አድራሻ አድራሽ።
• አድራሻ አድራሽ። «ለቁጣ የዘገየ ፍቅሩም የበዛ ነው።" እግዚአብሄር ለቊጣ የዘገየ፤ ፍቅሩሩ የበዛ፤ ኃጢያትን እና ዐመፃን ይቅር የሚል ነው። (ዘኁልቊ ፲፬፤፰።) 1) አድራሻ #ጠብቆ ሲነበብ። የሃሳብ ዓላማ እና ግብ መዳረሻ፤ የቦታ መለያም። 2) አድራሽ #ላልቶ ሲነበበ አቀባይ፤ ፖስተኛ፤ መልዕክተኛ። «ፕሬዝዳንት ትራምፕ የሕዳሴው ግድብ ጉዳይን "ቅድሚያ ሰጥተው" እንደሚመለከቱት ተናገሩ» ዘገባው የBBC ነው። ኢትዮጵያ አለመጋበዟ ይጎረብጣል። ለምን ስለምንን ያነሳሳል። #ምዕራፍ ፲፱። ኢትዮጵያ የመንፈስም፤ የፓን አፍሪካኒዝምም አዳራሽ አድራሽም ናት። በG7 ጉባኤ ላይ ያውም #ፈረንሳይ ላይ በተካሄደ ዕድሉን አለማግኜቷ ከተሟጋች አንፃር ሳይሆን እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሁኔታው ሊያሳዝነን ይገባል። የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት እና ጠቅላይ ሚር አብይ የቀረበ ግንኙነት እንዳላቸው አያለሁና። የኢትዮጵያ የመንፈስ ልቅእና በልዕልና ያላት፤ ቀደምትነት፤ የአፍሪካ አንድነት እና በተመድ ምስረታ ላይ ያላት የሙሉዑነት ተሳትፎ፤ በነፃነት ዙሪያም ያለት ብቃት እና ክህሎት ዘመን #ሊጠቀጥቀው የማይገባ ዕንቁ ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያ የቀደመ ሥልጣኔዋ "ምን አላት እና ለካሪክለም የሚያበቃት" የሚል #የዛለ መንፈስ እንዳለ ባውቅም፤ ኢትዮጵያዊነት ግን ሊማሩት የሚገባ የዕውቀት ዘርፍ መሆን የሚችል የልቀት ማዕከል ነው። ከዚህ አንፃር የግብጽ እና የኬኒያ ውክልና የአፍሪካን አህጉራዊ አቅም የሚፈትን ገጠመኝ ነው ብዬ አስባለሁኝ። ኬኒያም ይሁን ግብጽ መወከላቸው እንዳለም ሆኖ፤ ኢትዮጵያን አግልሎ መነሳት ግን ትክክል ነው ብዬ እኔ በግሌ ...