መች ይሆን ጸሐይሽ?

?እቴጌ ኢትዮጵያ መች ይሆን ጸሐይሽ?
                                         ሥርጉተ - ሥላሴ  17.11.2017 (ሲዊዘርላንድ - ዙሪክ ።)

„የኃጢአያተኞችም ወገናቸው እንደ ገለባ ክምር ነው። ፍፃሜያቸውም ለገሃነም ይሆናል።“
                                                    (መጸሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፳፩ ቁጥር ፱)
ጥ አሮጎ ይዞ ነፍስን ሲጎትተው
ቀኑ ተገትሮ ቁሞ ʼሚጠብቀው፣
ሌሊቱ ʼማይነጋው ጠር ተንትርሶ
በምሬት ተቀርፆ፤ በሀዘን ዳጉሶ።
እቴጌ ኢትዮጵያ መች ይሆን ሰናይሽ?
… እሜቴ ነፃነት እምትሳለምሽ?
የጠቡን ግድግዳ እመነዘረ
በኢትዮጵያ ጽናት እመነዘረ፤
የጭንቅላት ካንሰር ትግራይ ላይ ጎልቶ
ፍቅር ኮሰኮሰ ልዩነት ጎልብቶ።
እቴጌ ኢትዮጵያ መች ይሆን ሰናይሽ?
… እሜቴ ነፃነት እምትሳለምሽ?
እጅግ ተንጠራርቶ በቅጥ ተንቦልቡሎ
ትዕቢት በትምክህት ጉሮ ሸባ ብሎ፤
ጥጋብ አገር ፈቶ እላፊ ዘልዝሎ
ማግስትን አራቁቶ፤ ፉከራው ቀጠለ /// ኧረ ዘራፍ¡ ብሎ።
እቴጌ ኢትዮጵያ መች ይሆን ጸሐይሽ?
… እሜቴ ነፃነት እምትሳለምሽ?
ድቃቂ አሽዋ በስርንቅ ተሠርቶ
ሽርቱን ምናቡን በሰው ደም አርክቶ፤
በሳጥናዔል ግብር ህሊናው ተቶ፤
ይታማሳል ሐገር፤ ይቆላል // ይፈጫል በፈንድሻ ፈክቶ።
እቴጌ ኢትዮጵያ መች ይሆን ጸሐይሽ?
… እሜቴ ነፃነት እምትሳለምሽ?
ድርቀታማ ግራር በሟተት ተገምዶ
ዬቁልቋሉ ስሪት መኖርን ጎራርዶ፣
ማህበረ ሳዖል የሰው ጭራቅ ዘንዶ፤
ትውልዱን አጨደው በጭካኔ ጎም
እቴጌ ኢትዮጵያ መች ይሆን እልፈትሽ?
… እሜቴ ነፃነት እምትሳለምሽ?
ታምሃል ይሉሃል „ጊዜ“ ታጥራለኽ፣
„ነገስ“ ትሆናለኽ? ምሰህ ትምጣለኽ?
በስትያስ“ ታስባለኽ? እንዴት ትሆናለኽ?
በዛሬ ውስጥ አልቀህ፤ በጭካኔ ወልቀኽ።
እቴጌ ኢትዮጵያ መች ይሆን እልፈትሽ?
… እሜቴ ነፃነት እምትሳለምሽ?
የግራዚያኒ ማገር ትግራይ ላይ ቆ
ተበጠሰ ማተብ ፋሽስት ቀድሶ።
ልብ የት ተፈጣረ? ለመሆኑ አለ?
የቅብጥርስ ጭቃሾኽ ገለባ እያለ።
እቴጌ ኢትዮጵያ መች ይሆን ማግሥትሽ?
… እሜቴ ነፃነት እምትሳለምሽ?
ሙሶሎኒ ልቡ ደም እንደ ጎረሰ
ቅሪቱን አውርሶ በሥሙ ነከሰ፤
በክብር ዘመነ ትውፊት ከሰከሰ
ዘመኑ ጠንዝሎ „ማረን“ ተከለሰ።
እቴጌ ኢትዮጵያ መች ይሆን ማግስትሽ?
እሜቴ ነፃነት እምትሳለምሽ?
ማህበረ - እርኩም፣ እረቂቅ ምስጣምስጥ ከፍሬ ተዳቅሎ
አነዛት እሷን ውስጧነን ቀቅሎ፤
በማይጠፋ ነዲድ ሰብዕናን አክስሎ
ዐነባ ተፈጥሮ ድንኳኑ ተጓጉሎ።
እቴጌ ኢትዮጵያ መች ይሆን ትንግርትሽ?
?… እሜቴ ነፃነት እምትሳለምሽ?

·         ሥጦታ - ለኢትዮጵያ ዕንባ ይሁንልኝ። ተጣፈ 15.11.2017 (ዙሪክ - ሲዊዘርላንድ)
·         አንድ ለመንገድ - የልቤ አንተነህ የሆነ ጹሑፍ ሳተናው ላይ ስላገኘሁ የኔዎቹ ትታደሙበት ዘንድ በትህትና
     እና በልዑቅ አክብሮት እንሆ
„ጎንደር የተጠራው የወያኔ የማጭበርበሪያ ጉባኤ፥ ዶሮን ሲደልሏት በመጫኛ ጣሏት ነውጥሩነህ ይርጋ“
ምን „የማጨበርበሪያ“ ብቻ የማህበረ - ሽፍቶች፤ የማህበር - ሌቦች፤ የማህበረ - ዘራፊዎች፤ የማህበረ - ገዳዮች፤ የማህበረ - ሳዖሎች የማህበረ - ጥጋበኞች፤ የማህበረ - እርኩሞች፤ የማህበረ - ጃርቶች፤ የማህበረ - ወራሪዎች እንጦርጦስ እንጂ ///


አዶናይ ከመንበሩ ካለ - እግዚአብሄር ይስጥልኝ። መሸቢያ ጊዜ።

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።