ልጥፎች

• ለፓን አፍሪካኒዝም #አጀንዳ መጋቢ ቁም ነገር። ለዓለም የጠይማን ዕንቁወችም አጤ #ተስፋን ዘለግ አድርጎ ይመግባል። "#ምህረትህ ከሰማያት በላይ ታላቅ ናት።" (መዝሙር ፻፰፤፬።)

ምስል
  • ለፓን አፍሪካኒዝም #አጀንዳ መጋቢ ቁም ነገር። ለዓለም የጠይማን ዕንቁወችም አጤ #ተስፋን ዘለግ አድርጎ ይመግባል። " #ምህረትህ ከሰማያት በላይ ታላቅ ናት።" (መዝሙር ፻፰፤፬።)   «የአፍሪካ እና የካሪቢያን አገራት በጥቁሮች ላይ ለተፈጸመው የባሪያ ንግድ ይፋዊ ይቅርታ እና ካሳ ጠየቁ» BBC. https://www.bbc.com/amharic/articles/cd6eg440px0o   ምዕራፍ ፲፱።   #ጠብታ ። እንዴት ነን ቤተ - ሥርጉትሻ? እኮ እንዴትስ አረፈድን? ዛሬ ውሽክ ብሏል። ልዕልቲቱ ነጋ አልነጋ ብላ ስትንቆራጠጥ ቆያይታ ወገግን ስታበስር #ፏ ብላ ነበር። ዝማሬው የወፎቹ ቀልጧል። ፏፏቴ ቢኖር እንዴት ያምራል መሰላችሁ። ጠሐይቱ የተስፋ ስንቅ ናት። ዜናውን መሠረት አድርጌ ተያያዥ ጉዳዮችን ለማንሳት ፈቀድሁኝ።    #ይህ ዜና ጠይም ዕንቁውያንን ቀና ያደርጋል።    ሽልንጓ የጎረባበጠቻቸው ፈረንሳውያን እና እንግሊዞች ደግሞ ቼክ አያስፈልግም ባዮች ናቸው። ያልተሰላ ረቂቅ ጉዳይ ተዜናው አስኳል አየሁበት ጭብጡን ሳዬው።    የመዋለ መንፈስን ልዩ የጠይማን ተሰጥዖን፤ ሥልጡን አቅምን ጠይማዊ ዊዝደም እና የቅኝ ገዢወች ሥልጣኔ ምንጭነት ተብራርቶ አልተነሳም ከጭብጡ እንደተረዳሁት። በዚህ ዘርፍ ኢትዮጵያ አለችበት። ዊዝደም በማዋጣት፤ መኖርን በማሰልጠን፤ አብሮነትን ተቋማዊ አድርጎ በመቀደስ። ምንም እንኳን ባርነቱ #ባይነካካትም ።    ለነገሩ ባርነት ተቀምሶ ቢሆን ኖሮ የተለጠጠው፤ ልቅ የሆነው፤ #ባሊህ ባይ ያጣው የቀደምትን ዊዝደም የማጣጣል፤ የመንቀል፤ የመቅደድ እና የማቃጠል ዘመቻ በተከታታይ ባልተካሄደ ነበር። የአማራ ህዝብ ሃጢያቱ ይሁን ኩነኔው እኮ ለባር...

በአውሮፓ #ህብረት በጀርመነኛ እና በእንግሊዘኛ ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና ስለ አማራ፤ የቀረበ መግለጫ #በዋርካው ሊቀ ሊቃውንት የቀረበ ነው።

  • በአውሮፓ #ህብረት በጀርመነኛ እና በእንግሊዘኛ ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና ስለ አማራ፤ የቀረበ መግለጫ #በዋርካው ሊቀ ሊቃውንት የቀረበ ነው።   “A remark on the systematic persecution of Orthodox and Amhara.”    "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ። "   ክቡር ልዑል አስፋውወሰን አሥራተ ካሳ ናቸው አቅራቢው። ባለመታደል ሆነ እንጂ በመጀመሪያ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ ወደ ሥልጣን ሲመጡ #በአወንታዊ በአክብሮት ከተቀበሏቸው ሊቀ - ሊቃውንት ውስጥ አንዱ ነበሩ። በወቅቱ #ጽፌበታለሁኝ ። ብሎጌ ላይ ይገኛል። ቆጥቤ፤ መስጥሬ የያዝኳቸው ናቸው። #ኢትዮጵያና #ኢትዮጵያዊነትን በሚመለከት #ዋርካ ናቸው። ጥግም መከታም ናቸው። ትውልዱ እናቱን #ውስጡ እንዲያደርግ ጥረት ያደርጋሉ።    ክቡርነታቸው መሆናቸውን እራሱ ልለያቸው አልቻልኩም። በድምፃቸው ነው የለየኋቸው። በጣም ተለውጠዋል። #ጀርመንኛቸው #የማይጠገብ ነው #አክሰንቱ የአፃፃፍ አወቃቀሩ፤ ቃናው ሳቢ ነው። ለመረዳት ግን ሥነ - ጹሁፋዊ ስለሆነ እጅግ ከባድ ነው። በጀርመንኛ መጽሐፍም አላቸው። ጀርመኖች ሰው ማክበር ባህላቸው ስለሆነ #ልቀታቸውን በታላቅ ትህትና ያስተናግዱታል።   ቁጥቧ እምዬ #ሲዊዘርላንድም ታከብራቸዋለች። ጋብዛም ፕረዘንቴሽናቸውን #ታጣጥማለች ። በብዙ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ በክብር እንግድነት ተገኝተው የመክፈቻ #ንግግር ያደርጋሉ።የራሳቸውም #ተቋም ነበራቸው። ዓለም ዓቀፍ የኢትዮጵያ #ወዳጆች የሚገኙበት። ለሰማዕታት ቤተሰቦች መጽናናትን ይለግሳል።    በዘንድሮ ምርጫ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የፖለቲካ ውክልናዋ በአማራ ክልል ብቻ ነው። ይህ...

