ዓለም እና #ዛሬወነገ። የዓለማችን ፖለቲካ #ኢንፍሌሽን (ግሽፈት) እንደገጠመው ይሰማኛል።
ዓለም እና #ዛሬወነገ ። የዓለማችን ፖለቲካ #ኢንፍሌሽን (ግሽፈት) እንደገጠመው ይሰማኛል። ስለሆነም ዓለማችን በጠና ታማለች። አይዞሽ ባይ #አጽናኝ መንፈስ ትሻለች። #አናርኪዝምም ያስፈራኛል። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። #ምዕራፍ ፲፰ በርከት ያሉ ዕርዕሰ ጉዳዮች በአንድ የወግ ገበታ። ዓለም የመረጠችው ጎዳና በሁሉም ዘርፍ ጭንቅ ሆኗል። ጫናም በዝቶባታል። በሌላ በኩል የዓለማችን ፖለቲካ ኢንፍሌንሽን የገጠመው ይመስለኛል። በዘመኑ የፖለቲካ ባህሪ አንፃር ሳስተውለው ካፒታሊዝም እድገቱን ጨርሶ ወደ #ኢንፕሪያሊዝም እያማተረ ይመስለኛል። ስለሆነም የፖለቲካ ሊቃናት ሰራሽ ችግሮች የተሻለ ዕድል ያገኙ ይመስለኛል። የህዝብ የመወሰን አቅም ደግሞ ፈተና ላይ የወደቀ ይመስለኛል። ይመስለኛል እምለው ጥናታዊ መረጃዊ ሁነትን ስለአላካሄድኩ ነው። በዚህ ዙሪያ የሁሉም የሃይማኖት ተቋማት አቨው የዓለማችን የመኖር ቀጣይነት በሚመለከት አጀንዳቸው አድርገው ስለ ዓለማችን የጸሎት ቀናትን ወስነው ሊተጉ የሚገባ ይመስለኛል። ዓለም ሃዘን ላይ ናት። አጽናኝ መንፈስ ትሻለች - ና። በሁሉም ቦታ #ስጋት አለ። በሁሉም ቦታ የሰው ልጅን የሰው ልጅ ይገድለዋል። #ጭካኔ መለያ #ማልያ የመሆን ዝንባሌም አለ። በሁሉም ቦታ #የታመቀ ጭንቀት አለ። በሁሉም ቦታ አስፈሪው የጦርነት ሁነት አድማጭ አግኝቶ ገኖ ይታያል። ጦርነት ተፈጥሮ ሰራሽ አይደለም። ጦርነት ፖለቲካ ሰራሽ ቀመር ነው። ፖለቲካ ደግሞ የሰው ልጅ የሚፈላሰፍበት አንኳር የዕውቀት ዘርፍ ነው። ስለሆነም ጦርነትን የሚያነሳሱ፤ የሚገፋፉ፤ የሚያበረታቱ ሁነቶችን መግታት ፖለቲከኞች ይችላሉ። ግን ፈቃዳቸው እንብ...