ልጥፎች

ወርሃ የካቲት ለእኔ የቅኔው ልዑል፤ #ፓን አፍሪካኒስቱ የብላቴው ጸጋዬ ገ/ መንፈስ የሚከብርበት ዓውዴ ነው። ለእኔ ጸጋዬዚም + ኢትዮጵያኒዝም + አፍሪካኒዝም= #የዕውቀት ዘርፍ ነው ብዬ አምናለሁኝ።

ምስል
  ወርሃ የካቲት ለእኔ የቅኔው ልዑል፤ #ፓን አፍሪካኒስቱ የብላቴው ጸጋዬ ገ/ መንፈስ የሚከብርበት ዓውዴ ነው። ለእኔ ጸጋዬዚም + ኢትዮጵያኒዝም + አፍሪካኒዝም= #የዕውቀት ዘርፍ ነው ብዬ አምናለሁኝ።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።        #ምዕራፍ ፲፰    #እፍታ ።   ክብሮቼ ማዕረጎቼም ቤተ ሥርጉትሻ ቅኖች ሆይ! ዛሬ የ፲፰ ዓመት መንፈሰ ጸጋዬ ጉዞዬ በምዕራፍ ፲፰ቱ የአጤ ፌስቡክ ማዕዴ ዘለግ ብሎ ይቀመራል። እኔ ወደ ብላቴው አቀናሁ ወይንስ እሱ ወደ እኔ መጣ። ቅኔውን ለባለቅኔወች፤ ዕድምታውን ለዕድምታ ባለሙያ ሊቀ - ሊቃውንታት ልተወው።    ብላቴ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንን በሚመለከት ለሙሉ ፲፰ ዓመታት የተጋሁበት፤ የተከሰስኩበት፤ ብዙ ፈተና ያስተናገድኩበት፤ ብዙም የተንገላታሁበት፤ የተገለልኩበት፤ ባን በሉት ብሎክ በእኔ ላይ ፈርሰስ ብለው ወክ እንዲህ ያሉበት፤ የተንበሸበሹበትም በኽረ ጉዳዬ ነው። በፓልቶክ በሉት፤ በድህረ ገጽ፤ አሁን አዲስ ገብ በሆነው የሚዲያ ዕድል ዩቱብም ሳይቀር #ፋክክሩ ለወረት ይደራል፤ የዘለቀ ግን የለም። ለምን? #በድንግልና የተወጠነ ስለማይሆን። አንድን የዕውቀት ዘርፍ ሊያዘልቅ የሚችለው የውስጥ #ቅንነት እና ንጽህና ብቻ ነው።    የጸጋዬ ድህረ ገጽ ነበረኝ። በቦርድ ነበር የሚመራው። የልጆች ፕሮግራም ለመጀመሪያ ጊዜ የነበረው ድህረ ገጽ ነበር። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ተገዢነት፤ ተጠቅላይነትን ይሻ ስለነበር አሻም በማለቴ ቦርዱ ተበተነ። ግን ብቻዬን እኩል የጀመርኩት የጸጋዬ ራዲዮ ስለነበር። ያ ቀጠለ። የመጀመሪያው ፕሮግራም ሲደመጥ ነበር በአክራሪ ኦሮሞነት እና በአክራሪ ኦርቶዶክስነት የተከሰ...

