና ላይ ያለሽው
በባሩድ መቀቀል ታንም ያጣሽው
በሰቀቀን ኑሮ ምሳር የተጋትሽው፤
ዕንባሽ አላገ መች ደርሶ ከደጁ
ይሄው ይደመጣል - አሞ ዓዋጁ።
ገመዱ ተገምዶ ተከንድቶ ሳለ
መሬቱም እራደ ከውስጡ ከሰለ።
የትዕቢት ጭንቅላት ካለልኩ ሆኖ
ይቆላል ይፈጫል የሰው ደም ተከድኖ።
የ40 ዓመቱ ምጣድ ከሰሉ ይስቃል
የትውልድ ብርንዶ በዕለት ይቋደሳል፤
ነጭናጫውን ዘመን በሆዱ አምቆ
ያልፋልን ይጠብቅ በእምታ ደምቆ።
የወርቁ - የጨርቁ - የጉልበት  ሰርዴታ
የጥርጥር - ዋሽንቱ  የጥጋብ ዕንቢልታ።
በበቀል ተፈጭቶ በዘሩ ተቁላልቶ
ይታረዳል ጎንደር ልኳንዳ ተከፍቶ።
ለሆዱ ያደረ አብሮ እዬዘመረ
ትቢያ ያለብስሻል እዬመነዘረ።
የተጋሩ ሎሌ ማተቡን የበላ
ጥቃት ተንተርሶ ለከርሱ እያላ።
እናት ጡት አጥብታ እሱነቷን
እንዴት ይክዳታል በከፋኝ ለታ?
እንዴት ይረሳታል በጨቃት ለታ?
እንዴት ይተዋታል በጨለማ ለታ?
ናፍቆቴ ልበልሽ፤ ስስቴ ልበልሽ፤
መንፈሴ ልበልሽ፤ ልበልሽ እቴጌ ልበልሽ  --- ልበልሽ፤
እመቤት ልበልሽ፤ ህሊና ልበልሽ
ታቦቴ ነሽና በውስጥ ልሳለምሽ
የበሞቴ እናት ሙያ በልብ ነሽ።
·         ሥጦታ ----  ከቀደምቱ የክ/ሐገራት ርዕሰ ከተማ በድህነት፤ በጉስቁልና፤ በልጅ እርድ፤ በርስት አልቦነት
      ምነና/ትንና ላይ ለምትገኘው ጎንደር ይሁንልኝ። 13.11.2017 (ሲዊዘርላንድ - ዙሪክ።)


ካለ ከመንበሩ እግዜሩ ይስጥልኝ። መሸቢያ ጊዜ። 

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።