#እርፍ። እልልልልል……… የዓመቱ ብርቅ ዜና። ተመስገን። «አሜሪካ #በህወሓት #መሪዎች እና ቤተሰቦቻቸው ላይ #የቪዛ #ማዕቀብ ጣለች»

ምስል
  • #እርፍ ። እልልልልል……… የዓመቱ ብርቅ ዜና። ተመስገን።   • «አሜሪካ #በህወሓት #መሪዎች እና ቤተሰቦቻቸው ላይ #የቪዛ #ማዕቀብ ጣለች»   https://www.bbc.com/amharic/articles/cy4ek8z92z3o   "አቤቱ ንጹህ ልብን ፍጠርልኝ፤ የቀናውን መንፈስ በውስጤ አድስ።"   (መዝ ፶፩፤፲።)   ይህ #ሰማያዊ #ስጦታ ነው። የፈጣሪም ሥራ ገሃድ የሆነበት ዕንቁ ዜና። #የእናትነት ዕንባ #አፈራ ። በየቀኑ የህወሃት ዕውቅና ብሪፊንግ በነጩ ቤተ - መንግሥት ቀርቶ እዚህ ተደረሰ። ተመስገን ነው። ለዚህም ነው የዘመኑን የፖለቲካ ባህሬ ዕወቁት ስል የባጀሁት። ዓለም እንደ ትናንትናው #አትቀጥልም ። ዘመን በሂደት ውስጥ በዚህ መልክም ባህሬውን ይከሰታል። ለህወሃት ይህ ውሳኔ #አፍ ያለው መቃብር ነው። ተስፋቸውን ቅርጥምጥም አድርጎ መቅኖውን ፍስስ የሚያደርግ።    ለቀኑ ቀን ሲሰጠው #አናርኪዝም እንዲህ #ያሟሟል ። ከህግ በላይነት ትርፋ #የተመለመለ ግንድነት ነው። "ወጣቶች ተውን፤ እንኑሩበት፤ እናግባ እንውለድ። አወን #ፈሪ ትውልድ ነን። ተውን አሉ ዕንባ እየተናነቃቸው ተማጽነዋል። እናቶች ትቢያ ለብሰው አፈር ለአፈር ተንበርክከው ለምነዋል። #ሰሚ ጠፋ። ኮንፊደንስ #ጣሪያ ነካ። ተለጠጠ። ግን ሟሸሸ።   አሁን ኢትዮጵያም #ወህ ትላለች። ተመስገን። ሁልጊዜ ማመስ፤ ማወክ። እሽ አይዋ #ጥምዶስ ምን ታስብ ይሆን???? የህወሃት የዲፕሎማሲ አቅም እንዲህ ቅስሙ እንኩት ሲል??? በዝልቀት እሰቡት።   ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን። ኑሩልኝ ማህበረ - ቅንነት። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።   ሥር...

መጥኒ ለእናታዊነት።

ምስል
  መጥኒ ለእናታዊነት።   • ዘገባው የBBC ነው።   "በትግራይ ከሥራ ቦታ፣ ከመንገድ እና ከመኖሪያ ቤት እየተካሄደው ያለው አፈሳ የፈጠረው ስጋት"   https://www.bbc.com/amharic/articles/c3vywvgnv2qo «የትግራይ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ በትግራይ "የተመለመሉ" ወጣቶችን ለሠራዊት እያሰለጠነ መሆኑን ለቢቢሲ ትግርኛ ገልጾ የምልመላው ሂደት ግን "በክልሉ መንግሥት እንደሚፈፀም" ተናግሯል።   ቢቢሲ ያነጋገራቸው በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ ወጣቶች ከሥራ ቦታቸው፣ ከመዝናኛ ስፍራ እንዲሁም ከሕዝብ ትራንስፖርት ላይ በግዳጅ ተወስደው ወደ ተለያዩ ካምፖች መላካቸውን ተናግረዋል።   ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች ኢትዮጵያ በበኩሉ የትግራይ ፀጥታ ኃይሎች በክልሉ መጠነ ሠፊ አፈሳ እና የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ እያካሄደ መሆናቸውን በመጥቀስ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።   የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጊቶቹ ይፈጸምባቸዋል በሚል ከዘረዘራቸው አካባቢዎች መካከል፣ ሰሜን ምሥራቅ ዞን፣ ማዕከላዊ ዞን እና ምሥራቃዊ ዞን ይገኙበታል።   ለሁለት ዓመታት የተካሄደውን ጦርነት ባስቆመው የፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት የተቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር በማፍረስ ከጦርነቱ በፊት የነበረው የክልሉ ምክር ቤት ሥልጣን ከያዘ በኋላ በህወሓት መሪዎች እና በፌደራል መንግሥቱ መካከል ውጥረት ተፈጥሯል።   ተመልሶ ሥራ የጀመረው ፈርሶ የነበረው የትግራይ ክልል ምክር ቤት ሕጋዊ የፓርቲ ዕውቅናው የተሰረዘበትን የህወሓት ሊቀመንበር ደብረፂዮን ገብረ ሚካኤልን የክልሉ ፕሬዝዳንት አድርጎ የሾመ ሲሆን፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ያሉበት ሁኔታ አስካሁን በይፋ አይታወቅም።   በዚህም የተነሳ በክልሉ ሌላ ...