#ነገረ #ራያ።

  #ነገረ #ራያ ።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፰   ወደ 60 ሺህ የሚጠጉ ራያወች በህወሃት ምክንያት ከመኖሪያቸው ተፈናቅለው እዬተንገላቱ ስለመሆኑ ቢቢሲ የአማርኛው ዘገባ መረጃውን ሰጥቷል። ለእነኝህ ተፈናቃዮች ሁነኛ #ባለቤት የተገኜ አይመስልም። እርዳታ የሚያደርግላቸውም አላገኙም። በውነቱ #ባለቤትም ያገኙ አይመስልም።    ሚኒስተር በለጠ ሞላ ምን ያስባሉ (ዶር)???? ሃይቅ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ የሚኒስተሩን ሥም አጉልተው ሲያነሱ የሚያስደስት ከሆነ ኃላፊነትን በቀጥታ በሚመለከት ጉዳይ ፋይዳ ያለው ተግባር ተፈጽሞ ቢሆን መልካም ነው። መግለጫ ለ60ሺህ ግፋዓን አፍ ማርጠቢያ ስለማይሆን። ለነገሩ ማህበራዊ መሠረት አልቦሽ የመሆን ሁነት ነው ያለው።    የአማራ ክልል በወዘተረፈ ችግር እየተጣደፈ ነው። የራሱን ችግር ማስተዳደር ያልቻለ ክልል፤ ተጨማሪ ብሄራዊ ግዴታ ሲታከልበት ለራሱ የውስጥ ችግር መብቃት ያቃተው ሌላ ሃላፊነት #የሚያስቃስት ነው የሚሆነው።    በዚህ 8 ዓመት በዕድሉ ጨምቶ እየተጠቀመ ያለው #ሱማሌ ክልል ነው። የወደፊቱ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሚዛንም ወደዚህ እንደሚያደላ አስባለሁኝ። ከታች ጀምሮ የአወቃቀሩ ስታይል ብቃት ባላቸው ወጣቶች የተገነባ ነው። ሰላምም ነው። በሲዳም የተበራከተ ስሞታ አልሰማም። ደቡብም እንዲሁ። የጠቅላይ ሚር #የአትኩሮት አቅጣጫም #ደቡብ - ገብ ነው።    የሆነ ሆኖ ነገረ ራያ ጉዳይ የሚመለከታቸው አካላት ትኩረታቸውን #ቢያቀኑለት ስል በትህትና አሳስባለሁኝ። ለነገሩ በደባርቅ #ከሱዳን የተፈናቀሉ ወገኖች እንዳሉም ሪፖርተር ላይ በዚያ ሰሞን አንብቤያለሁኝ። ደብረብርሃ...

ሕይወት #የሚቀለው የሰው ልጅ ለመኖር #ፍላጎት ሲኖረው ነው።

ምስል
  ሕይወት #የሚቀለው የሰው ልጅ ለመኖር #ፍላጎት ሲኖረው ነው።    የመኖር #ፍላጎቱ ምኽዋር ደግሞ ሰላም።   ለእኔ ሰላም ፲፫ኛው ፕላኔት ነው።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       ለመኖር ፍላጎት ማመንጨት የሚቻለው #በስኬት ብቻ አይመስለኝም። የተሳካላቸው ፈቅደው መራራውን ስንብት ሲወስኑ ስለምናይም /// ስለማድመጥም። ለመኖር ፍላጎት መኖር #መማርም ብቻውን፤ የመኖር ፍላጎትን ያበረታታል ብዬ አላምንም - እኔው። ለመኖር ፍላጎት አስቻይ ሁኔታ የሽልማት ብዛትም አይመስለኝም። ሽልማቱ ሲቀር ወይንም ሲቀንስ መኖር #በቁዘማ ውስጥ ሊታክት ይችል ይሆናል። የመኖር ፍላጎት እንዲቀጥል ቤተሰብ መመስረት፤ ልጆች መኖር፤ ጥሩ ቢላ ሠርቶ ምቾትን ማስተናገድ ብቻውን ለመኖር ፍላጎት መጨመር ሚና ሊኖረው ይችላል ብዬም አላስብም።   መኖርን የሚያኖረው #የውስጥ #ሰላም ፤ የከባቢ ሰላማዊ አየር፤ ከጭንቀት ጋር የማይነካካ ገጠመኝ ሲኖር የሰው ልጅ መኖርን ሊፈልገው፤ በመኖሩ ተስፋ ሊያደርግ፤ መኖሩን እንደ አንድ #በኽረ መሪ ኃይል አድርጎ ሊወስደው ይችላል ብዬ አስባለሁኝ።   #ሰላም ።   ቁልፍ ግን የሰው ልጅ ለሰላም ያለው አትኩሮቱ ቀጫጫ። የመፍትሄ ጎዳና ግን የሰው ልጅ ለሰላም ያለው አክብሮቱ ስስ። የውስጥ ሐሤት አመንጭ ሆኖ ግን የሰው ልጅ ውስጡን ያሸፈተበት። ሰላም የማሰብ አቅምን አፋፍቶ የህሊና #ብቃትን የሚያጎለብት ግን የሰው ልጅ የሚሰጠው ትዕግስት ኮሳሳ። የፍልስፍና ልቅና ገላጭነት ባለቤት ሆኖ ግን የሰው ልጅ በመቻል አቅም ጥብቆነት እንዲሰቃይ የሚደረገው።   የሰላም ጎዳና፤ ሰላሚዊ - እርምጃ፤ ሰላማዊ - ሩጫም፤ ልቅናም ይሁን ልዕልና፤...

ከአቶ ታደሰ ሞገስ ፔጅ ያገኜሁት ነው። አመሰግናለሁኝ። የእቴጌን ብልህ አመራር ያዘከረ ነው።

ምስል
        ከአቶ ታደሰ ሞገስ ፔጅ ያገኜሁት ነው። አመሰግናለሁኝ። የእቴጌን ብልህ አመራር ያዘከረ ነው።   "የጥሙ ዘበኛ" ኦገስት ዋይልድ ክፍል ስድስ" (ታዴሞ)   "​አሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን ሊያበቃ ጥቂት ዓመታት ሲቀሩት፣ በለንደን ጎዳናዎች ላይ የሚታየው ጭጋግ በፖለቲካው ዓለምም ተጋርዶ ነበር። በወቅቱ የታወቀው እንግሊዛዊ ጋዜጠኛና ዲፕሎማት ኦገስት ዋይልድ (Augustus B. Wylde)፣ ከለንደን ወደ ቀይ ባሕር ዳርቻ የሚወስደውን መርከብ ሲሳፈር፣ ወደፊት የሚጠብቀው ታሪክ የዓለምን ካርታ እንደሚቀይር አልተገነዘበም ነበር።   ​ዋይልድ ተራ መንገደኛ አልነበረም። ቀደም ሲል በምሥራቅ አፍሪካና በሱዳን በኩል በነበረው የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ውስጥ እጁ የነበረበት፣ የቀይ ባሕርን ፖለቲካና የአቢሲኒያን ምድር እንደ እጁ መዳፍ የሚያውቅ አርቆ አሳቢ ነበር። የብሪታንያ መንግሥት "በጣሊያንና በኢትዮጵያ መካከል የሚነሳው እሳት ወዴት ያመራል?" የሚለውን ምስጢር እንዲሰልልና ዘገባ እንዲያቀርብ በስውር ዓይኑን ወደ እርሱ ጥሎ ነበር።   ​ከለንደን ተነስቶ በሱዌዝ ካናል በኩል በማለፍ፣ ቀይ ባሕርን አቋርጦ ምጽዋ ደረሰ። በወቅቱ ምጽዋ በጣሊያኖች እጅ ብትሆንም፣ ዋይልድ ግን ወደ መረብ ወንዝ ተሻግሮ የንጉሠ ነገሥቱን ግርማ ለማየት ቆርጦ ተነሳ። በአህያና በበቅሎ ጀርባ ተጭኖ፣ አስቸጋሪዎቹን የሰሜን ተራሮች እያቋረጠ፣ በኤርትራ በኩል አድርጎ ወደ ትግራይ ምድር ዘለቀ።   ​ወደ መቀሌ ሲቃረብ፣ በየመንገዱ የሚያያቸው ነገሮች ሁሉ ያስገርሙት ነበር። "እነዚህ ሰዎች እንዴት በጎራዴና በናስ ጠመንጃ ታላቋን አውሮፓዊት ሀገር ይጋፈጣሉ?" የሚለው ጥያቄ በአዕምሮው ይመላለሳል። ነገር ግን መቀሌ ሲደርስ ያየው ...